🌼 ምን ብትወደኝነው 🌼
ምን ብትወደኝ ነው ምን ብታስበኝ
አዲስ ዘመንን ቀን ያሳየኸኝ
ኦ አምላኬ ዘመንን ካየሁ ከተሻገርኩኝ
ኦ ጌታዬ እዘምራለሁ ስቡህ እያልኩኝ/2/
ጠዋትም የለኝ ካንተ በቀር ማለዳዬ ነህ
ማምሻዬም አንተ አልሻገርም አንተ ካልፈቀድህ
ማዕበል ወጀቡን አሳልፈህ ጨለማውን አብርተህ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/
/አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼አልፍ እንድትሆን አንተ የባረካት ከመሬት ወድቃ
ትላንትናዬን ወዜን ባርከኸው ለዚህ ብበቃ
ባጌጠችው የምድር መሀል ሆኜ
እቀኛለሁ ስለአዳኜ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/
/አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼 ፍሬ ፈልገህ መጣህ ወደኔ በብርሀን ጸዳል
ፀሐይ አውጥተህ ልትባርከው ጌታ ፈቅደሀል
ያንተ ወንዞች ውሃ ከተሞሉ
ተራራዎችም ምስጋናህን ያመጣሉ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/
/አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼ማለፍ በክንድህ አዲስ ዘመንን ላንተ መዋጀት
ግዛው ዘመኔን ውረስ አምላኬ የኔን ማንነት
አዝማናቱ ስራህን እያሳየ
ልሁንልህ ከዓለም የተለየ
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/
/አዝ 🌼 🌼 🌼 🌼ቀንን ብቆጥር ዘመን ባሰላ ካልተለወጥኩኝ
ከጸጋህ ዙፋን በዕምነት ቀርቤ ካልተፈወስኩኝ
ምን ሊረባኝ ካንተ ጋር ካላረጀሁ
ያለቃልህ በዘመን እንዲያው ባውጀው
በአዲስ ዘመን ጌታዬ ስራኝና
ላገልግልህ በዜማዬ እንደገና/2/
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