💛💞መልካም ልቦች™💞💛


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


🥀♡ ማፍቀር ስትጀምር ከእምነት ጀምር ♡🥀
⚡️WELLCOM TO MELKAM LBOCH 💜
💚 በዚህ ቻናል ውስጥ ደስ የሚሉ የ ፍቅር ቃላቶች፣ግጥሞች፣የፍቅር ታሪኮች ያገኛሉ !
● ቻናላችንን SHARE ያድርጉ 🙏
➤ For any promotion and Advertising 📩
👉 @Z_afro ያነጋግሩ::

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ከግቢ ማንም ሳያየኝ በፍጥነት ወጣሁ ወደፋኖስጋ አመራሁ ምን ምኗ ላይ እንደምወጋት ቀጭንቅላቴ እየተመላለሰ ነው እዛ የተደረስኩት ቀኑ እየጨላለመ ነው የቤቷ ፊት ለፊት የደረስኩት ደወለኩላት አታነሳም ያለማቋረጥ ደወልኩ አነሳችው ከቤትሽ ፊት ለፊት ቆሚያለሁ በእህትሽ ይዤሻለሁ አንዴ ውጭ አልኳት።

የሚቆራረጠውን ድምፄን እንዳታውቅብኝና እንዳትጠራጠር ለማድረግ የቻልኩትን እየሞከርኩ ስልኩን ዘጋሁት መንጎራደድ ጀመርኩ ቀና ብዬ ወደሰማይ ተመለከትኩና አንተኮ አታደርገውም አደል አሁን ቤት ስደርስ እናቴን አስቀምጠህ ትጠብቀኛለህ እንዴ.... አታሳዝንህም ምን ቻቃለች እሷ የኔ እናትኮ ምስኪን ናት እኔ ብሆን ጨክኜ አልገላትም አንተም አታደርገውም ከፈጣሪጋ ያለኝን ንግግር ፋኖስ አቋረጠችኝ ከቤቷ ፎጣውን እላይዋ ላይ ጣል እንዳደረገች ወጣች ።

ከኋላ የከተትኩት ቢላ አወጣሁና እጄን ወደኋላ እንዳደረኩ ያዝኩት ልክ አጠገቤ ስትደርስ.....


ይቀጥላል...

🟫ፀሀፊ ✍️ ማኔ

🔻ክፍል  9️⃣ ነገ ማታ2️⃣🟰3️⃣0️⃣  ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like💝 ማድረግ አይርሱ።
🔺🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!
😀
 
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔  @MELKAM_LBOCH13 💔

➖የዩቲዩ ገፃችን➖
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333
https://www.youtube.com/@Kezerareaction33


      🔸🔸🔺🔺🔹🔸

      
❤️ የፍቅር ጥግ ❤️


ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ  ታሪክ
❤️

ፀሀፊ
✍️ ማኔ

                        ክፍል  
8️⃣

እቃ ስታነሳ ሁላ ሚከፋው አባት ነበረኝ።

እኔም ተወለድኩ ስራ እረፍት ጠይቆ እንደ እናት አረሳት እሷ ምንም ዘመድ ስላልነበራት ሚጠይቃት ሰው እንኳን የላትም።
ብቻ ምን አደከመሽ እኔ ተወልጄ ሁለት አመት ከሆነኝ ቡሀላ እሱ እንደአራዊት ሌሊት እየወጣ ሌሊት እየገባ አንቀባሮ ሲያኖራት እናቴ ጠገበችና እዛው ግቢ ተከራይቶ ከሚኖር ወንደላጤጋ መማገጥ ጀመረች።

አባቴ ተደጋጋሚ ጊዜ ወሬ ቢደርሰውም ንቆ ያልፈው ነበር።
የሆነ ቀን ግን እጅ ከፍንጅ ያዛት እና ተጣሉ እራሷ አኩርፋ ከቤት ጥላ ወጣች ከወር ቡሀላ ግን እኔ እየተጎዳሁ እንደሆነ ስላሰበ መልሶ እራሱ ለምኖ ታረቃት እሷ ግን ይቅርታ አድርጎላት እንኳን አመሏን አልተወችም አባቴ ደሞ ከምልሽ በላይ ይወዳት ያፈቅራት ነበር ከሷ ሌላ ሴት ምድር ላይ የተፈጠረች አይመስለውም እሷን አጥቶ መኖር መተንፈስ እንደሚችል አያምንም።
ብቻ በጣም ብዙ ጊዜ እየታረቁ እየተጣሉ ቆዩ በመጨረሻም አታስገድደኝ እኔ ከሌላ ሰው ፍቅር ይዞኛል አንተንም ልጄንም አልፈልጋችሁም አለችው።
አባቴ ተስፋ አልቆረጠም ያለማቋረጥ ሽማግሌ እየላከ ሰላም ሲነሳት ወደሌላ ከተማ አድራሻዋን አጥፍታ ጠፋች አባቴ በሷ ናፍቆት ብዙ ተሰቃየ እሷ ልቴድበት ትችላለች ብሎ ያሰበው ቦታ በሙሉ እኔን እየያዘ እየዞረ ይፈልጋት ነበር በሷ ምክንያት ከስራ ተባረረ።
የምንበላው አጣን አባቴ ግን በዛን ሰአት የምንበላው ከማጣታችን በላይ የሷ ካጠገቡ መራቅ አብዝቶ ያሳስበው ነበር እኔንም በጣም ስለሚወደኝ ለደቂቃ ካይኑ ዞር እንድል አይፈልግም።

የሆነ ቀን የድሮ አከራያችን የት እንዳለች ነገረችው እኔን ይዞ ከአክስቴ ብር ተበድሮ ያለችበት ይዞኝ ሄደ እናቴ ከሌላ ሰው አርግዛ ለመውለድ ተቃርባ ነበር ያንን የተመለከተው አባቴ እህቱጋ ሄዶ አደራ ሰቷት እሱ ሄዶ እራሱን አጠፋ ።

በሰአቱ አክስቴ መሀን ስለነበረች  እኔን እንደልጇ ተቀበለችኝ እናትም አባትም ሆና አሳደገችኝ።
ግን እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ ስለናቴ ምሰማው ነገር ሴትን ልጅ እንድጠላና ፍቅር ሚባለው ነገር በራሱ የሰው ልጅ የመሞቿ ገመድ እንደሆነ እያሰብኩ ነው ያደኩት።መንገድ ላይ ወንድና ሴት ተቃቅፈው ሲሄድ የወንዱ መሞቻ ቀን መች ይሆን እያልኩ ነው የኖርኩት።
ገባሽ ሴትን ልጅ አደለም ለፍቅር ለጓደኞነት እራሱ ለመቅረብ አስቤ ሞክሬ አላቅም ሁሉም ሴቶች እንደናቴ ይመስሉኛል ልክ እናቴ አባቴን ለሞት እንደዳረገችው እኔም ባፈቀርኳት ሴት የምጠፋ ይመስለኛል ።
ለዛ ነው እራሴን ከሴት ልጅና ከፍቅር ማርቀው።
ደሞ የዛን ቀን እህትሽ ከነዩኒፎርሟ መጥታ እወድሀለሁ ተረዳኝ ስትለኝ ገና ህፃን እይደሆነችና አርፋ ትምህርቷን እንድትማር ስነግራት እሷ ግን ግግም ብላ ስልክህን ስጠኝ ስትለኝ ገና በዛ እድሜዋ ለዛውም ከነዪኒፎርሟ እንደዛ መሆኗ አናዶኝ ነው በጥፊ የመታኋት እንጂ እኔ እንድትሞት አደለም ከልቤ ፀፅቶኛል አስተዳደጌ ነው እንደዚህ ያደረገኝ አልኳት።
አደል አትርሳ አሳዳጊህምኮ ሴት ናት ለሴት ልጅ ጥላቻ ካለህ እሷን እንዴት በዚህ ልክ ልትወዳት ቻልክ አለችኝ።

ንግግሯ አናደደኝ እማዬንማ የምወዳት ከልቧ ሴት ስለሆነች ነው ገባሽ ለኔ ላልወለደችው ልጇ ህይወቷን ለመስጠት ስለማታመነታ ነው።
ጠያቂ ዘመድ ባጣሁ ሰአት እሷ ብቻዋን ዘመድ አዝማድ ሆና ስላሳደገችኝ ነው።
አንድም ቀን የናትና አባቴን አለመኖር እንዳስታውለው እድል ስላልሰጠችኝ ነው

በኔ ምክንያት ስትሰደብ ስትገፋ የሰውን አይን ሲገርፋት አንገቷን ደፍታ ስላሳለፈች ነው።
ኮንፊደንስ ያለው ጠንካራ ወይድ አድርጋ ስላሳደገችኝ ነው ገባሽ እማዬን መጥላት ማለት እራሴን መጥላት ነው ።
ደሞ ይቅርታ አድርጊልኝና እህትሽንኮ እኔ አፍቅሪኝ አላልኳትም እኔ እንደሌሎች ወንዶች አፈቅርሻለሁ እወድሻለሁ ብዬ አልሸወድኳትም በህይወቷ በሴትነቷ አልተጫወትኩም እኔን እንደጠላት ማየትሽ እራሱ ተገቢ አደለም።በእርግጥ ሴት ልጅ ላይ እጅ ማንሳት ወንድነት አደለም አጥፍቻለሁ እኔም ካለፈ ቡሀላ ፀፅቶኝ ነበር ግን እኔ እንደሞተች እንደዚህ አይነት አደጋ የደረሰባት ሴት እሷ እንደሆነች አላወኩም አንድ ተማሪ ተገጭታ ሞተች የሚል ወሬ ብቻ ነው የሰማሁት አልኳት።

ዝም አለች በእጇ ሂድ የሚል ምልክት ሰጠችኝ ከዛ በላይ እዛ ቦታ መቆየቴ አስፈላጊነቱ አልታየኝም ስትረጋጋ ባወራት እንደሚሻል አስቤ ተነስቼ ሄድኩኝ ጓደኞቿ ሁላ ገላመጡኝ።

ልክ ከዛ ቤት ለቅቄ እንደወጣሁ ስልኬን ከኪሴ አወጣሁት መጀመሪያ የተደወለልኝ ስልክ 15 ሚስኮል ተደርጓል።
እማዬም ከአስር ጊዜ በላይ ደውላለች ልቤ መምታት ጀመረ እየተንቀጠቀጥኩ መልሼ ደወልኩ አይነሳም የማላቀው ስልክ ላይም ደጋግሜ ደወልኩ አይነሳም እንዴት ብዬ መኪና ውስጥ እንደገባሁ አላቅም ግን ወደሰፈር መሄድ ጀመርኩ መኪና ውስጥ ከገባሁባት ሰአት አንስቶ ያለማቋረጥ እየደወልኩ ነበር ከየትኛውም ስልክ ግን ምላሽ አላገኘሁም  መኪና ውስጥ የተቀመጥኩበት ወንበር በረዶ ሰራብኝ።
መኪናው እየተነዳ ያለ አልመስልህ አለኝ ሹፌሩን ተቀብዬ ባበረኩት ብዬ ተመኘሁ።

ሰፈር እንደረስኩ እየተሯሯጥኩ ነው ወደውስጥ የገባሁት ልክ ከሩቅ ቤታችን ሳይ ግርግር የሚሉ ሰዎችን ስመለከት አንዳች የተስፋ መቁረጥ ስሜት ተሰማኝ በደመነፍስ ደረስኩ ግቢው በለቅሶ እየተደበላለቀ ነው በር ላይ የቆሙት ሰዎች አልታይ አሉኝ።

እንዴት አልፊያቸው እንደገባሁ አላቅም ብቻ ስደርስ እናቴ ሞታ ነበር።

ለመሳቅና እናቴንም ቀልዱን ትታ እንድትስቅልኝ አውቃ እንደሆነ እያተናገርኩ ለመቀስቀስ ሞከርኩ እናቴ የምሯን ነው የሞተችው።
ያቺ ውጭ ምግብ ከበላሁ የተጎዳሁ ሚመስላት እናቴ
ያቺ ማታ ትንሽ ሲመሽብኝ ከግቢ ውጭ እየተጎራደደች ተጨንቃ መንገድ መንገዱን እያየች ምትጠብቀኝ ደርባባዋ ሴት ያቺ ዘመድ ያልወለድሽውን ልጅ ለማሳደግ ምን አሰቃየሽ አንቺስ እንደናቱ አትጥይውም ብለው ሲናገሯት እኔን የጎዱባት መስሏት ከሙሉ ዘመዶቿ የተቆራረጠችው እናቴ ያቺ ሳትበላ ሳትለብስ ሙሉ ህይወቷን ክርትት ስትል የኖረችልኝ እናቴ ሞታለች።

