አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና መላክ የሚችሉት ቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ማሻሻያ ሊደረግ ነዉ ተባለ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና መላክ በሚቻለው ቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ጭማሪ ለማድረግ መመሪያውን እየከለሰ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
ላለፉት 27 አመታት ሲተገበር በቆየው አሰራር መሰረት አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና ለሚያስገቡት እቃ በቅድሚያ መላክ/መክፈል የሚችሉት የውጭ ምንዛሬ መጠን ከ5 ሺ ዶላር መብለጥ እንደማይችል የማእከላዊ ባንኩ መመሪያ ደንግጓል።
ይህን ተከትሎ ከ5ሺ ዶላር በላይ ቅድመ ክፍያ መፈፀም ከፈለጉ ከአገር ውስጥ ባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸው እንደነበር ይታወቃል ።
ይህ የጭማሪ መጠኑ ምን ያህል እንደሆነ የተገለፀ ነገር ባይኖርም አዲሱ መመሪያው ግን በቀጣይ መጋቢት ወር ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና መላክ በሚቻለው ቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ጭማሪ ለማድረግ መመሪያውን እየከለሰ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
ላለፉት 27 አመታት ሲተገበር በቆየው አሰራር መሰረት አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና ለሚያስገቡት እቃ በቅድሚያ መላክ/መክፈል የሚችሉት የውጭ ምንዛሬ መጠን ከ5 ሺ ዶላር መብለጥ እንደማይችል የማእከላዊ ባንኩ መመሪያ ደንግጓል።
ይህን ተከትሎ ከ5ሺ ዶላር በላይ ቅድመ ክፍያ መፈፀም ከፈለጉ ከአገር ውስጥ ባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸው እንደነበር ይታወቃል ።
ይህ የጭማሪ መጠኑ ምን ያህል እንደሆነ የተገለፀ ነገር ባይኖርም አዲሱ መመሪያው ግን በቀጣይ መጋቢት ወር ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily