Ethiopian Business Daily


Channel's geo and language: Ethiopia, English


Stay ahead of the curve with EBD. We provides daily updates on business news and trends in Ethiopia, perfect for start-ups, entrepreneurs, businessmen, & anyone interested.
Contact us: @EBD_enquiries
Join Discussion Group:
https://t.me/+eq3KEXbX55s1YWQ0

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Statistics
Posts filter


ኢትዮ ቴሌኮም በጥቅምት ወር 10 በመቶ ድርሻውን ማለትም እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ለህዝብ በሽያጭ ማቅረቡ ይታወቃል።

የአክስዮን ሽያጩ ለ121 ቀናት ቆይቷል። አጠቃላይ 47,377 ኢትዮጵያውያን ኢንቨስተሮች ሼሮችን ገዝተዋል፤ በአጠቃላይ 10.7 ሚሊየን ሼሮችን ሽያጭ ተከናውኗል በገንዘብ ሲተመን 3.2 ቢሊዮን ብር ይይዛል።

አሁን ላይ በአክስዮን ሽያጩ የተገኘው 3.2 ቢሊየን ብር ገንዘብ እስካሁን ለምንም አይነት ጥቅም ሳይውል በዝግ አካውንት ተቀምጦ እንደሚገኝ ኢትዮ ቴሌኮም አሳውቋል።

Source: theethiopianeconomistview
@Ethiopianbusinessdaily


ከ31 ባንኮች መካከል 28ቱ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መጭበርበራቸው ተገልጿል! በዚህ ዓመት ባንኮች ያጡት ገንዘብ ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ300 ሚሊዮን ብር ጭማሪ አለው!

የማጭበርበር ድርጊቶቹ የተፈጸሙት በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች፣ በተሰረቁ የATM ማሽኖች፣ በሐሰተኛ ቼኮች፣ በሐሰተኛ የስልክ መልዕክት እና ተያያዥ መንገዶች አማካኝነት ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርትን ጠቅሶ የፌደራል የሥነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሞሽን ነው ይፋ ያደረገው፡፡

Source: theethiopianeconomistview
@Ethiopianbusinessdaily


Partners Content: #EDtechMondays

Join us on Monday, 28th April 2025, at 8:10 PM EAT on Fana FM 98.1 for Harnessing Data for Better Educational Outcomes: Innovative Infrastructure Funding.

Featuring insightful panelists Michael Kahsay (Co-Founder & CEO, HENON Adaptive Learning), Inku Fasil (EdTech Trainer and Advisor), and Dr. Bethelhem Seifu (Lecturer at AAiT, Addis Ababa University), moderated by Rediet Meshesha (Journalist and Host of Cybergna at Ethio FM).

We'll discuss how data analytics can transform education, innovative financing solutions, and ways to ensure equitable EdTech access for marginalized groups.

Don't miss this vital conversation on empowering inclusive education in Ethiopia!


IMF ይህ ዓመት ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ GDP 117 ቢሊየን ዶላር ሲሆን የኬንያ GDP 132 ቢሊየን ዶላር ይሆናል ሲል ትንበያ አውጥቷል! ይህ ማለት በምስራቅ አፍሪካ ኢትዮጵያ የነበራት የኢኮኖሚ መጠን መሪነት ወደ ኬንያ ይሸጋገራል ማለት ነው!

በኢትዮጲያ የምንዛሬ ሁኔታ በገበያ እንዲወሰን ከተደረገ ጀምሮ የብር የመግዛት አቅም መዳከሙ ጠቅላላ ሀገራዊ የምርት መጠኑን ቀንሶታል!

በዚህ ወቅት፡ አንድ የአሜሪካ ዶላር የ129 የኬንያ ሽልንግ ዋጋ አለው! እንዲሁም  የ131 የኢትዮጵያ ብር ዋጋ አለው (የብሄራዊ ባንክ የዶላር የጨረታ አማካይ ዋጋ ቢወሰድ)!

ከምንዛሬ ፖሊሲ ለውጡ በፊት (የዛሬ 10 ወር)  አንድ የአሜሪካ ዶላር የ57 የኢትዮጵያ ብር ዋጋ ነበረው (የባንኮች Official የሚጠቀስ ተመን ሲወሰድ)!

ኢትዮጵያ የምንዛሬ ፖሊሲ ለውጥ ከማድረጓ በፊት (2024) አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ የ134 የኬንያ ሽልንግ ዋጋ ነበረው!

ልዩነቱን የሚፈጥረው የኢትዮጵያ ብር በ10 ወር ውስጥ ከ57 ብር ወደ 131 ብር ሲወርድ የኬንያ ሽልንግ ከ134 ወደ 129 የኬንያ ሽልንግ ከፍ ነው ያለው!

Source: theethiopianeconomistview
@Ethiopianbusinessdaily


Holland Dairy, a leading name in Ethiopia’s dairy scene, has introduced a new Banana Yoghurt made with locally sourced bananas. Announced earlier this week, the product merges traditional Ethiopian flavors with modern dairy trends, offering consumers a creamy, naturally sweet treat without artificial additives.