በሰአቱ የሰው ልጅ በህይወት ኖሮ እንደሚሞት ተረድቻለሁ እኔ ቆሚያለሁም ሞቻለሁም ።
የእናቴን አስክሬን ለማስለቀቅ ሲሞክሩ አቅፊያት ከሷጋ መሆን እንደምፈልግና ከአጠገቤ እንዳይወስዷት ከሁሉምጋ መጣላት ጀመርኩ።
የእናቴን ፊት ገልጬ ተመለከትኩት አሳዘነችኝ ፊቷ እንደከፋው ነው
እንባዬ ደረቀ ከፊት ለፊቴ ልእልት ቆማ ስትንሰቀሰቅ አየኋት እንደእብድ እየጎተትኩ መኝታ ቤት አስገባኋትና እናቴ ምን እንደሆነች ጠየኳት።

ለማውራት እየተናነቃት እቴቴ ከታመመች ቆይታለች በየተኛውም ሰአት እንዳትጨነቂ ንዴትና ጭንቀት የሞትሽን ቀን ያፋጥኑታል ተብላ በሀኪም ተነግሯት ነበር ቀን ከተፈጠረው ነገር ቡሀላ እቴቴ ደና አልነበረችም የሆነ ሰአት በጣም ሲብስባት ለመረጋጋት ያንተን ድምፅ መስማት ፈልጋ ደጋግሜ ስደውል አታነሳም እሷም እየደወለችልህ አታነሳም በዛ ሰአት ልጄ በንዴት የሆነ ነገር ሆኖብኝ ነው ብላ እንደ እብድ አደረጋት ተነስታ ከቤት ለመውጣ ስትሞክር ወደቀች ግን ደግማ አልተነሳችም አለችኝ።

በቃ የዚህ ሁሉ መንስኤ ፋኖስ ናት እሷ ናት የናቴ ገዳይ እያወራሁ ተቻኩዬ ኪችን ገባሁ ስለት ያለውን ቢላ አንስቼ ከጀርባዬ ሱሪየ ውስጥ ከተትኩት የኔ እናት ሞታ እሷ በህይወት አትኖርም እገላታለሁ ....


      🔸🔸🔺🔺🔹🔸

      
❤️ የፍቅር ጥግ ❤️


ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ  ታሪክ
❤️

ፀሀፊ
✍️ ማኔ

                        ክፍል  
7️⃣

ከፊት ለፊቷ ሄጄ ቁጭ ስል እልህ ውስጤን ተናንቆኝ ሰውነቴ መንቀጥቀጥ ጀመረ።

ምንም ሌላ ነገር ልልሽ አደለም ግን ምክንያትሽን ብቻ ንገሪኝ አልኳት።

የፌዝ ሳቅ ፈገግ አለችና ታስታውሳለህ ከአመት በፊት የሆነች ቀይ እንቡጥ ለማየት ምታሳሳ ፀጉሯ በጀርባዋ የተነሰነሰ አደለም ለመምታት ለማየት ምታሳሳ ያያት ወንድ ሁሉ የሚመኛት አንዴ በሳቀች ብሎ ሰው ሁሉ የሚጠብቃት ልጅ እእ ለኛ ቤተሰብ ደሞ የመሳቃችን ምክንያት እሷ ነበረች።
እናትና አባቴ ለመፋታት ጫፍ ደርሰው እሷ በመረገዟ ምክንያት ትዳራቸው ስለቆየ ስጦታ ብለው ስም አወጡላት በቃ ለቤታችን ስጦታ ናት እሷ ከተወለደች ጀምሮ ቤታችን በረከት በበረከት ሆኖ ነበር።
ያ ለመፍረስ ጫፍ የደረሰው ትዳር እንዳዲስ የሰው ምሳሌ የሚያስቀና ትዳር ሆኖ ነበር።

ሁሉም ነገር ግን ነበር ለምን አትለኝም ባንተ ምክንያት ነው ለችኝ የሚፈሰውን እንባዋን ካይኗ ላይ እየጠረገች።

እንዴት??? ነገሮች ይበልጥ ተወሳስበውብኝ በአግራሞት እየተመለከትኳት ነበር።

ጥሩ እንዴት ማለት አሪፍ ነው ምን መሰለህ እህቴ ምትማረው ከእናት መስሪያ ቤት አስፋልት ተሻግሮ ያለው የሀብታም ትምህርት ቤት ነው ።
እና እሷ ወደትምህርት ቤት ባባቴ መኪና እየሄደች አንተ ከtaxi ወርደህ ወደስራ ቦታህ እየሄድክ ታይሀለች ምንህን እንደወደደችው ባላቅም ብቻ ባንድ እይታ ፍቅር ያዛት አባቴ ትምህርት ቤት በር ላይ አድርሷት ሲመለስ እሷ ተደብቃ አስፋልት ተሻግራ ቆማ አንተ ስራ ቦታህ እስክትመጣ ቆማ ትጠብቅሀለች አንተ ወደስራ ቦታ ለመግባት ስለምታረፍድ አንተን  ጥበቃ እየቆየች እሷም ክላስ አርፍዳ ትገባለች ተደጋጋሚ ጊዜ በማርፈዷ ምክንያት ለአባቴ ተደውሎ ለምን እንደምታረፍድ ጥያቄ ቀረበበት አባቴ ደሞ ሁሌ በጊዜ ነው ክላስ አድርሷት የሚመመለሰው በዛ ምክንያት ግራ ስለገባው እህቴን አብዝቶ ተቆጣት ድጋሜ በማርፈድ ቅሬታ ከቀረበባት እዚሁ ለቤታችን ቅርብ የሆነ ሌላ ትምህርት ቤት እንደሚያስገባት ሲነግራት ሁለታችንም ደነገጥን ምክንያቱም እኔ ስላንተ ሁሉንም ነገር ጠንቅቄ ስለማቅ ነው።  ለህቴ ከኔ በላይ ቅርብ ሰው የላትም ምንም ነገር ሳደብቅ ትነግረኛለች ስምህን እንኳን ሳታቀው ስላንተ ስታወራ አይኗ ይበራ ነበር አንዴ በሳቀች ብለን ምጠብቃት ልጅ ስላንተ ስታወራ ግን ፊቷ እንደፀሀይ እያበራ ሳቅ በሳቅ ሆና ነበር ምታወራኝ።

በመጨረሻም ሁሉንም እውነት ላንተ ነግራህ ሰአት አመቻችታችሁ እንድትገናኙ እሷም ክላስ ሳታረፍድ ወይ ስትወጣ እንድታይህ ካልሆነም ማታ ላይ ከስራ ሰአትህ ቡሀላ እየመጣን ልናገኝህ ወሰንና ለእህቴ ሁሉንም እውነት አፍረጥርጣ እንድትነግርህ ሌሊቱን ሙሉ ስመክራት አደርኩ እሷም ተስማማች ።
በነጋታው ስልኳን ይዛ ወደትምህርት ቤት መጣች ያንተን ስልክ ተቀብላ በዛውም ለኔ ምን እንዳልካት ደውላ ለመናገር ስለፈለገች ነበር ስልክ የያዘችው።

አይገርምም አንተ ጢባራሙ እእ አንተ ብቻ ወንድ የተፈጠርክ የሚመስልህ አንተ ግን እንደምትወድህ ስትነግርህ በጥፊ ብለህ ሸኘሀት።
እህቴ በሰአቱ እያለቀሰች እጅህን እንዳነሳህባትና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተመታች በዛም ምን ያህል እንደከፋት እያዞራት እንደሆነና ትምህርት ቤት መጥቼ እንድወስዳት እየነገረችኝ ነበር ንግግሯን እንኳን ሳትጨርስ እህቴ የመኪና ሰለባ የሆነችው የቤታችንን ድመቀት ነው የቀማኸን ሳቃችንን ነው ያሳጣኸን የናትና አባቴን ትዳር ነው የበተንከው ገባህ ባይኔ ሙሉ ስላየኋት ምትሟሟብኝ የሚመስለኝን እህቴን በመኪና አደጋ እንዳጣት ያደረከኝ ታስታውሳለህ አደል አስክሬኗ እንኳን ከመሬት ተለቅሞ ነው የተቀበረችው የሚሰቀጥጥ የመኪና አደጋ ነው የደረሰባት እሷን ካጣሁ ቡሀላ ከልቤ ስቄ አላቅም ከእናትና አባቴ ቤት ወጥቼ ነው ምኖረው እናቴ ጤነኛ አደለችም ባንዴ ልጇንም ትዳሯንም ነው ያጣችው አባቴ ከስንት አንዴ ነው ስልክ እንኳን ሚያነሳልን የት እንዳለ የት እንደሚኖር አናቅም።

አንተ ካደረከን ነገር አንፃር እኔ ምንም አላደረኩህም ሰው ፊት ብቻ ነው ያዋረድኩህ ማፍቀር እንዴት እንደሆነ ስቃዩ እንድትረዳ ስለምፈልግ ነው እስካሁንም የታገስኩህ እንጂ እንደኔማ ቢሆን ገና የመጀመሪያ የተገናኘን ቀን መጥህ ውስጥ መርዝ አድርጌ ብገልህ ምኞቴ ነበር ስታቅፈኝ እንዳባ ጨጓሬ ነው ምትኮሰኩሰኝ ሳይህ ፊቴ ላይ ቀድሞ ሚመጣው ነፍሰገዳይነትህ ነው ምን ያህል ትግስተኛ እንደሆንኩ የገባኝ አንድ አመት ሙሉ አንተን መታገሴን ሳስበው ነው።
እህቴ ምን ጥሎባት አንተን እንደወደደችህ አላቅም አንተን እንኳን ማፍቀር ለትንሽ ቀን አብሮ ጊዜ ማሳለፍ እራሱ ይከብዳል ምትቀፍ ሰው ነህ ምንህም አይስብም።

ይታይሀል ከነሱጋ የተቀመጠው ሰው ፍቅረኛዬ ነው የአራት አመት ፍቅረኛዬ አሁን አብረን ነው ምንኖረው በከፋኝ ሰአት ከጎኔ የነበረው እሱ ነው አለችኝ።

አንዳንዴ የምንሰማውን ነገር ማመን አቅቶን ፈጣሪን በቃ ከህልሜ ቀስቅሰኝ እንጂ እስካሁንኮ አልነቃንም ብለነው አናቅም እኔ በሰአቱ እንደዛ ነው ያልኩት።

ፋኖስ ይሄን ሁላ ነገር ስትነግረኝ እያለቀሰች ስለነበር አሳዘነችኝ ውስጤ ተላወሰ እራሴን ጠላሁት በእህቷ ፈንታ እኔ በነበርኩ ብዬ ተመኘሁ።


ምንም ነገር ሳልነግራት ዝም ብዬ ተነስቼ መውጣት ፈልጌ ነበር ግን ለማንም አውርቼ ማላቀውን ሚስጥሬን ለመንገር ወሰንኩ ምናልባት ትንሽ ልቧ ላይ ያለውን ጥላቻ ማብረድ ከቻልኩ ብዬ አስቤ ስለነበር ነው ንግግሬን ሳልጀምር ማላቀው ስልክ ተደወለልኝ አላነሳሁትም ስልኬን ሳይለንት አድርጌ ኪሴ ከተትኩትና ለፋኖስ ከልጅነቴ ጀምሮ የተፈጠረውን መተረክ ጀመርኩ።

እኔ የተወለድኩት እዚሁ ነው።
እኔ ስወለድ እናቴ መውለድ ሳትፈልግ በድንገት ነው የተረገዝኩት ለማስወረድ ብዙ ብትሞክርም ፈጣሪ ስላልፈቀደው ሳይሳካላት ቀረ  አባቴ የልጅ ፍቅሩ በጣም ከፍ ያለ ስለነበር በእናቴ ማርገዝ ደስታው ጣራ ነክቶ ነበር።
እሷ ስትወልድ እንዳትሳቀቅ ብሎ ሰፊ ቤት ተከራየላት እሷ ሌሊት ወጥቶ ማታ እየገባ እሷን አንድም ስራ እንድትሰራ አይፈቅድላትም ሰራተኛ ቀጠረላት ከመሬት እቃ ስታነሳ ሁላ ሚከፋው አባት ነበረኝ።


ይቀጥላል...

🟫ፀሀፊ ✍️ ማኔ

🔻ክፍል  8️⃣ ነገ ማታ2️⃣🟰3️⃣0️⃣  ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like💝 ማድረግ አይርሱ።
🔺🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!
😀
 
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔  @MELKAM_LBOCH13 💔

➖የዩቲዩ ገፃችን➖
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333
https://www.youtube.com/@Kezerareaction33

4.8k 0 29 8 297

በቤተ ዘመድ ፊት ቃል ቢገባልሽም
እሱም ቤት አልገባም አንቺም ቤት የለሽም የባልሽ ንግግር ቅኔው ተበተነ
እሰራላታለሁ ያለሽ እውነት ሆነ

5k 0 6 11 66

ነፍሴን

ነፍሴን ከቀበርሻት ከመቃብር ስፍራ ይደማል አካሌ የአንቺ ስም ሲጠራ ትዝታሽ ሲነሳ ከተንቀላፋበት ይነቃል ህመሜ የትም ባደረበት


      🔸🔸🔺🔺🔹🔸

      
❤️ የፍቅር ጥግ ❤️


ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ  ታሪክ
❤️

ፀሀፊ
✍️ ማኔ

                        ክፍል  
6️⃣


በነጋታው ልክ ከፋኖስጋ እንደተገናኘን የጓደኛዋን ስልክ ሰበብ ፈልጌ ወሰድኩባትና ጓደኛዋን ማውራት ጀመርኩ።
ልደቷ በሚቀጥለው ወር ላይ እንደሆነ ነገረችኝ አጋጣሚ ሆኖ ሚውለው እሁድ ቀን ነበር በደስታ ብዛት ላብድ ምንም አልቀረኝም።
ቀጣዮቹን ጊዜዎች እንዴት ወጥሬ ሰርቼ
ለሷ ፕሮግራሙን እንደማዘጋጅላት እያሰብኩ መተኛት መነሳቱን ተያያዝኩት።
ወሩ ሁላ ረዘመብኝ ፋኖስ ሁሌ ምትሄድበት ቤት ስላለ እዛ ይዛኝ ሄዳ ቁጭ ብለን እያወራን የልደቷን ቀን እንዴት ማሳለፍ እንደምትፈልግ ጠየኳት።
ልደት የማክበር ልምድ ስለሌለኝ ተኝቼ ነው ምውለው ስትለኝ ይበልጥ ደስ አለኝ ካላሰበችበት እንደውም ለኔ ጥሩ ሰርፕራይዝ  ይሆንልኛል ብዬ ተደሳሰትኩ።
ለሷ ፕሮግራሙን እንደማዘጋጅላት እያሰብኩ መተኛት መነሳቱን ተያያዝኩት።
ወሩ ሁላ ረዘመብኝ ፋኖስ ሁሌ ምትሄድበት ቤት ስላለ እዛ ይዛኝ ሄዳ ቁጭ ብለን እያወራን የልደቷን ቀን እንዴት ማሳለፍ እንደምትፈልግ ጠየኳት።
ልደት የማክበር ልምድ ስለሌለኝ ተኝቼ ነው ምውለው ስትለኝ ይበልጥ ደስ አለኝ ካላሰበችበት እንደውም ለኔ ጥሩ ሰርፕራይዝ  ይሆንልኛል ብዬ ተደሳሰትኩ።

ለእናቴና ለጓደኞቼ ነገርኳቸው ሁሉም ያንን ቀን በጉጉት እንደሚጠብቁ ነገሩኝ።
የሷንም ጓደኞች የዛን ቀን ሰርፕራይዝ እንደምናረጋት ነገርኳቸው ሁሉም ደስተኞች ነበሩ።
እናቴ ቤት እናዘጋጅላት ፈጣሪ ይመስገን ቤታችን ቆንጆ ነው አያሳፍርም አደል እንዴ አለችኝ።
በደስታ ተስማምቼ ፕሮግራሙን ቤት ለማድረግ ወሰንና ቀኑ ሲደርስ ቤት ዝግጅቱን ጀመርን።
እኔ ቀኑ እስከሚደርስበት አምስት ቀናት ውስጥ እንቅልፍ አልወሰደኝም ሁሉም ነገር ብርቅ ሆነብኝ አንዳንዴ ሌሊት ላይ እየተነሳሁ እንዴት እንደምንበረከክ ሁላ እየተለማመድኩ ብቻዬን እስቃለሁ።

የፕሮግራሙ ቀን 8 ሰአት ላይ ቤት እንድትመጣ ነገርኳት ልእልት ከዋዜማው ጀምሮ ከኔ በላይ ከእናቴጋ እየተጋገዘች ሁሉንም ነገር ስትሰራራ ነበር።

የፋኖስ ጓደኞች ከሷ ቀደም ብለው መጡ የኔም የስራ ባልደረቦች ተገኙ።
እኔ የሆነ ጭንቀት ውስጤን ተናነቀኝ።
ዝም ብዬ መቅበዝበዜን ያየችው እናቴ እቅፍ አደረገችኝና ልጄ እራስህን እያየኸው ነው አደል እንደልጅ እየተቅበዘበዝክኮ ነው አለችኝ። ፈገግ ብቻ ብዬ ዝም አልኳት።

ሰአቱ ደረሰ ፋኖስ ደውላ እየመጣች እንደሆነ ነገረችኝ።
መጣች። መጀመሪያ ዝምብለን ልደቷን ሰርፕራይዝ ያደረግናት እንዲመስላት ስትገባ ቀለል አድርገን ሰርፕራይዝ አልናት በፍፁም እንዳልጠበቀችና ደስ እንዳላት ሆና አለቀሰች። አቅፌ አባበልኳት።
ለልደቷ የተዘጋጀውን ኬክ ከመቁረሷ በፊት እኔ የጋብቻ ጥያቄዬን ማቅረብ ስለነበረብኝ ሁሉም በአይናቸው አሁን አሁን ጠይቃት የሚል ምልክት ሲሰጡኝ
ሳታስበው ከኋላዋ ተንበርክኬ በፍርሀት ውስጥ እንዳለሁ ታገቢኛለሽ ብዬ ጠየኳት።

በውስጤ የልጅነት ህልሟን የሁልጊዜ ፍላጎቷን ስላሳካሁላት ምን ያህል እድለኛ ወንድ እንደሆንኩ እያሰብኩ ነበር።

እሷ ግን ልክ ከፊት ለፊቷ ተንበርክኬ ጥያቄውን ሳቀርብላት ቃል ካፏ ሳይወጣ ወደጓደኞቿ ዞረችና ከት ብላ ሳቀች ጓደኞቿም አላስቻላቸውም አብረዋት ሳቁ..........

ግራ ገባኝ ምን እየተካሄደ እንዳለ እኔ ከተንበረከኩበት ሳልነሳ የሁሉንም አይን በየተራ እያየሁ ምንድነው ፋኖስ ታገቢኛለሽ ብዬ እየጠየኩሽ ነውኮ አልኳት።
እሱኮ ነው ያሳቀኝ አየህ አደረኩት ፊት ለፊቴ አንበረከኩህ ይቺን ቀን ለማየት አመት ከምናምን መጠበቄ እራሱ ቆጭቶኛል ግን አደረጉት አንበረከኩህ ብላ በእልህ እየተናገረች እንባዋ ካይኗ ጠብ ጠብ አለ።
ጓደኞቿ እኔን በግልምጫ እያነሱ እየጣሉ እሷን አየሽ አንቺ አውርተሽ አልተውሽውም አሳካሽውኮ ጀግና ነሽ በቃ ለምን ታለቅሻለሽ እያሉ ይዘዋት ወጡ እኔ ነገሩ ህልም እየመሰለኝ ዝም ብዬ እናቴን አይን አይኗን እያየሁ ቆምኩኝ።
ወዲያው ተመልሳ መጣችና ለሌላ ጊዜህ ግን ሰዎች ላይ አትበጣጠስ ምድር ላይ ያለሁት ወንድ እኔ ብቻ ነኝ አትበል እሺ የምድራችን ባዶው ወንድ አንተ ነህ ብላ ተመልሳ ወጣች እኔ እየሮጥኩ ተከተልኳትና ምን እያወራች እንዳለች ጠየኳት ላንተ ማብራራት የለብኝም ምክንያቱም አንተ ለኔ ምንም ነህ ብላ ጥላኝ ወጣች የሚተናነቀኝን እንባ ዋጥ አድርጌ ወደቤት ተመልሼ ገባሁ ።

እናቴ መሬት ላይ ወድቃ ከበዋት እንድትረጋጋ እየነገሯት ነበር እሷ ዝም ብላ ታቃስታለች  እየሮጥኩ ሄጄ እማዬ እማዬ እያልኩ ከወደቀችበት ለማንሳት ስሞክር ልጄ በሰው ፊት አዋረደችህ አደል እኔ ባይኔ ሙሉ ለማየት የምሳሳልህን ልጄን ሰው ፊት አንበርክካ ጥላህ ሄደች ምን አርገሀት ነው ልጄ አንተ ለሰው ክፉ አታስብ ምን ሴጣን አሳስቶህ ምን ጥፋት ሰርተህ ነው አለችኝ እያለቀሰች የእናቴን ንግግር ስሰማ እኔ ሳግ እየተናነቀኝ አብሪያት ማልቀስ ጀመርኩ።  
አንስተን ወደመኝታ ቤት ወስደን አስተኛናት ዶክተር ልጥራ ወይ ሀኪም ቤት ልውሰድሽ ስላትም አሻፈረኝ ስትል ምንም ማድረግ አልቻልኩም።
ጓደኞቼ ምንም አታረጉም ሂዱ በቃ ብያቸው መቆየት ቢፈልጉም አስኬድኳቸው።

እኔ ከእናቴ አጠገብ ቁጭ ብዬ አስሬ ትንፋሿን ቼክ እያደረኩ.....አይን አይኗን መመልከቱን ተያያዝኩት።
ልእልት መጥታ ካጠገቤ ቆማ መሬት መሬት እያየች ፋኖስን ሄደህ ምን እንደተፈጠረ ማውራት ከፈለክ እኔ ከእቴቴ አጠገብ እሆናለሁ እኔ አለሁ ለሷ አለችኝ።

አመሰግናለሁ ግን ጥያት አሌድም ከምንም ነገር በላይ እናቴ ናት ለኔ አስፈላጊዋ አልኳት።
እናቴ ፈገግ ብላ አየችኝና በቃ አሁን ደና ሆኛለሁ ሂድ አናግራትና ና እኔም ልቤ እርፍ ይበልልኝ እኔኮ አሞኝ ስለቆየሁ ድንጋጤ ንዴት ጭንቀት ሲያጋጥመኝ ስለሚጥለኝ ነው እንጂ ደና ነኝ ሂድ እስቲ መቼስ በጤናዋ እንዲህ አላደረገችም ምክንያቷን ጠይቃት ለወደፊት መማሪያ ይሆንሀል ሂድ አለችኝ።

እዛ ተቀምጬ የባሰ ጭንቀት ልሆንባት ስላልፈለኩ ተነስቼ ወጣሁ ልእልት እስከበር እየተከተለች እንዳትቆይ እሺ አደራ እቴቴ ደና አትመስለኝም አደራ አደራ አለችኝ።
ዞሬ እንኳን ላያት ስላልፈለኩ በእጄ ወደዛ ሂጂ የሚል ምልክት ሰጥቻት ግቢውን ለቅቄ ወጣሁ።
ፋኖስጋ ተደጋጋሚ ጊዜ ደወልኩ አታነሳም በመልእክት አንዴ እንኳን እንድታናግረኝ ለመንኳት ጭራሽ አትመልስም ሲጨንቀኝ ጓደኛዋጋ ደወልኩና ቢያንስ ምክንያቷን ብቻ ትንገረኝ ለሌላ ጊዜም ትምህርት ይሆነኛል በናትሽ ብዬ ተማፀንኳት ና በቃ የተለመደው ቤት ነን አለችኝ።

እንደ እብድ እያደረገኝ የነገረችኝ ቦታ ሄድኩኝ ስደርስ ሁሉም ተሰብስበው ቆዝመው ተቀምጠዋል።

ሁሉም እኔን ሲያዩ ተነስተው ብቻዋን ትተዋት ቦታ ቀይረው ተቀመጡ የሆነ ወንድ አብሯቸው አለ።

ከፊት ለፊቷ ሄጄ ቁጭ ስል እልህ ውስጤን ተናንቆኝ ሰውነቴ መንቀጥቀጥ ጀመረ።


🟫ፀሀፊ ✍️ ማኔ

🔻ክፍል 7️⃣ ነገ ማታ2️⃣🟰3️⃣0️⃣  ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like💝 ማድረግ አይርሱ።
🔺🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!
😀
 
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔  @MELKAM_LBOCH13 💔

➖የዩቲዩ ገፃችን➖
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333
https://www.youtube.com/@Kezerareaction33

5.8k 0 30 15 323

🎉ሰላም ቤተሰብ ከነገ ጀምሮ እኔ ስለሆንኩኝ ሀሳብ አይግባችሁ ያለ ማቋረጥ ወደናንተ የማደርስ ይሆናል ለስካሁኑ ስህተት ይቅርታ እንጠይቃለን ከወደዳችሁኝ
❤️


የፍቅር ጥግ

                        ክፍል 5
 

ጥሩ በቃ ተጫወቱ እማዬ እኔ ልተኛ ነው ብያት ብድግ አልኩ እናቴ ግን እጄን ያዘችና አስቀመጠችኝ።
ምነው እማ ፈለግሽኝ አልኳት።

አዎ አንድ ነገር ልነግርህ ነው ባንተ ፊት ቃል ላስገባት ነው አለችኝ።
ማንን???
እስካሁን ስሟን እንኳን አታቀውም አደል ልእልት ትባላለች ።
ልጄ እኔ አንድ ቃል የማስገባችሁ ነገር ቢኖር እኔ የሆነ ነገር ብሆን አይበለውና ብሞት እሷን ጓደኛ ጎረቤት እናት አድርገህ ትከሻዋን ተደገፋት አንቺም ልእልቴ በምትወጃት እናትሽ ይዤሻለሁ ልጄን ተቆጣኝ ገላመጠኝ ብለሽ ፊቲሽን እንዳታዞሪበት ምንም ሁኔታ ውስጥ ቢሆን አደራዬን ላንቺ ነው የሰጠሁት በምድር የሰጠሁሽን ቃል በሰማይ እቀበልሻለሁ ይሄንን ቃሌን እንዳትረሱ አለች።
እናቴ ተናግራ እስክትጨርስ እኔ ቀድሞ እንባዬ ፈሶ አለቀ።
በጣም ስለተናደድኩ ተነስቼ ተቻት ወጣሁና አልጋዬ ላይ ተዘረርኩ አላስችልህ ሲለኝ ደሞ ተመልሼ ሄድኩና እማዬ ሁለተኛ ይሄ እኔ ብሞት ወይ የሆነ ነገር ብሆን የምትይውን ነገር ደግመሽ ከተናገርሽው እንጣላለን ሁለተኛ እንደዚህ ስትይ ከሰማሁሽ ደግመሽ ፊትን አታይውም ቆይ እኔ ተጨንቄ እንድሞት ነው እንዴ ምትፈልጊው ደሞስ ቆይ ካልጠፋ ሰው ለዚች ዘገምት ነው አደራ ምትሰጭኝ እእ እኔኮ ፍቅረኛ አለኝ በቅርቡ ሚስቴ ላደርጋት ነው ታዲያ ይቺ ምን ቤት ናት ደሞ እሷን ብሎ ልእልት በስርአት ማውራት እራሱ አትችልምኮ ብያት ተመልሼ ወጣሁና ሳሎን ቁጭ ብዬ ቴሌቪዥን መመልከት ጀመርኩ።
ትንሽ ቆየት ብለው እናቴና ልጅቷ ተያይዘው መጡ እናቴ ተነስና ትምህርት ቤት አድርሰሀት ና አንተጋ መኪና እያለ ለምን taxi ትጠብቃለች አለችኝ።

ውስጤ ቅጥል እያለ ቢሆንም እሺ ብያት ቁልፈን አንስቼ  ወጣሁ ።
ልጅቷ ቅርፍፍ እያለች መጣችና ጋቢና ገብታ ቁጭ አለች።

ልክ ከግቢ እንደወጣን ውረጂና በእግርሽ ሂጂ ልላት ፈልጌ ነበር ግን እናቴ ስትሰማ ምን እንደሚሰማት አሰብኩና እዛው ትምህርት ቤቷ አደረስኳት።

ስትወርድ ፊቴን እንኳን አላየችውም ቻው ወይም አመሰግናለሁ እንኳን አላለችኝም።
ይባስ እየተናደድኩ ወደቤት ለመመለስ መኪናውን እያዞርኩ እናቴ ደወለችና አንድ ክላስ ብቻ ነው ያላት ቢበዛ 45 ደቂቃ ነው በዛው ይዘሀት ና አለችኝ ።
እየማልኩ አላረገውም እማዬ አልኳት።
እሷ ግን ግግም አለች ልጄ ትራንስፖርት የያዘችውን ብር ቅድም ለኔ ቡና ገዛዝታበት መጣች እሰጥሻለሁ ብያት እረስቼውኮ ነው አለችኝ።

እየሳኩ አይ እማ ቤቱን የሞላው ቡና አደል እንዴ ያ ሁሉ ቡና እያለ ለምንድነው ምትገዛልሽ ብዬ መለስኩላት።

አደለምኮ ልጄ የሌለኝ መስሏት ነው እንጂ እኔ አጥቼ አደለምኮ አሁን 45 ደቂቃ መጠበቅ ከብዶህ ነው ይሁን በቃ አንተ እንደፈለክ አላስቸግረህ ተወው አለችኝ።

እንደከፋት ስለገባኝ እሺ በቃ እማዬ በሰው መኪና እኔ ምን እንቢ አስባለኝ በቃ ይዣት እመጣለሁ ቻው ብያት ስልኩና ዘጋሁትና ተመልሼ ያወረድኳት ቦታ ላይ ቆምኩኝ።

ፋኖስጋ ደውዬ ማውራት ጀመርን እንደለመድነው ምን እንዳወራን እንኳን በቅጡ ሳላውቅ 1ሰአት ከሀያ አውርተናል እኔ 10 ደቂቃ እራሱ ያወራኋት አልመሰለኝም ነበር።
ልክ ልጅቷ መጥታ መኪናዬ ፊት ለፊት ስትቆም ነው ያወራነውን ሁላ የተመለከትኩት።

ፋኖስን ተሰናብቻት ስልኩና ዘጋሁትና ከፍቼ አስገባኋት ።
እየተመለስን ምነው 45 ደቂቃ ነው ምትቆየው ብላኝ ነበርኮ እማ አንቺ ስንት ሰአት እንደቆየሽ ታውቆሻል አልኳት።

ዝም አለችኝ።
ንቀቷ ከምንም በላይ አናደደኝና ጥጌን ይዤ ቆሜ ውረጂ ከመኪናው ጭራሽ እኔን ማውራት እየደበረሽ ነው አብረሽኝ ምቴጂው አልኳት።

እንዳጎነበሰች ይቅርታ አለችኝ።
በፈጣሪ ስም ስንት አይነት አድርቅ ሰው አለ የሷ ግን ይለያል ።
ቤት ስንደርስ ከመቼው ከመኪናው ወረዳ እናቴጋ ሄዳ መሳሳቅ እንደጀመሩ አላውቅም ብቻ ግን መኪናውን እንኳን በስርአት እስካቆም የጠበቀችኝ አይመስለኝም ።

እኔም ችግሯ በትክክል ከኔጋ እንደሆነ ስለገባኝ ትቻቸው ገብቼ ለጥ አልኩኝ ።
ተኝቼ ሳስበው የነበረው ለፋኖስ ቀለበት ማስርላት መቼ ነው እንዴት አድርጌ ግሮግራሙን ላዘጋጀው ሚለውን እያሰብኩ ነበር እንቅልፍ የወሰደኝ።


ይቀጥላል...

5.3k 0 31 11 222

የፍቅር ጥግ

ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ  ታሪክ


             ክፍል  4
 

በደስታ ተስማማች እንደ እብድ አደረጋት አለምን የገዛች ያህል እንደተሰማት ነገረችኝ።
እኔም ወስጄ ከእናቴጋ አስተዋወኳት እናቴና እሷ እረጅም አመት እንደሚተዋወቅ ሰው በአንዴ ተግባቡ እኔም ያንን ደስታቸውን ሳይ በጣም ደስ ብሎኝ በፈገግታ እየተመለከትኳቸው ነበር።
ፋኖስ ልክ ፈጣሪ የጨለመው ህይወቴን አይቶ ብርሀን ትሆነኝ ዘንድ እሷን ስለላከልኝ አመሰገንኩት የመጀመሪያዬ ስለሆነ ይሁን ወይ የኔ የተለየ ፍቅር ሆኖ አላቅም ግን አብረን ውለን ባንለያይ ደስታዬ ነው ሳገኛት አይኔን ካይኗ ላይ ለደቂቃ መንቀል አልፈልግም አስቸኳይ ስራ ኖሮኝ እሷ ከደወለችልኝ ትቼ ወደሷጋ ነው ምሄደው በየቀኑ ማለት በሚያስችል ሁኔታ ከሷ የሆነ ስጦታ ይሰጠኛል።

ፍቅር እብድም ጅልም ነው ሞኝ ያደርገናል ምንም ነገር እንዳይታየን እውር የሚያደርገንም ነገር አለ።
እኔ ከስራ ቀርቼ እሷም ከስራ ቀርታ ቀኑን ሙሉ አብረን እንውላለን እንደዛም ሆኖ እኔ አልጠግባትም ቤት ገብቼ ሌሊቱን ሙሉ ለእናቴ ስለሷ እያወራሁላት ባድር ደስታዬ ነው።

ጠዋት ላይ ከእንቅልፌ ተነስቼ ወደስራ በመሄድ ፋንታ እሷ ወዳለችበት መሄድ ነው ምፈልገው።
አንድ ወንድ ከሴት ልጅ የሚመኘውን በሙሉ ሰታኛለች ህይወት ውስጥ በነበረኝ ደስታ ላይ እጥፍ ደስታን ጨምራልኛለች ብቻ ለምን አስከዛሬ ሳላፍቅር ቆየሁ ፍቅር እንደዚህ ደስ ይላል እንዴ ብዬ እስክገረም ድረስ ለኔ ልዩ ሴት ነበረች በፍቅሯ አብጃለሁ ለማለት ስድስት ወር ብቻ ነበር የበቃኝ በነዛ ወራት ውስጥ እኔ ስወለድ አብራኝ ተወልዳ አብራኝ አድጋ ሁሌም ከጎኔ የነበረች ሴት እንደሆነች ያህል ነበር  የተሰማኝ ።

ገና ስንገናኝ ፊቷን አይቼ ስሜቷን አቀዋለሁ እሷም እንደዛው ሰው ፊት ሳናወራ ተያይተን ብቻ እንግባባለን።

ልክ ከእናቴጋ ስሆን የሚሰማኝን ነፃነት እሷጋም አገኘዋለሁ ብር ቢኖረኝ ባይኖረኝ ግዴላትም የኛ ዋናው ነገር መተያየታችን ብቻ ነው ።

ብቻ እናቴ በኔ ፀባይ እስክትገረም ድረስ  በወጣሁ በገባሁ ቁጥር አፈዘዘችህ አደል እያለች መቀመጫ እስክታሳጣኝ ከልቤ አፈቀርኳት።

ፋኖስ ሁሌ ምትነግረኝ አንድ ነገር ከለ ጓደኞቼ በተሰበሰቡበት ያንተም ጓደኞች ተሰብስብው ተንበርክከህ ታገቢኛለሽ ብለህ ስጠይቀኝ ያለውን ደስታ ሳስበው በቃ እኔጃ ያንን ቀን አይቼ ብሞትም አይቆጨኝም ለኔ ምድር ላይ ሚያጓጓኝ ያ ቀን ብቻ ነው ትለኛለች ይሄ ንግግሯ በተገናኘን ቁጥር ካፏ ጠፍቶ አያቅም እኔም እንደምንም ብዬ ለሷ ቀለበት ለማሰር መሯሯጥ ጀመርኩ ።


ቀኑ እሮብ ነበር ፋኖስ አሞኛል አንገናኝም ስትለኝ በጣም ደብሮኝ ስለነበር የሚሰራውን የከስተመር መኪና ይዤ ወደቤት ሄድኩ ሰአቱ ሰባት ወይ ስምንት ቢሆን ነው።
ስደርስ እናቴ ከጎረቤታችን ልጅጋ የሞቀ ጨዋታ ይዘው ፍንድቅድቅ እያሉ ይሳሳቃሉ ።
እናቴ አልጋ ላይ ጋደም ብላለች።
ልጅቷ ደሞ ሙሉ እቃውን መኝታ ቤት አስገባብታ ቡናዋን እያፈላች  ከአልጋው ስር ካጠገቧ ቁጭ ብላለች ።

ልክ ስገባ እናቴ እርፍ ብላ እንደዛ እየተፍለቀለቀች ሳያት ደስ አለኝና ሄጄ ሳምኳት ሁሌም እንደዚህ ሳቂልኝ እሺ ብያት አጠገቧ ቁጭ አልኩ።

እናቴ ገልመጥ አድርጋኝ ሰላም በላት እንጂ አላየሀትም እንዴ አለችኝ።
የውሸት ፈገግ እያልኩ ውይ ይቅርታ አላየሁሽም ነበር ደናነሽ የጎረቤቴ ልጅ አልኳት።
አንገቷን ደፍታ ደና ነኝ አለችኝ።


ይቀጥላል...

✎ክፍል 5 ነገ ማታ 2:30 ይቀጥላል♥️    ቶሎ እንዲ🀄️ጥል LIKE♥️ እና Share አድርጉ።


  ይ🀄️ላ🀄️ሉን
https://t.me/+4dGFaH_mUnExZjg8
https://t.me/+4dGFaH_mUnExZjg8

💝የዩቲዩ ገፃችን💝
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333

6.4k 0 31 4 204

      🔸🔸🔺🔺🔹🔸

       ❤️ የፍቅር ጥግ ❤️

ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ  ታሪክ ❤️


                        ክፍል 3
 
እንዲሁ እየተወዛገብኩ ካሁን ካሁን ደወለች ወይ መልእክት ላከች ብዬ ስልኬን እያየሁ ቤት ደረስኩ።
ቤት ስገባ የጎረቤታችን ልጅ ከእማዬጋ ቁጭ ብለው ከት ብለው ይሳሳቃሉ እኔ ስገባ ግን ልጅቷ ሳቋም ጥፍት አለ ከተቀመጠችበት ብድግ አለችና በቃ ክላስ እረፈደብኝ እቴቴ ቻው ብላት ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ ወጣች ከመጀመሪያውም ተናድጄ ስለነበር ለእናቴ ቆይ ይቺ ዘገምተኛ ልጅ ግን ያማታል እንዴ ምንድነው እኔ ስገባ እያሮጠ ሚያስወጣት ልጠልዛት እንዴ አልኳት።

አይ እንግዲ ስርአት በሷ ቀልድ የለም ልጄ እንደው እስከዛሬ ብዙ ሰው አውቃለሁ ግን እንደሷ ንፁህ ልብ ያለው ምስኪን ልጅ አይቼ አላቅም ልቧ ከእንቁ የከበረ ነው ውስጧ እንደወተት ነጭ ነው ክፋት አይቶት አያቅም አደራህን እንደው ካፍህ ክፉ ቃል ወጥቶ እንዳታስቀይማት አደራ አለችኝ።

እሺ በቃ ልተኛ ነው ብዬ ልገባ ስል ና ቁጭ በል በምን ተናደህ ነው አለችኝ
ነገሩን ነግሪያት የባሰ ከሷጋ መጨቃጨቅ ስላልፈለኩ  አረ ደክሞኝ ነው እማ እረፍት ላድርግ በናትሽ እእ ትንሽ ብቻ ብያት ገብቼ ተኛሁ ወዲያው ስልኬ ላይ መልእክት ገባልኝ ።
ካሁን ቡሀላ አላስቸግርህም ቃሌ ነው ደህና ሁን ይላል።
አይቼው ዝም አልኩኝ።
ግን ነገሩ ከሶስት ቀን አላለፈም ነበር ደግማ መልእክት ላከች< እውነት ለመናገር ልረብሽህ ፈልጌ አልነበረም ግን ከዚህ በላይ ዝም ማለት አልቻልኩም ከፈለክ አውራኝ ከደበረህ ዝም በለኝ> ብላ ላከችልኝ።

እስከማታ ዝም ብያት ቆየሁና እኔ ዝም ብልሽ አንቺ ዝም ትይኛለሽ አልኳት።
አይ እኔ ዝም አልልህም እስከሞት ድረስ ላንተ እፋለማለሁ አለችኝ።
በቃ ያንን መልእክት ካየሁ ቡሀላ መሳቅ ማቆም አቃተኝ በትርፍ ሰአትሽ ኮሜዲ ትሰሪ ነበር እንዴ ብዬ መለስኩላት።

ከብዙ መዘጋጋት ከዛ መልሶ ማውራት ቦቻ ከብዙ ልመና ቡሀላ እኔም እየለመድኳት መጣሁ ።
ተቀጣጠርንና በድጋሜ ተገናኘን እንደተለመደው ውብ ሆና ነበር የመጣችው ቁጭ አድርጌ  ሁሉንም አወራኋት ከልጅነቴ ጀምሮ ፍቅረኛ ኖሮኝ እንደማያቅ እናቴ ኮራ ጀነን ያልኩ ወንድ እንድሆን አድርጋ እንዳሳደገችኝ በህይወቼ አንድም ቀን አፍቅሬ ወይም የፍቅር ስሜት ተሰምቶኝ እንደማያቅ ነገርኳት።

በቃ የልብህን ድንግልና ለኔ ስጠኝና ዘላለሜን እንደፋኖስ እያበራሁልህ አብረን እንኑር አለችኝ።
እንደዚህ ስተለኝ በድጋሜ ከት ብዬ ሳኩና ልብም ድንግልና አለው እንዴ አልኳት።

ቀላል አሁን ምላሽህን ንገረኝ አለች።
ባሁን ሰአት ምንም ልላት እንደማልችልና ግን እንደስከዛሬው እንደማልዘጋት እንደጓደኛ እንደምቀርባት ምናልባት ለሷ የፍቅር ስሜት እንዲሰማኝ ካደረገች አብሪያት እንደምሆንና ያንን ማድረግ ካልቻለች ግን እንደምንለያይ ነገርኳት።

በራሷ በጣም እርግጠኛ ነበረች አታስብ ማመን እስኪያቅትህ ድረስ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ነው ፍቅር የሚይዝህ አለችኝ።

ኮንፊደንሷ ደስ እንደሚል ነግሪያት አብረን ጊዜ አሳለፍን።

ከዛ ቀን ቡሃላ ጠዋት በእናቴ ፈንታ ከእንቅልፌ ምትቀሰቅሰኝ እሷ ሆነች ምሳ ሰአት እንኳን ምሳ መብላት እንዳለብኝ ምታስታውሰኝ እሷ ሆነች።
በተገናኘን ቁጥር የሆነ ስጦታ ይዛልኝ ትመጣለች ።
በፍፁም ያልተገባ ነገር አታደርግም ረጋ ያለች ናት ከኔጋ አብራኝ እየሄደች በተአምር አይኗ ሌላ ወንድ ላይ አያርፍም።
አክብሮቷ ላቅ ያለ ነው እኔ አጥፍቼ ቀድማ ይቅርታ ምትጠይቀኝ እሷ ናት አትወደኝም እንዴ ብዬ እስክጠራጠር ድረስ ትልቅም ትንሽም ጥፋት ባጠፋ ቀድማ ይቅርታ ትጠይቀኝና ሼም ታሲዘኛለች።

ስራ ቦታ ካሉት ጓደኞቼጋ  ካስተዋወኳት ጊዜ ጀምሮ ሁሉም ጓደኞቼ በጣም ነው ሚወዷት ስትመጣ በፍቅር ነው ሚቀበሏት እኔም እንዳለችው እሷን ለማፍቀር ብዙ ጊዜ አልፈጀብኝም ነበሮ ግን የፍቅር ስሜት በራሱ ምን እንደሆነ ስለማላቅ ከራሴ ስሜትጋ እየታገልኩ ነበር የቆየሁት።

በመጨረሻም እኔ እራሴ አብረን እንድንሆን ጠየኳት።
(እናቴ ከልጅነቴ ጀምሮ የሰው ልጅ አጥብቆ የፈለገው ነገር መጥፊያው ነው ትለኝ ነበር)
.
.
.
ይቀጥላል


ድጋሜ ሌላ መልእክት።
አለመኖሬን ማስተዋልህ ገርሞኛል እኔኮ ማታ ማታ እዛ ስቆም ብርድ መቶኝ ታምሜ ተኝቼ ነበሮ ከስራም ተባረርኩ ታምሜ ብዙ ቀን በመቅረቴ አባረሩኝ።
በጣም ከፍቶኝ ነበር መልእክትህን ሳየው ልቤ እንዴት እንደመታ
ይላል።

መልእክት ተከታታይ ስትልክ ደበረኝና ደና ደሪ ብዬ ላኩላት።

ደና ደር ከቻልክ ነገ ስራ ከሌለህ እንገናኝ እኔ ማታ መጥቼ እንዳልጠብቅህ ድጋሜ በሽታዬ ይነሳብኛል አለችኝ።

ሲመቸኝ አሳውቅሻለሁ በቃ ድጋሜ መልእክት እንዳትልኪልኝ ብዬ ላኩላት።

በዛው አመረረችና ለሳምንት ያህል ዝም ስትለኝ ድጋሜ በኔ ምክንያት ታማ ይሆን እንዴ ብዬ ሲጨንቀኝ ነገ ቅዳሜ ስለሆነ ከሰአት ስራ አንገባም ከሰአት ላግኝሽ ብዬ መልእክት ላኩላት እሺ ስንት ሰአት አለችኝ 8 ሰአት ብዬ መለስኩላት።

በነጋታው 6.30 ሲል ስራ ቦታህጋ መጥቻለሁ እስክትወጣ እየጠበኩህ ነው ብላ ላከችልኝ።
ስምንስት ሰአት እንደተቀጣጠርንና አሁን ለምን እንደመጣች ጠየኳት።

አይ የምር ልታገኘኝ መሆኑን ስላላመንኩ እዚህ ተቀምጬ ልጠብቅህ ብዬኮ ነው ሀሰብ እንዳትቀይር ፈራሁ ችግር የለም እስከ ስምንት ሰአት እጠብቅሀለሁ ብላ መለሰችልኝ።

ሳቄ መጣ ያማታል እንዴ ይቺ ደሞ ከሁሉም የባሰች ናት ብዬ ከራሴጋ አወራሁና ልብሴን ቀያይሬ ተጣጥቤ ወጣሁ እዛው ቅርብ የነበረ ቤት ይዣት ሄድኩ ፊት ለፊት ለፊት ለፊት ተቀመጥን አይን አይኔን ስታየኝ እኔም ትኩር ብዬ አየኋት።

በጣም ቆንጆ ናት ድርብ ጥርስም አላት ፀጉሯም የራሷ ነው በዛ ላይ በጣም እረጅም ነው በውስጤ እሷን እያደናነኩ ለማውራት ግን ጅንን አልኩባት።
በዛ መሀል አስተናጋጇ መጥታ ምን ልታዘዝ አለችኝ እኔ ምንም አልፈልግም አልኳት እሷ ግን አረ ምሳኮ አልበላሁም አትበላም እንዴ አለችኝ
ውጭ ምግብ በልቼ እንደማላቅ ነገርኳት እሺ በቃ እኔም አልበላም አመሰግናለሁ አለች።

ያምሻል እንዴ አሁን ምሳ አልበላሁም አላልሽም መልሰሽ አልበላም ማለት ምን ማለት ነው አልኳት።
አይ እኔኮ አብረን እንበላለን ብዬ አስቤ ስለመጣሁ ነው አሁን ግን በቃኝ አልበላም አለች።

ለማንኛውም ፈጣሪ ያመመሽን ህመም ያርቅልሽ ደና መሆንሽን ለማወቅ ነው ዛሬ የቀጠርኩሽ በኔ ምክንያት የታመመሽ መስሎኝ ጥሩ ስሜት ስላልተሰማኝ ነው ደና ከሆንሽ ደና ሁኚ በቃ ድጋሜ እንዳትደውይ እኔም መልእክት አልክልሽም በዚህ ሰአት ስራዬ ላይ ማተኮር ነው ምፈልገው አንቺ ደሞ ነፃነቴን እያሳጣሽኝ ነው ብያት በተቀመጠችበት ጥያት ወጣሁ።

አልተከተለችኝም መኪና ውስጥ እየሄድኹ ግን ከራሴጋ ክርክር ጀመርኩ አንዱ ልቤ ደግ አደረክ ይለኛል ሌላኛው ልቤ ደሞ ልክ አላደረክም ወንድ የሆንክ መስሎህ ነው ይለኛል

ይቀጥላል...


