🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ገና እንዘምራለን እንደ መላእክቱ
ብርሃንን ለብሰን ገና እንዘምራለን
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርሰቲያን አሰተምሮ ና ሰርአት የጠበቁ
✥👉መንፈሳዊ ትምህርቶች
✥👉መንፈሳዊ መዝሙሮች
✥👉መንፈሳዊ ንግሰ እናሳዉቃለን
✥👉መንፈሳዊ ምክር ነክ ፁሁፍ
✥👉መንፈሳዊ ታሪኮች

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


♦ Giiftii Keenya /እመቤታችን/ ♦

Giiftii keenyaa Araarsummaa keen
Dubroo Maariyaam Araarsummaa keen
Fayyisaa Addunyaa Raajii Hojjete bishaan Qaanaatiin *2

Raajii Waaqayyootif.... Bishaan Qaanaatiin
Carroomuun Filamte
Qaanaa Za Galiilaan
Kan jalqabaa taate
Qaanaa Taasisuuf kan jalqabaa raajii Hojjete
Kabajni Dubroof Araarsummaan ishees mullate


Beektee Waan jetteeniif.... Bishaan Qaanaatiin
Waynii Hin Qabanii
Bishaan Wayni yo ta'u
Hunduu ilaalani
Qaanaa Taasisuuf kan jalqabaa raajii Hojjete
Kabajni Dubroof Araarsummaan ishees mullate

Keessummeessitoonni.... Bishaan Qaanaatiin
Yaaddoon isaan raase
Ilmi Dubroo maaryaam
Dhiphinaa isaan baase
Qaanaa Taasisuuf kan jalqabaa raajii Hojjete
Kabajni Dubroof Araarsummaan ishees mullate


Nutis ni Amanna.... Bishaan Qaanaatiin
Jechasheen dubbattu
Waadaasheef Galameen
Hundi akka sirratu
Qaanaa Taasisuuf kan jalqabaa raajii Hojjete
Kabajni Dubroof Araarsummaan ishees mullate

ዘማሪ ተፈራ በቀለ




✞ በሐዘኔ ደራሽ ነሽ✞

በሐዘኔ ደራሽ ነሽ በጭንቀቴ 
ለችግሬም ደራሽ ነሽ 
የአምላኬ እናት ጌታዬ እናት 
ድንግል እመቤቴ ወላዲተ ቃል 

መልካሚቷ ርግብ ድንግል እመቤቴ 
ማርያም እናቴ ነሽ           " 
ከፍጥረታት ሁሉ            " 
ገናና ነው ክብርሽ           " 
የሐዘኔ መጽናኛ              " 
እንባዬን አባሽ ነሽ           " 

አዝ••••••••••••••••••••

ዋሻ መጠለያ  ድንግል  እመቤቴ 
የዘላለም ቤቴ                " 
መንገድ ስሄድ ስንቄ        " 
መጠጤ ነሽ ምግቤ       " 
እመ አምላክ ስጠራሽ     " 
ይጠፋል ረሀቤ             " 

አዝ••••••••••••••••••••

የእናትነትሽን ድንግል እመቤቴ 
ፍቅርሽን አየሁኝ        " 
ጎጆዬን ስትሞዪው     " 
ባዶ የሆነውን           " 
አንቺ እያለሽልኝ        " 
ምን እሆናለሁኝ    


አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል

አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል
አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል/2/

በመስቀል ተሰቅለህ መድኃኒት ሆነሃል
አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል
ሳታቆስል በፍቅርህ ማርከኸን
ከፊት ቀድመህ በድል አስከተልከን
በደለኞች እኛ ሆነን ሳለ
አንተ ከፍለህ ክሳችን ተጣለ
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን
አዝ--------------
እንደሰማን እንዲሁ አይተናል
ማዳንህን ቀምሰን መስክረናል
የእግዚአብሔር በግ ቆስለህ የፈወስከን
ወደ ድንቁ ብርሃን ያሻገርከን
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን
አዝ--------------
አፅናንተኸን ሞትን አስተከዝከው
ወደ ጥልቁ እንዲወርድ አዘዝከው
ባንተ ፍቅር ምርኮ በዝቶልናል
ማማ ሆነህ ከፍ ከፍ ብለናል
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን
አዝ---------------
ስንሸሽህ እየተከተልከን
ልጆች አርገህ በክብር አስጌጥከን
ተቅበዝባዡን ሰብስበሃልና
ከማደሪያህ ይፈልቃል ምስጋና
ኪርያላይሶን ኪርያላሶን
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@zmaredawt_zeortodocs
@zmaredawt_zeortodocs
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯


✞ሀና ብርክት✞

ሀና ብርክት ፀልይ በእንቲያነ(2)
ፀልይለነወሠአሊነነ(2)
ምስለእያቄም አቡነ

አዝ••••••••••••••••••••

መካን ሆና ሣለ ስታዝን ዘወትር
ልመናዋን ሠማት እግዚአብሔር
በትዕግስት ስትጠብቅ ለሊት ና ቀን
ሀዘናነ ማስርሻ ሠጣት ማርያምን

አዝ••••••••••••••••••••

የሀና መፅነሣን ታርጋግት ዳሳ
ማዬት  የተሣናት አየች ተፈውሣ
ሠላም ለኪ ሀና እሙ ለሠማይ
አይተናል ክብርሽን ልትባርኪን ነይ

አዝ••••••••••••••••••••

ሙቱን ስታስነሣ እዉር ስታበራ
በቅናት ተነሡ አይሁድ በየተራ
ከእግዛብሄር ተልኮ ቅዱስ ገብርኤል
ሊባኖስ ወሠዳት እንድትከለል


🛑#ሶበ_ተዘከርነሀ_ለጺወን🛑



ሶበ ተዘከርነሀ ለጺወን Ⓧ2
ውስተ አፍላገ ባቢሎን እየ
ነበርነ ወበ ከይነ እንዚራቲነ
ሰቀልነ ውስተ ኩይሀቲያⓍ2


ባሰብናት ጊዜ ጺወንን Ⓧ2
በባቢሎን ወንዞች አጠገብ
ተቀምጠናል አለቀስን
መሰንቆአችንን ሰቀልን በዛፎቿ ላይ Ⓧ2

ጥኑ መከራ ተቀበልን ተጨንቅን በፈተና
የደውይ ሞት በላያችን እንደዝናብ ወርዷልና
አህዛብም ዘበቱብን እንዲህ ብለውበየተራ
ዘመሩለት ለአምላካችን ቢያድናቸው ከመከራ

እግዚአብሄር ጺወንን በመንግስቱ መርጧታልና ማደርያው ትሆነው ዘንድ ወዷታልና
ጺወን ሆይ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ጺወን ሆይ እናታችን ቅድስት ቤቴ ክርስቲያን
አንቺን ብንረሳ ቀኛችን ትርሳን

አዝ.........

የማረኩን በጦራቸው በሀይላቸው የተመኩ
በጺወን ደጅ ያለ ፍርሀት የጺወንን ክብሯን ነኩ
ይህን ያየ ከላይ ሆኖ በደመና ተሸፍኖ
ባቢሎንን አሻገረን የማረኩን እንበትሎን

እግዚአብሄር ጺወንን:::::::::::

አዝ.........

ስጋችንን ይገል ዘንድ የሞት ጥላ ቢያጠላ
እናልፋለን ሁሉን ባንቺ የአምላክ እናት ድንግል ማርያም
ቅድስት ሆይ ከባረክሽን እንድናለን ከድዌአችን
ለስጋና ለነፍሳችን መድሀኒት ነሽ እናታችን

እግዚአብሄር ጺወንን:::::::::::

አዝ ..........

ባሰብናት ጊዜ ጺወንን.........

🌺🕊🌺🕊🌺🕊🌺


🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

     ⬇️ ለመቀላቀል⬇️
       ⬇️⬇️⬇️⬇️
            #ሼር
    🙏 🙏🙏


✞ በሀዘኔ በጭንቀቴ

በሀዘኔ በጭንቀቴ መፅናኛዬ ነሽ እረዳቴ
እመአምላክ አደራ ድንግል እመቤቴ 2

ለአለም ተዘርግቶ እጄ ባዶ ሆኗል
የእራሴ ላይ አክሊል ተሽንቀጥሮ ወድቋል
ከኤልዛቤል ሸሽቼ መጣሁኝ ወደ አንቺ
የጎሰቆልኩትን እኔን ተመልከቺ

አዝ----------------

የእግሬ መሰናክል ለአለም ደስታ ነው
ተስፋቢስ መሆኔ ለጠላቴ ድል ነው
የደስታ መፍሰሻ የኤልሳቤጥ ዘመድ
እንዳልሰናከል ምሪኝ በመንገድ