✎ክፍል 3 ነገ ማታ 2:30 ይቀጥላል♥️    ቶሎ እንዲ🀄️ጥል LIKE♥️ እና Share አድርጉ።


  ይ🀄️ላ🀄️ሉን
https://t.me/+4dGFaH_mUnExZjg8
https://t.me/+4dGFaH_mUnExZjg8

💝የዩቲዩ ገፃችን💝
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333

10.4k 0 43 50 434

የፍቅር ጥግ



ክፍል 2



እሷ ተስፋ የቆረጠች አትመስልም በነጋታው ድጋሜ አንድ ወረቀት ሰታኝ ሄደች ከዛሬ ቡሀላ ስራ ስለምጀምር ማታ ማታ ነው ላይህ ምመጣው 11ሰአት ነው ከስራ ምወጣው ከዛ እዚህ መጣለሁ ይላል።
የልጅቷ ጤነኝነት አሳሰበኝ በዛ ላይ እኔ ቋሚ የመውጫ ሰአት የለኝም አንዳንዴ ቀን ወደቤት ልመለስ እችላለሁ አንዳንዴ ደሞ እስከ ምሽቱ ሶስት ሰአትም ልንሰራ እንችላለን የጀመርነው መኪና አስቸኳይ ከሆነና አላልቅ ካለን ሳንጨርስ አንወጣም  ።

በነጋታው አውቄ አስር ሰአት ሲል ወደቤት አመራሁና እማዬን ይዣት ወደቤተክርስቲያን ሄድኩ ቁጭ ብለን የልብ የልባችንን አወራን።

እናቴ ሆድ እየባሳት አንተም ለኔ እኔም ላንተ ብቻኮ ነው ያለነው እኛው ነን ለኛ ያለነው አደል ድንገትኮ አንዳንችን የሆነ ነገር ብንሆን  ብቸኛ ሆነን መኖራችን ነው ለምን ፍቅረኛ አትይዝም ለምን አታገባም ለኔም ቡና ሚያፈላልኝ ሰው እፈልጋለሁ ቀን ቀን ብቻዬን ተኝዬ ስውልኮ እየጨነቀኝ ነው ስራ አለህ ,እንደምታየውም ያማረ ግቢ አለን ልጅኮ በልጅነት ነው አለችኝ።
እሺ ተነሽ ወክ እናድርግ ቤት ላድርስሽና አንድ ቦታ ደርሼ ልምጣ ብያት ወደቤት ተመለስን እሷን ቤት አስገብቼ እኔ ቀጥታ የሰፈራችን ደላላጋ ሄድኩና ለነገ ግዴታ ሰራተኛ ያስፈልገናል ነገ በጠዋት ሰው አምጣልኝ አልኩት።

እሱም አላሳፈርኝም በነጋታው ስራ ቦታ ሆኜ ደወለና ሰው አግቼልሀለሁ   መጥተህ ውሰድ አለኝ ስራ ስላልነበረኝ በፍጥነት ሄድኩና ወደቤት ወስጄ  ከእናቴጋ አስተዋወኳት ይኸው ቀን ቀን ቡና ምታፈላልሽ ምታዋራሽ ልጅ አምጥቼልሻለሁ አልኳት።

እናቴ ክፍት ብሏት አይ አንተ ልጅ እኔ አሁን ሰራተኛ ቅጠርልኝ አልኩህ እእ ቆይ አንድ ቀን ምግብ እንኳን ውጭ በልተህ ማታቅ ልጅ በሌላ ሰው እጅ የተሰራ ምግብ እየበላህ ለመኖር ዝግጁ ነህ አለችኝ።
አዎ እማዬ አሁን አንቺ እረፍት አድርጊ እኔ እለምዳለሁ ምን ችግር አለው ምግብ ምግብ ነው አልኳት።

ጥርሷን ነክሳ ቆይ አንተን በሚመስል አስተያየት እያየችኝ ልጅቷን ጠራችና የወር ደሞዟን ጠየቀቻትና ከደሞዟ በላይ ጨምራ ብር ሰጥታ ይቅርታ ስላስለፋንሽ ግን እኔ ሰራተኛ አልፈልንም እሺ አላድክመሽ በል ሸኝተሀት ና ደላላውጋ ብላ ከቤት አስወጣችን
እኔም ወስጄ ልጅቶን ለደላላው መልሼ በደንብ ይቅርታ ጠይቄ ተመለስኩ።

ቤት ስደርስ በቅጡ እንኳን አስተውያት የማላቃት የጎረቤት ልጅ ከእማዬጋ ቁጭ ብላ ከጣራ በላይ ይሳሳቃሉ።
እኔ ስገባ ልጅቷ አይኗን መሬት ላይ ተክላ ዝም አለች ያ ሁሉ ሳቅ ባንዴ ጥፍት አለ።

እናቴ ጠራችኝና ኑ በደንብ ተዋወቁ እኔ አንድም ቀን ደብሮኝ አያውቅም እሷ ሁሌም ከኔጋ ናት ከፍሪጅ እያወጣሁ አሙቄ ምሰጥህ ምግብ እሷ የሰራችው ነው እንደው ምን እንዳደረካት ባላቅም እንደጦር ነው ምትፈራህ ዛሬ እንኳን ደፍራ አይንህን ትየው በዛውም እኔ ትናት ቀን ቀን አብሮኝ የሚውል ሰው ያልኩህ እንድታገባ ልጫን ፈልጌ እንጂ የምር ደብሮኝ እንዳልሆነ እንድታቀው ነው አለችኝ።

እኔም ልጅቷን ሄጄ ሰላም አልኳት እጇን ስጨብጣት ከመንቀጥቀጡ የተነሳ  ጎንደረኛ እየጨፈረች ሰላም ምትለኝ ሁላ ነበር የመሰለኝ።
እናቴን ስለምትከባከብልኝ እያመሰገንኳት ካፌ ሳልጨርሰው ዝም ብላ እየሮጠች ከቤት ወጥታ ሄደች
ሁኔታው ግራ ገብቶኝ እማዬ ደሞ ምንድነው ከእንደዚች አይነት ህፃንጋ ምትውይው ደሞስ እብድ ናት እንዴ እያወራሁ ምን ያሮጣታል አልኳትና ቁጭ ብለን ማውራት ጀመርን።

በሚቀጥለው ቀን አንድ አስቸጋሪ መኪና ገጥሞን ከጠዋት ጀምሮ እሱን ስንሰራ ዋልን አንዴ ስንገጥም መልሰን ስንፈታ ወገባችን መቆም እስኪያቅተው ሰራን እኔና አለቃዬ ብቻ ስለቀረን ማታ 2,30 አካባቢ ሰርተን ጨረስን እኔ ገብቼ እስክታጠብና ቱታዬን እስክቀይር አንተ ነድተኸው ና ብዬው እሱ መኪናውን ይዞት ወጣ ።
እኔም ጨራርሼ ስወጣ  አስር ጉዳይ ለሶስት ይላል ሰፈሩ ትንሽ መሸት ሲል ሰው ጭር ስለሚል ብዙም ደስ አይልም ድባቡ እስኪመጣ በር ላይ ቆሜ እየጠቀኩት ልጅቷ ጥጓን ይዛ በዛ ጨለማ ቆማ አየኋት በሰአቱ ምን እንደሆንኩ አላቅም እንደእብድ ፈጥኜ የቆመችበትጋ ሄድኩና በጥፊ አጋጨኋት ያምሻል እንዴ በዚህ በምሽት ለዛውም እዚህ ሰፈር ብቻሽን እንዴት እስካሁን ትቆያለሽ ሲጀመር ውስጥ መሆኔን በምን አወቅሽ አልኳት።
11 ሰአትኮ ነው የመጣሁት ቅድም ጓደኞችህን ጠይቄ ነው ውስጥ መሆንህን ያወኩት አለችኝ።
እና ብሆንስ ምን ሆነሻል የሆነ ነገር ብትሆኚስ ሌባ ቢሰርቅሽስ እራስሽን አትወጂውም እንዴ አልኳት።

አንተን ከምወደው በላይ እራሴን አልወደውም አለችኝ።
ቃላት ለማውጣት አፌ ሁላ ተያያዘ.
ቆሜ ማወራው ነገር ግራ እንደገባኝ አለቃዬ መጣና በቃ እንሂድ አሪፍ ነው የሰራነው ዛሬ መኪናው እኔጋ ይደር በዛውም ልሸኝል አለኝ።

እሺ ብዬ ትቻት ልገባ ስል አሳዘነችኝና የት ነው ቤትሽ እንሸኝሽ አልኳት።
ነገረችን እኔም እሷም ከኋላ ገባን ንዴቴ ስላልበረደልኝ እየደጋገምኩ ድጋሜ እዚህ ቆመሽ እንዳታመሽ ሰፈሩ እንኳን ለሴት ለወንድ ያስፈራል አልኳት።

እንደዛ ከሆነ ስልኬን ከብሎክ አውጣው አልጨቀጭቅህም አላስቸግርህም አንዳንዴ ብቻ ድምፅህን እንድሰማው ነው ብላ ስትለምነኝ እሺ ብዬ ስልኳን ከብሎክ አወጣሁት በዛውም ሰፈሯ ደርሰን ስለነበር ተሰናብታኝ ከመኪናው ወረደች።

እሷ ከወረደች ቡሀላ አለቃዬ እየሳቀ አይ ይች አለም በቃ ፍትሀዊ አደለችማ።
አንተ ሴት አትቀርብ ሴት አጠገብህ ቆማ እራሱ አታስታውላትም ሴቶች ግን አንተን ነው ሚከተሉት ምነው ላንተ ከሚያሽቃብጡ እኛንም ቢመለከቱን አለና ተሳሳቅን።

ሰፈር አድርሶኝ በዛውም እናቴን ገብቶ ሰላም ብሏት ሄደ ደክሞኝ ስለነበር ቶሎ ነበር የተኛሁት።
ጠዋት እንደተለመደው እናቴ ቀስቅሳኝ አርፍጄም ቢሆን ወደስራዬ ሄድኩ ።
ቀኑን ሙሉ ስራ ባይኖርም ውስጥ ቁጭ ብለን ነበር የዋልነው ማታ ላይ ከስራ ስወጣ ልጅቷ መንገድ ላይ እንደምጠብቀኝ ተስፋ አድርጌ ነበር ግን የለችም የሆነ እቃ እንደረሳ ሰው ቅር ቅር አለኝ።
ቤት እንደገባሁ ዛሬኮ ታምሜ ነው ላይህ ያልመጣሁት ይላል መመለስ ስላልፈለኩ ዝም ብያት ተኛሁ።
እንዲሁ ፊልም እንደሰራችብኝ ድጋሜ ሌላ ሳምንታቶች ተቆጠሩ እኔም ልክ ከስራ ስወጣ የሆነ ነገር እንደሚጠብቀኝ ነገር ልቤ ስቅል ይላል ግን ደሞ ስልክ መደወል text መመለስ ወይ ስትደውልልኝ ማንሳት አልፈልግም።

ድንገት ግን ምን እንደተፈጠረ ሳላቅ ለአስራአምስት ቀን ያህል ጠፋች በየቀኑ እንደምትመጣ ተስፋ እያደረኩ ከስራ እወጣለሁ ግን የለችም ከዛሬ ነገ ትደውላለች ብዬ ጠበኩ እሷ በፍፁም መልእክት እራሱ ሳትልክልኝ ስለቆየች ድንገት የሆነ ነገር ተፈጥሮባት ቢሆንስ ብቻ መጨነቅ ጀመርኩ መሰለኝ ለእናቴ ነገርኳት ምነው አንተ በዚህ ልክ ይጨከናል እንዴ የሆነ ነገር ሆና ቢሆንስ ታማም ሊሆን ይችላል ባትወዳት እንኳን ድንገት ምታቀው ሰው እንደዚህ ቢሆን ያስችልሀል በል ደውልላት ብላ ተቆጣችኝ።
እኔ ግን መደወሉ ሞት መስሎ ታየኝ  አልደውልም ብዬ ከተውኩት ቡሀላ የእናቴ ውትወታ አላስቀምጥ ሲለኝ ስልኬን አንስቼ መልእክት ላኩላት

በሰላም ነው የጠፋሽው የሆንሽው ነገር አለ እንዴ ?ብዬ ላኩላት

ፅፌ መጨረሴንና መላኬን እርግጠኛ ባልሆንኩበት ቅፅበት አዎ ደናነኝ ብላ መለሰች።
ዝም አልኳት።
ቀጠለችና  መልእክት በድምፅ መላክ ቢቻል ምን ያህል ደስ እንዳለኝና መልእክቱን ሳየው እንዴት እንደጮኩ ብታይ ደስ ይለኝ ነበሮ አለች።
በድጋሜ አይቼው ዝም አልኩ።


የፍቅር ጥግ


             ክፍል 1


እነሆ የመጀመሪያ ክፍል 👇👇👇

በጠዋቱ ከእንቅልፌ ተነስቼ  እየተጣደፍኩ  መለባበስ ጀመርኩ እማዬ ከስር ከስሬ እየተከተለች ታጎርሰኛለች እኔ አንዱን እቃ ሳነሳ አንዱን  ስጥል እንደልማዴ እየተርበተበትኩ እማዬ ያጎረሰችኝ አጣጥሜ በልቼ ወጣሁ።

ገና ትንሽ ከመራመዴ ከኋላ ከኋላዬ እማዬ እየጠራች ትከተለኛለች ድምጿን ስሰማው ወደኋላ ዞርኩኝና ደንግጬ ወደሷ ተመለስኩ
ልጄ ምን ሆነህ ነው ምሳህን እረስተህ ምትወጣው በል እንካ ብላ ትንሿን ቦርሳዬን አቀበለችኝ።
እኔም አመስግኛት መልሼ ወደቤት አስገብቻት ስሚያት ወደስራ ቦታዬ ሄድኩ።

ትናት ጀምሬ የተውኩትን መኪና ወደመጠጋገኑ ገባሁ  ።
ወዲያው አለቃዬ ከውስጥ ወጣና አንተ ወመኔ በቃ ይሄ ማርፈድህን እንቢ አልክ አደል አለኝና ተሳስቀን አብረን መስራት ጀመርን።

ወዲያው እማዬ ደወለችና እንደለመደችው አለቃህ ምን አለህ እረፈደብህ ስንት ሰአት ደረስክ ብላ ጠየቀችኝ ሁሉንም ነገርኳትና ከአልጋ እንዳትወርድ ምግቧን ብቻ በልታ እንድትተኛ ቃል አስገብቻት ስልኩ ተቋረጠ።

ምሳ ሰአት ላይ ሁሉም ምግብ አዞ ሲበላ እኔ የራሴን ምሳ በላሁ።
ትኩስ ነገር ለመጠጣት ወጣንና ጠጥተን እየተመለስን ገራጁ በርጋ አንዲት ልጅ መጥታ ገጨችኝና እራሷ መሬት ላይ ወደቀች ትኩር ብዬ አየኋትና ያምሻል እንዴ የተገጨሁት እኔ የወደቅሽው አንቺ ምን ሆነሻል ብዬ እዛው በወደቀችበት አልፊያት ወደገራጁ ገባሁ።

ይኸው ከዛን ቀን አንስቶ ለድፍን አንድ ወር ያህል ያለምንም ማቋረጥ ጠዋት ስራ ከመግባቴ በፊት ከስራ ቦታዬ አጠገብ ቆማ ጠብቃ አይታኝ በፍጥነት ከዛ አካባቢ ትሰወራለች።

አንዳንዴ ማናስታውላቸው ግን ውስጣችን ተላምደው ሚቆዩ ነገሮች አሉ አደል ብቻ ሳላስበው ሁሌ ጠዋት ጠዋት እሷን ማዬቴን ተላምጄው ነበር።
ልክ ድፍን አንድ ወር ሲሞላት የመጀመሪያ የተገናኘን ቀን እንደተጋጨነው ምሳ ሰአት ላይ መጣችና አውቃ ገጭታኝ እራሷ ወደቀች ሳያት አላስቻለኝም አይቻት ፈገግ አልኩ ...ከኔ በላይ ከት ብላ ሳቀችና ወይኔ ጉዴ አንተ ስቀህ ታቃለህ እንዴ ልክ በወሩ ታምር አየሁ ማለት ነው ፈገግ ስትል ነው ያየሁህ አደል አለችኝ።

አንቺ ጤነኛ አትመስይኝም እብድ ብያት አሁንም ትቻት ገባሁ።

ወደውስጥ ገብቼ ዞር ብዬ ሳያት ብቻዋን እየሳቀች እንደ እብድ እየሮጠች ሄደች።

ምኗን ነው የጣለብኝ እንዴ ምን ሆና ነው ብዬ ከጓደኞዬጋ ተሳስቄ ወደስራ ገባሁ።
እማዬ ህመሟ ትንሽ እየባሰባት ስለነበር በየደቂቃው ነው ስልክ ምደውልላት

በነጋታው ደገመችና ጠዋት በር ላይ ጠበቀችኝ ስተየኝ ብቻዋን ሳቀችና ተመልሳ ሄደች።
ያ ነገር ያለማቋረጥ ድጋሜ ለ15 ቀን ቀጠለ።


የሆነ ቀን ጠዋት ላይ እማዬ በጣም ስላመማት ከስራ ቀረሁ።
ጓደኞዬ ደጋግመው እየደወሉ ሲጨቀጭቁኝ ስልኬን አጠፋሁት።
ለእናት ቡና አፈላልቼ ምግብ ሰርቼላት አበላኋትና አለባብሻት ወደሀኪም ቤት ይዣት ሄድኩ እንደተለመደው ምንም በሽታ የለባትም።
እረፍት ታድርግ እራሷን እንዳታስጨነቅ ብለው መለሱን።
ሁኔታው ሰላም ስለነሳኝ ቁጭ አድርጌ አወራኋት ምንሽን ነው ሚያምሽ ምንሽጋ ነው የሚሰማሽ ብዬ ጠየኳት እናቴ ነገሩን ቀለል አድርጋው አረ ልጄ እኔ በሽታዬ ይሄ ነው አልልህም በቃ እዚህጋ ነው ስል ሌላጋ ያመኛል ልቤን ስል ኩላሊቴን ኩላሊቴን ስል ጨጓራዬን ጨጓራ ስል እራሴን በቃ ግራ ነው ሚገባኝኮ አለችኝ።

በቃ ዛሬ ቤት ውለን እረፍታችንን እናጣጥም ብያት ስልካችንን ዘጋግተን ከእናቴጋ ፈታ ስንል ዋልን ማታ ላይ ተያይዘን ቤተክርስቲያን ሄድን ስንመለስ እማዬ በዛው ጎረቤት ገብታ ወሬ ስትጀምር እኔ ትቻት ወደቤት ገባሁና ስልኬን ከፈትኩት ብዙ ያልተሳካ ጥሪ ገባልኝ ከፍቼው ደቂቃ ሳልቆይ ማላቀው ቁጥር ተደወለልኝ አነሳሁት።
ሄሎ!
ሄሎ አንተ በሰላም ነው ዛሬ ከስራ የቀረኸው አለችኝ።
ማን ልበል አልኳት።

ውይ እራሴን ሳላስተዋውቅ ፋኖስ ነኝ አለችኝ።
እሺ እኔ ደሞ ጨለማ ነኝ እንዴ... ፋኖስ ማነሽ አቅሻለሁ አልኳት
አዎ ታቀኛለህ ጠዋት ጠዋት አንተን ጥበቃ ብርድ እየጠጣሁ እየጠበኩህ እንዴት አታቀኝም ዛሬኮ ጠዋት ስትቀር ጓደኞችህን አልቅሼ ለምኜ ነው ስልክህን የሰጡኝ አለችኝ።
ማን እንደሆነች ሳውቅ እሺ ፋኖስ አሁን አወኩሽ ምን ፈልገሽ እንደደወልሽ ንገሪኝ ሰአት የለኝም አልኳት።

እእ ያው ዛሬ በሰላም ነወይ የቀረኸው ልልህና ድምፅህን ልሰማው ነው አለችኝ።

ስትሟዘዝ ነገረ ስራዋ አስጠላኝ
እንደውም ከቻልሽ ካሁን ቡሀላ ጠዋት ጠዋት እንዳላይሽ እያጨናነቅሽኝ ነው እኔ ሰላሜን ሚነሳኝ ሰው አልወድም አትከታተይኝ ስልኬ ላይም ደግመሽ እንዳትደውይ ብዬ ዘጋሁባት
ስልኳንም ብሎክ አደረኩት።


በነጋታው እንደለመደችው ከበሩ ፊት ለፊት ቆማለች እንደሌላ ጊዜው ፈገግ አላለችም አኩርፋ ነበር ባላየ አልፊያት ገባሁ።
የእማዬም ህመም ግራ እያጋባኝ ስራውም ትንሽ ቀዝቅዞ ስለነበር አንዳንድ ቀን ስራ እየገባሁ አንዳንድ ቀን ደሞ እየቀረሁ ሶስት ወራቶች ቆየን።

ሶስት ወር ሙሉ ፋኖስ አንድም ቀን ከመምጣት ተቆጥባ አታቅም ታየኝና እየሮጠች ትሄዳለች።
የቀረሁ ቀን በማይታወቅ ስልክ ትደዎልና ድምፅህን ልስማው ብዬኮ ነው በቃ ቻው ብላ ስልኩን ትዘጋዋለች እኔም የደወለችበትን ስልክ ብሎክ ማድረግ ሳይደክመኝ እሷም ስልክ እየቀያየረች መደወል ሳይደክማት ነው የቆየነው።

ጠዋት እንደተለመደው የስራ ቦታዬ በር ላይ ስደርስ ከሩቅ አንዴ አንዴ ጠብቀኝ እያለች እየሮጠች መጣች ።
ተኮሳትሬ ቆሜ ጠበቋት
ጥቁር ፌስታል አንጠልጥላለች እንካ ስጦታ ገዝቼልህ ነው እያለፍኩ ሳየው በጣም ስለወደድኩት ላንተ ገዛሁልህ እንካ አለችኝ።
አልፈልግም ሲጀመር አንድ ነገር ልንገርሽ ሴት ልጅ እራሷን ስታከብር ነው ደስ የሚለው በዚህ ልክ እራስሽን አታውርጅ እኔ ደሞ እንዳንቺ አይነት ሰው ምርጫዬ አደለም አትከታተይኝ ድጋሜ እዚህ ቦታ ቆመሽ እያየሽኝ ካገኘሁሽ አስቀይምሻለሁ ስጦታውን ደሞ ሂጅና ለሚፈልግ ሰው ስጭው ብያት ገፍትሬ ጥያት ገባሁ።
ንግግሬ ልኮ እንዳልሆነ ውስጤ ቢነግረኝም ግን ስላደረኩት አልፀፀተኝም ነበር።

ይቀጥላል....