አዝ--------------

አለም ትለኛለች ተስፋቢስ ብቸኛ
ሳለቅስ ሳነባ አይታኛለች እና
ከቤተ መቅደሱ ለእኔስ እናት አለኝ
በአዘኔ ሰዓት አለው የምትለኝ

አዝ----------------

ከአመድ የወደቀ ትንሽ ገንዘብ አለሽ
ልብሽ እራርቶልኝ ፈልጊኝ አጥብቀሽ
እምነቴ እዳይደክም እዳልጠፋ ልጅሽ
አድጌአለሁ እና ከደጀ ሰላምሽ

                   ዘማሪ
      ቀሲስ አሸናፊ ገብረ-ማርያም


✟እሰይ አበራ መስቀሉ✟

እሰይ አበራ መስቀሉ ለአለም ሁሉ
ይለኮስ ችቦ ደመራ ጨለማው ይብራ


የጥል ግድግዳ ፈረሰ   እሰይ አበራ
ዳግም እንባችን ታበሰ  እሰይ አበራ
ህይወት ነው ለኛ መስቀሉ  እሰይ አበራ
ታምነናልና  በቃሉ  እሰይ አበራ

አዝ_____

አይሁድ በክፋት ቢነሱ  እሰይ አበራ
የሀሰት ካባ ቢለብሱ  እሰይ አበራ
ዕሌኒ ሄደች ገስግሳ  እሰይ አበራ
ቆስጦንጢኖስን አንግሳ  እሰይ አበራ

አዝ____

ዛሬም ሀይል አለው መስቀሉ  እሰይ አበራ
አንድ አልፎበታል ለሁሉ  እሰይ አበራ
አልሸሸገውም ተራ ውነት  እሰይ አበራ
መውጊያውን ስለወጋበት  እሰይ አበራ

አዝ____

የመስቀሉን ቃል ላመነው  እሰይ አበራ
ከሞት ማምለጫ ስንቅ ነው  እሰይ አበራ
ለአለም ቢመስል ሞኝነት  እሰይ አበራ
ተከፍሎበታል ስርየት  እሰይ አበራ


መስቀል ኃይላችን ✞

መስቀል(፪)ኃይላችን ጠላትን ማጥፊያችን/፪/
በመስቀል እንመካለን እንድንበታለን/፪/

የክርስቲያን ጋሻ መስቀል ኃይላችን
የክርስቲያን ጦር መስቀል ኃይላችን
ዕፀ መስቀሉ ነው መስቀል ኃይላችን
የማያሳፍር መስቀል ኃይላችን
/አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞
መድኃኒት የሚሆን መስቀል ኃይላችን
ደሙ ፈሶበታል መስቀል ኃይላችን
መስቀሉን ጥግ አድርጉ መስቀል ኃይላችን
እርሱ ይፈውሳል መስቀል ኃይላችን
      
/አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞
ክርስቶስ በደሙ መስቀል ኃይላችን
ስለቀደሰው መስቀል ኃይላችን
መስቀል ላመነበት መስቀል ኃይላችን
ድል ማድረጊያ ነው መስቀል ኃይላችን
      
/አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞
የክርስቶስ ሥጋ መስቀል ኃይላችን
የተፈተተበት መስቀል ኃይላችን
መስቀል ኃይላችን ነው መስቀል ኃይላችን
የምንድንበት መስቀል ኃይላችን
       /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞
ሕይወትን ለማግኘት መስቀል ኃይላችን
ከሞት ለመዳን መስቀል ኃይላችን
መመኪያ ኃይላችን መስቀል ኃይላችን
መስቀል አለልልን መስቀል ኃይላችን

👉ዘማሪ ሚኪያስ ፀጋዬ
👉ዘማሪ ዲያቆን ቀዳሜፀጋ ዮሐንስ
👉ዘማሪ ሊቀ ዲያቆናት ነቢዩ ሣሙኤል
👉ዘማሪ አቤል ተስፋዬ
👉ዘማሪ በርሱፈቃድ አንዳርጋቸው


✞ መስቀል አበባ ✞

መስቀል አበባ ነህ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ/2/
      
መስቀል አበባ   ተቀብሮ ሲኖር
አደይ አበባ       ስነ ሥቅለቱ
መስቀል አበባ   ዕሌኒ አገኘች
አደይ አበባ       ደገኛይቱ

       /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

መስቀል አበባ   ጥራጊ ሞልተው
አደይ አበባ       አይሁድ በክፋት
መስቀል አበባ   ጢሱ ሰገደ
አደይ አበባ       መስቀል ካለበት

       /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

መስቀል አበባ   ወንዙ ጅረቱ
አደይ አበባ       ሸለቆው ዱሩ
መስቀል አበባ   አሸብርቀው ደምቀው
አደይ አበባ       ለአንተ መሰከሩ


✞ እሰይ እልል በሉ ✞

እሰይ እልል በሉ
ተገኘ መስቀሉ  /2/

የጥል ግድግዳ አበባ
የፈረሰበት  አበባ
ሰው ከእግዚአብሔር ጋር  አበባ
የታረቀበት  አበባ
የእግዚአብሔር ልጅ  አበባ
የነገሰበት  አበባ
የሞት አበጋዝ  አበባ
የወደቀበት  አበባ

   /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

አይሁድ በቅናት  አበባ
መስቀሉን ቀብረው  አበባ
ቢከድኑት እንኳን  አበባ
በቆሻሻቸው  አበባ
ጌታን መቃወም  አበባ
ስለማይችሉ  አበባ
ይኸው ተገኘ  አበባ
ወጣ መስቀሉ  አበባ

   /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

ደጉ ኪራኮስ  አበባ
ሽማግሌው  አበባ
እሌኒን መራ  አበባ 
በደመራው  አበባ
ጌታ በሱ ላይ  አበባ
በመሰቀሉ  አበባ
ጢሱ ሰገደ  አበባ 
ወደ መስቀሉ  አበባ

   /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

የእምነት ምልክት  አበባ
መስቀል ነውና  አበባ
ተራራው ሜዳ  አበባ
ሆነ እንደገና  አበባ
እንደ ተነሳው  አበባ
ጌታ እንደቃሉ  አበባ
ከጉድጓድ ወጣ  አበባ
እፀ መስቀሉ  አበባ

   /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

እኛም በመስቀል  አበባ
እንመካለን  አበባ
በእግዚአብሔር ጥበብ  አበባ
መቼ እናፍራለን  አበባ
ሞኝነት እንኳን  አበባ
ቢሆን ለዓለም  አበባ
ኃይል እፀ ወይን ነው  አበባ
ለዘላለም  አበባ

   /አዝ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

ግድግዳው ፈርሷል  አበባ
የልዩነቱ  አበባ
ምድርና ሰማይ  አበባ
ሆኑ እንደ ጥንቱ  አበባ
ነብስና ስጋ  አበባ
በሱ ታርቀዋል  አበባ
ሕዝብና አሕዛብ  አበባ
ወንድም ሆነዋል  አበባ     


✟ መስቀል ተመርኩዘን ✟

መስቀል ተመርኩዘን ወንጌል ተጫምተን
ሀይማኖትን ሰብከን በክርስቶስ አምነን
ማን ያሸንፈናል እኛ ክርስቲያንን ክርስቶስ አለንን


ንግስቲቷ ዕሌን በጣም የታደለች
በእጣን ጢስ ተመርታ መስቀሉን አገኘች
መድሃኒት ስትፈልግ ኪራኮስን ይዛ
መስቀሉን አገኘች የአለሙን ቤዛ

ንዑ ንወድሱ ለእጸ መስቀል
የተሸከመውን የአምላክን ቃል
ንዑ ንወድሳ ለማርያም ድንግል
አክሊለ ምዕመናን ምክሃ ደናግል

ሙታንም ተነስተው ያመሰገኑት
እፀ መስቀሉ ነው የኛ መድሃኒት
መስቀል ምርኩዛችን ጎዳና ወንጌል
ወደ ገነት እንጂ አንሄድም ሲኦል




✞የመስቀሉ ፍቅር ሲገባን✞

የመስቀሉ ፍቅር ሲገባን (4)
እመቤታችንን እንወዳታለን
የመስቀሉ ፍቅር የገባቸው (4)
እመቤታችን አለች ከጎናቸው

አባ ሕርያቆስ አባታችን
የመስቀሉ ነገር ቢገባው
ልቤ አፈለቀ አለ መልካም ነገር
ከእመቤቴ ጋራ ሲነጋገር
ከድንግል ማርያም ጋር ሲነጋገር


ነይ ነይ እምዬ ማርያም
ነይ ነይ ቤዛዊት አለም
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (2)
አንዱ ሃገር ስትሄድ መድሃኒአለም አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (2)
አንዱ ሃገር ስትሄድ ኢየሱስ አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (2)
አንዱ ሃገር ስትሄድ ክርስቶስ አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (2)

ለመናኒው ፀሎት ልዩ እጣን
የዋሻው ሻማ ነሽ እመብሃን
መአዛሽ ሸተተኝ ከግሸን
ትናፍቂኛለሽ ምን ልሁን
ትርቢኝማለሽ ምን ልሁን

ዳዊት በመዝሙሩ ያነሳሻል
የያዕቆብ ድንኳን ነሽ ይልሻል
የእግዚአብሔር ሃገር የሚሉሽ
እመቤቴ ማርያም አንቺ ነሽ (2)

ቤተልሔም ስሄድ አይሻለሁ
ቀራኒዮ ስሄድ አይሻለሁ
ፍጹም አትለይም ከልጅሽ
የአንቺስ ልዩ ነው ፍቅርሽ (2)


የመስቀል መዝሙሮች ይለቀቁ?


✞ይላል አንደበቴ✞

ይላል አንደበቴ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው
አይተወኝምና ወላጅ እንደሌለው
ትናንት የጠበቀኝ የነገም ተስፋዬ
ትልሃለች ነፍሴ ፍቅር ነህ ጌታዬ
አዝ----------
የትናንት ሕይወቴን ዞር ብዬ ሳየው
ማምለጫ የሌለው አጥሩም እሾህ ነው
ወደ እረፍቴ ወጣሁ ይድረስ ምስጋናዬ
ደጆች ቢዘጉብኝ በር ሆኖኝ ጌታዬ (2)
አዝ----------
በጥልቁ በረሃ ምግብ መጠጥ ሆኖኝ
መንገዴን አቀናው እጄን በአፌ አስጫነኝ
በእሳትና ውሃ መካከል አልፌ
ተመስገን እላለሁ ቅኔ ሞልቶት አፌ (2)
አዝ----------
የብቸኝነቴን ማዕበል ገስጿል
ለእኔ ብርሃን ሆኖ ለከሳሽ ጨልሟል
ቀስቱን እያጠፈ ታደገኝ ከስቃይ
የጌታዬ ሃሳብ ፍቅር ነው በእኔ ላይ (2)
አዝ----------
ትናንት ዛሬ ነገ ዘላለም ጠባቂ
የልቤን ፍላጎት ሳልነግረው አዋቂ
በባሕርይው ቅዱስ የሌለው አምሳያ
ስሙ ወደቤ ነው መልህቄን መጣያ

ሊቀ መዘምራን
ቴዎድሮስ ዮሴፍ


✞የካህናት አለቃ✞

የካህናት አለቃ ኢየሱስ ሲመጣ
የብርሃን ድንኳን ስትታይ ተገልጣ
ለጽድቁ ስርዓት ምሥጢሩ ሲፈጸም
በበቤተመቅደሱ ይታወጃል ሰላም

ከፀሐይ አብርተው ከከዋክብት ደምቀው
ካህናት ሲታዩ በዕንቁ ተሽቆጥቁጠው
ቀሳውስት በቀኙ ዲያቆናት በግራው
ቆመው ይታያሉ ስርዐት ሊያሳያቸው
አዝ= = = = =
ከካህናት አለቃ ከጌታችን ጋራ
ልታገለግሉ ስማችሁ ሲጠራ
በሰማይ መቅደሱ ፏፏቴ መስላችሁ
እንዴት ያማረ ነው አገልግሎታቾሁ
አዝ= = = = =
የወርቅ ሻሻቴ የምትመስሉ ፍጹም
እናንተ ዲያቆን እስከ ዘለዓለም
ምስጢሩን ልታዩ በሰማዩ መቅደስ
በእሳት ሰረገላ ጌታ ሲመላለስ
አዝ= = = = =
የአንድነት ጉባዔ ከሚደረግበት
ለተጋበዛችሁ ወደዚያች ሠርግ ቤት
ምዕመናንን አይቶ አምላክ ተደሰተ
የብርሃን ከዋክብት የምትመስሉ እናንተ
አዝ= = = = =
በፍጹም ትህትና ብታገለግሉ
የእናንተ ሞገስ ነው ክብር ነው ይህ ሁሉ
ለወንጌሉ ስርዐት በጽናት ቆማችሁ
ሳትነዋወጹ ክብርን ያውርሳችሁ