✎ክፍል 2 ነገ ማታ 2:30 ይቀጥላል♥️    ቶሎ እንዲ🀄️ጥል LIKE♥️ እና Share አድርጉ።


  ይ🀄️ላ🀄️ሉን
https://t.me/+4dGFaH_mUnExZjg8
https://t.me/+4dGFaH_mUnExZjg8

💝የዩቲዩ ገፃችን💝
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333
https://www.youtube.com/@Kezerareaction333

10k 0 89 22 351

"Arguing with a fool proves there are two."


ከሞኝ ጋር መጨቃጨቅ ሁለት መሆናችንን ያረጋግጣል
🔻


ውድ የመልካም ልቦች ቤተሰቦች ፈጣሪ ካለ ከነገ ማታ 2:30 ጀምሮ አዲስ ታሪክ እጀምርላቹሃለው ዝግጁ ናችሃ ?


እኔን ነው የምቶደኝ እሱን አገባች እንጂ !

ጠይም ፍልቅልቆ ኤዱ ተሰፍሮ ከተሰጠን ብዙ ሽራፊ ጊዛያትን አብረን ሸርፈናል ብዙ ትዝታዎችን ተጋርተናል  ። ጥቁር ብዙ  ፀጉሯን በእጅ ጣቶቼ  እያርመሰመስኩ ፍቅሬን ገልጬላታለሁ ።

ተቀንድባ ያልቀነሰቻቸውን ብዙ  የቅንድቦቾን ፀጉር  በሌባ ጣቴ  እየዘበራረኩ አበሳጭቻታለሁ ። 

እወዳታለሁ፤ ትወደኛለች ፤ እንዋደዳለን ።

አብረን ስንሆን ሳቅ ይኖራል።  ነፃነት ይረበርባል ። ካለ አጀንዳ የመጣልን  ወሬ ላይ እንረባረባለን ።

እየተጨቃጨቅን ጭቅጭቃችን መሃል ላይ ሳቃችን ታግሎን እንደሚያውቅ ጭቅጭቁ በርዶ በሌላ ቀን  ሁለታችንም እየሳቅን ያሳቀንን አገላለፅ እየመዘዝን ስቀንበታል  ። 

በየቀኑ እየተገናኘን መሰልቸት የሚባል  Concept ውል ብሎን አያውቅም።

አንዳንድ   እንቅስቃስዬ በጥሞና ግዜ እንደሚጎረብጣት ትነግረኛለች።  ልቦናዬ ታውሮ ስለነበር  እሷን እንሚያሳጣኝ አልተገለፀልኝም ነበር።

ፍቅሯ በነፍሷ ስርቻ ውስጥ አለ ።  ዳስሸዋለሁ የማይዳሰስ ፍቅር ምላስ ላይ ብቻ  ያለ እንቶፈንቶ ነው ።

ለንቦጯን ጥላ ፤አኩርፋ ፤ተማራ እያጉመተመተች ስታገኘኝ ። የቆጥ የባጡን ለማሳቅ ዘብዝቤ ሳትስቅ የቀረችባቸው እለቶች አልነበሩም ።

እሱን አገባችው እንጂ እኔን ነው የምትወደው !

ስንት ቀን በግሬ ስኳትን ከባሏ ጋ በመኪና ቃል ሳይሰናዘሩ  ሲሄዱ አያቻቸዋለሁ።

ዘመናዊ ሆቴል ሲገቡ ጥግ አረቄ ቤት ተቀምጬ አይቻቸዋለሁ እጆን አልያዛትም ወይ ደሞ እሷ እጆን ጉያ ውስጥ አልወሸቀችም   ።

የኔ ኤዱ ከሁለት አንዱ አለማድረግ አይቻላትም ነበር ። እኛ መንገድ ላይ እንኳን ስናሽካካ እና ስንላፋ አፍረት አያግደንም

ከሱ ጋ ያጋመዳት ኑሮ ነው  ፍቅሯ እኔ ጋ ነው ያለው  ።

የፍቅር ታሪክ ብቻውን ለኑሮ አይሆንም ብላ ነው የወሰነችው ። ማሰላሰል የሌለው
ውስጣዊው ስሜት ብቻውን ረብ የለውም ብላ ነው አሰላስላ የተወቺኝ ።

አውጥታ አውርድ ስሜቷን አፍና ነው እሱን ያገባችው። ፍቅር ያረጃል ብሰለት ያሻግራል ብላ እንጂ  ቀልቧ እኔ ጋ ነው።  በግዜ ብዛት ልጅ ሲመጣ የኑሮ ቀንበር ሲጫናት  ከልቧ እወጣለሁ ። ከጓደኞቾ ጋ እንደዘበት ታነሳኛለች ።

ትክ ብላ ስታየኝ መወሰን እየታጋላታ እንደነበር ስታገባ ነው የገባኝ።  እንደቀልድ ስጋቷን ሹክ ስትለኝ ዋስትናዬን በተግባር አስደግፌ ማስዳስስ አልቻልኩም።

ኤዱ ዝም ብላ እንኳን ፊቷን አንብቤ ትገባኛለች። የንዴት መፍለቅያ ጠርዞቼን ታቃቸዋለች ። 

የኤዱን ገላ ከራሴም ገላ በላይ   እሷ የማታቃቸውን ገላዋ ላይ ያረፈ ጥቁር ጥንጥ ነጥብ ብዛት ሳይቀር አውቀዋለሁ።  ከኔ ጋ ነበር ማርጀት የነበረባት፤ ምን ያደርጋል  እኔን እየወደደችኝ እሱን  አገባችው እንጂ !

ይሄ ሁሉ አንብባችሁ ማ 👍👍 ተጫኑ

🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!
😀
 
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔  @MELKAM_LBOCH13


ፍቅር ማለት❤️


ፍቅር ማለት ወሲብ አይደለም፡፡ወደም ጥሩ ምሽቶችን በጋራ ማሳለፍ አይዷለም፡፡በየጎዳናው ተቃቅፎ መታየትም ፍቅር ሊሆን አይችልም፡፡ፍቅር ማለት ማንም ሊያስዷስተን በማይችልበት መንገድ ላይ ደስታን የሚፈጥርላችሁ ከሚችል ሰው ጋር አብሮ መሆን ነው፡፡

🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!
😀
 
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔  @MELKAM_LBOCH13 💔

13k 0 64 1 134

:–መንገድ ይወስዳል መንገድ ይመልሳል
የምኖዳቸውን ሰዎች የወሰደው መንገድ ግን _ ●  መመለሻ የለውም መሰለኝ




መመለሻው መንገድ ጠፍቷቸው ነው?

በህይወታችን ማለት እስከ አሁን በኖርንባቸው እድሜ ስናስበው ብዙ የምኖዳቸው ሰዎች እኮ በዙርያችን አልፈዋል

አይደል? እስኪ ስንት የምኖደውን ሰው እስከ ዛሬ አጣን? በዙርያችን በጭራሽ እማይጠፉ እኛን አጉል ልማድ አስለምደውን ከዙርያችን የጠፉ ስንት ሰዎች አሉ?

እኔ በበኩሌ ብዙ የምወዳቸው እና እነሱ ስላሉ ብቻ ህይወቴ በደስታ የተሞላበት ጊዜያቶች እንዳሉ አስታውሳለው።እና ከነሱ ሰዎች ጋር የማሳልፋቸው ጊዜያቶች መቼም ቢሆን አይቀየሩም ሁሌም እንደዚ እንቀጥላለን ብዬ ነበር የማምነው።ግን እነዛ ሰዎች አሁን ከጎኔ የሉም።ለምን ግን አላውቅም

እነዛ ሰዎች የሚለዩን እኮ በሞት ላይሆን ይችላል ምናልባት የህይወት መንገዳችን ተለያይቶም ይሆናል ምናልባት እነሱም ፍላጎት ሳይኖራቸው ቀርቶም ይሆናል እኮ ግን በድንገት ተስፋ የጣልንባቸው የምኖዳቸው ሰዎች ርኛ ሳናስበው ይሄዳሉ።መሄድ ይሂዱ ታድያ ለምን አየመለሱም?

እኔ ሁሌ መንገድ ይወስዳል መንገድ ይመልሳል የሚባል አባባል እሰማለው እነሱን የወሰደው መንገድ ከሄዱ ቧላ በመሀል በ ድልድይ ተዘግቶ ነው ወይስ እነዛ ሰዎች መንገዱ ጠፍቷቸው?®

ይሄን ካልን በስተመጨረሻ ግን ሰው ይሄዳል ሰው ይመጣል ግን እድሜያቹን የማይመጣ ሰው እየጠበቃቹ አጠገባቹ ያለውን ሰው አትዘንጉ

አንዳንዴ ለሄደ ሰው ብቻ ሳይሆን በዙርያችን ላለ ሰውም ጊዜ መስጠት ያስፈልጋል ይሄ ማለት ግን እነሱም ቢሆኑ ሰው ይሄዳል ሰው ይመጣል ናቸው እና ደስታቹንም ሆነ ሀዘናቹን ሰዎች ላይ አታድርጉ
አሁን ላይ በጣም የምቶዱት ሰው ይሄዳል።የናንተ የመውደዳቹና የመቀራረባቹም ብዛት አይወስነውም። ሁሌ አብሯቹ አይሆንም የሰዎች መሄድ ተፈጥሯዊ ነገር ነው ምክንያቱም ስነ ፈጥረቱንም ስናየው የሰው ልጅ እዚህ ምድር የመጣው ተመልሶ ሊሄድ ነው። እንደዚ ብላቹ ካመናቹ ለመጣው እና ለሄደው ሰው ሁሉ ልባቹ አይሰበርም ለማንኛውም ቸር ይግጠማችሁ

🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!
😀
 
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔  @MELKAM_LBOCH13 💔

15.2k 0 42 12 165

🔦ምክር_ቢጤ🔦


እውነታ ነገር ቢኖር ድሀ አግብታ በርሀብ የሞተች ሴት የለችም!!.....
🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀
>>>

ሀብታም አግብታ ግን እንደፈለገ ከፍ ዝቅ ሲያደርጋት በብር የገዛት እስከሚመስለው የሚያመናጭቃት ለበሺታ የተዳረጉ ለሞት ስበብ ያደረጓቸው ሀብታሞች አሉ....

soምርጫውን አስተንትነው ለሚመርጡ ይሁን!? ድሀ ማለት የጭንቅላት የድን እንጅ የገንዘብ ምንም አይደለም…....!! ተሰርቶ የሚገኝ ነው ገንዘብ በአእምሮ ታስቦ በሰውነት ተሰርቶ የሚገኝ ነው!! በሀብት፣ በመልክ፣ በጤንነት፣ አትተማመኑ እነዚህ በድንገት ከእኛ የሚጠፋ ናቸው ።

🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌‌      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!
😀
 
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔  @MELKAM_LBOCH13 💔

13.6k 0 38 13 151

🔹10 ቀን ነው የቀረው አሁኑኑ ጀምሩት በሁአላ ታተርፉበታላችሁ 🔸

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

119 908

obunachilar
Kanal statistikasi
Kanalda mashhur

⭐⭐ውድቀት የደበቀው ውበት ሴተኛ አዳሪ ነች። ለብዙ ሰው የሽፍደት ማስታገሻ ናት። እሷን ከወሲብ ጋር ብቻ አጋምደው ነው የሚያስቧት ፤ የሚያዋሯት ፣ የሚ...
🔹 ፍለጋ 🔹 🔹ደስታን ስፈልግ ነው🔸 ደስታዬ የራቀኝ 🔹ፍቅርን ስሻ ነው🔸 ፍቅር የጠፋብኝ 🔹ሰላምን ሳስስ ነው🔸 ...
🔸ቤተሰቦች በአል እንዴት እያለፈ ነው? 🔻እስኪ ኮሜንት ላይ አሳውቁን🔻
​በሚወድህ ሰው ላይ ክፉ አትስራ ለሚፈልግህ ሰው ቢዚ ነኝ አትበል የሚያምንህን ሰው አታታል ሁሌም የሚያስታውስህን ሰው አትርሳ!! ቦታ ለሚሰጥህ ሰዉ ጊ...
ብንቆይ ይሻላል    ከመኖር አለመኖር ይሻላል እሚሉህን እንዳትሰማቸው። አለመኖር ተሽሎ አያውቅም…ሁሌም ፈጣሪን እንዲያቆይህ ለምነው…ለንሰሐ ሞት እንዲያበ...