        መዝሙር
      ይልማ ኃይሉ


መሐረኒ ድንግል | ማሪኝ ድንግል

መሀረኒ ድንግል ወተሰሀለኒ በበዘመኑ 2×
ለእመ መሀርከኒ 3× አንቲ ዘይኩነኒ መኑ
ኮናኔ ስጋ ወነብስ 3× ወልድኪ ያኮኑ

ይጠሩሻል ካህናቱ
ንዒ ይሉሻል በሳታቱ
ለለመነሽ የማትቀሪ
በልቤ ውስጥ ፀንተሽ ኑሪ
የስጋና የነብስ ፈራጅ 3× ልጅሽ አይደለም ወይ

መሀረኒ ድንግል ወተሰሀለኒ በበዘመኑ 2×
ለእመ መሀርከኒ 3× አንቲ ዘይኩነኒ መኑ
   
ያዲስ ኪዳን ኪሩ የሆንሽ
ለምኚልን ካንዱ ልጅሽ
ርግብየ ሰናይትየ
ነይ ወደኔ ነይ ወልድየ
ኮናኔ ስጋ ወነብስ 3× ወልድኪ ያኮኑ
..............................................
ማሪኝ ድንግል ማርያም ይቅርም በይኝ በየዘመኑ 2×
ድንግል ሆይ ከማርሽኝ እናቴ ሆይ ከማርሽኝ
ድንግል ሆይ ከማርሽኝ ልጅሽ አይፈርድብኝ


ባለም መኖር ሰልችቶኛል
መልካም መስራት አቅቶኛል
እጄን ይዘሽ ድንግል ምሪኝ
አዛኚቷ  አትለይኝ
የስጋና የነብስ ፈራጅ 3× ልጅሽ አይደለም ወይ

መሀረኒ ድንግል ወተሰሀለኒ በበዘመኑ 2×
ለእመ መሀርከኒ 3× አንቲ ዘይኩነኒ መኑ

እበላለው ብዬ ማርያም
እመካለው ባንቺ አላፍርም
ካንቺ ወዴት እሄዳለው
ስምሽን ልጥራው እፅናናለው
ኮናኔ ስጋ ወነብስ 3× ወልድኪ ያኮኑ

ማሪኝ ድንግል ማርያም ይቅርም በይኝ በየዘመኑ 2×
ድንግል ሆይ ከማርሽኝ እናቴ ሆይ ከማርሽኝ
ድንግል ሆይ ከማርሽኝ ልጅሽ አይፈርድብኝ


ዘማሪ በሱፍቃድ አንዳርጋቸው


እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ
ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አደረሳችሁ

🌼 መልካም አዲስ አመት 🌼

5k 0 10 1 33

🌼 ምን ብትወደኝነው 🌼

ምን ብትወደኝ ነው ምን ብታስበኝ
አዲስ ዘመንን ቀን ያሳየኸኝ
ኦ አምላኬ ዘመንን ካየሁ ከተሻገርኩኝ
ኦ ጌታዬ እዘምራለሁ ስቡህ እያልኩኝ/2/

ጠዋትም የለኝ ካንተ በቀር ማለዳዬ ነህ
ማምሻዬም አንተ አልሻገርም አንተ ካልፈቀድህ
ማዕበል ወጀቡን አሳልፈህ ጨለማውን አብርተህ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/

     /አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼

አልፍ እንድትሆን አንተ የባረካት ከመሬት ወድቃ
ትላንትናዬን ወዜን ባርከኸው ለዚህ ብበቃ
ባጌጠችው የምድር መሀል ሆኜ
እቀኛለሁ ስለአዳኜ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/

     /አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼

ፍሬ ፈልገህ መጣህ ወደኔ በብርሀን ጸዳል
ፀሐይ አውጥተህ ልትባርከው ጌታ ፈቅደሀል
ያንተ ወንዞች ውሃ ከተሞሉ
ተራራዎችም ምስጋናህን ያመጣሉ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/

     /አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼

ማለፍ በክንድህ አዲስ ዘመንን ላንተ መዋጀት
ግዛው ዘመኔን ውረስ አምላኬ የኔን ማንነት
አዝማናቱ ስራህን እያሳየ
ልሁንልህ ከዓለም የተለየ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/

     /አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼

ቀንን ብቆጥር ዘመን ባሰላ ካልተለወጥኩኝ
ከጸጋህ ዙፋን በዕምነት ቀርቤ ካልተፈወስኩኝ
ምን ሊረባኝ ካንተ ጋር ካላረጀሁ
ያለቃልህ በዘመን እንዲያው ባውጀው
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/

ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.