Managing Director Jean-Paul Rieu said the product supports smallholder farmers and offers a natural, creamy taste without artificial ingredients. Available in 150ml and 425ml sizes, the Banana Yoghurt joins the company’s existing fruit yoghurt range.

The initiative has already injected about US$50,000 into rural economies and uses eco-friendly packaging. With rising demand for flavored yoghurt, Holland Dairy’s new product is set to make a mark locally and in neighboring markets soon.

Source: linkupbusiness

@Ethiopianbusinessdaily


Ethio Telecom’s IPO Left Hanging with Just 10.7% of Shares Sold

Six months after issuing 100 million ordinary shares in Ethiopia’s first-ever Initial Public Offering (IPO), Ethio telecom has announced that it sold just 10.7 million of them.

Read More

Source: shegamedia
@Ethiopianbusinessdaily


በኢትዮጵያ ጨምሮ በሌሎች አፍሪካ ሀገራት የሚንቀሳቀሰዉ "አግራ" በዩኤስኤአይዲ መቋረጥ 40 ሚሊዮን ዶላር አጣ

የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ህብረት (AGRA) የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በወሰዱት የእርዳታ ቅነሳ ምክንያት 40 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የገንዘብ ድጋፍ ማጣቱን አስታውቋል።

በኬንያ መቀመጫውን ያደረገዉ አግራ በኢትዮጵያ ጨምሮ በ12 የአፍሪካ አገራት ውስጥ ከትናንሽ አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር የግብርና ልምዶችን ለማሻሻል፣ ገቢን ለማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ለማበረታታት የሚሰራ ግዙፍ ግብረሰናይ ተቋም ነው።

ድርጅቱ እንደገለፀዉ ከ ዩኤስኤአይዲ የሚገኘው የገንዘብ ድጋፍ መቋረጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን እየጎዳ እንደሚገኝ ጠቁሟል።

የአግራ ፕሬዝዳንት አሊስ ሩህዌዛ እንደተናገሩት ሌሎች የአውሮፓ አገራት ለጋሾችም የገንዘብ ድጋፋቸውን እየቀነሱ መሆኑን ። ይሁን እንጂ የአሜሪካ የእርዳታ ቅነሳ የአፍሪካ አገራት በግብርናው ዘርፍ ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ እንደ "ማንቂያ ደዉል" መሆኑን መናገራቸውን  ኤኤፍፒ ዘግቧል።

ይህ የ 40 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ አግራ ከ ዩኤስኤአይዲ ሊያገኘው ከታቀደው 100 ሚሊዮን ዶላር የእርዳታ አካል እንደነበር ገልጿል።

በተመሳሳይ በዚህ ሳምንት የተባበሩት መንግስታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ በቂ የገንዘብ ድጋፍ ባለመኖሩ 650,000 የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ያለባቸውን ሴቶችና ህጻናት እርዳታ ሊያቋርጥ እንደሚችል አስታውቋል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


በአዲስ አበባ የመሬት ሊዝ 5ኛ ዙር ጨረታ ከፍተኛው ዋጋ በካሬ 265 ሺህ ብር ተመዘገበ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ባካሄደው 5ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎችን ይፋ አድርጓል።

በዘጠኝ ክፍለ ከተሞች ለ427 ፕሎቶች ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዚያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በተካሄደው በዚህ ጨረታ በአንድ ካሬ ሜትር ከፍተኛው ዋጋ 265 ሺህ ብር በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ተመዝግቧል።

የጨረታ ኮሚቴ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በዚህ ዙር ጨረታ ከፍተኛ ተወዳዳሪነት የታየ ሲሆን፣ በተለይም ለንግድና ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውሉ ቦታዎች ከፍተኛ ዋጋ ተሰጥቷቸዋል

ይህ ውጤት ከዚህ ቀደም ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓ.ም. በአስር ክፍለ ከተሞች በተካሄደው በ4ተኛዉ ዙር የሊዝ ጨረታ ከነበረው ከፍተኛ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ነው።  በወቅቱ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አንድ ካሬ ሜትር መሬት በ306 ሺህ 600 ብር ከፍተኛ ዋጋ ተመዝግቦ እንደነበር ካፒታል መዘገብ ይታወሳል። በንፅፅሩ ዝቅተኛው ዋጋ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 12 ሺህ 320 ብር ነበር።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


ኬንያ በ2025 የምስራቅ አፍሪካን ትልቁን ኢኮኖሚ በመሆን ኢትዮጵያን ልትቀድም ነው - አይኤምኤፍ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ባወጣው አዲስ ትንበያ መሰረት ኬንያ በ2025 የምስራቅ አፍሪካ ትልቁን ኢኮኖሚ በመሆን ኢትዮጵያን ልትቀድም ትችላለች።

ትላንት የወጣዉ አዲሱ ትንበያው እንደሚያመለክተው የኬንያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) በ2025 ወደ 132 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን 117 ቢሊዮን ዶላር ይበልጣል።

ይህ ትንበያ የወጣው የኢትዮጵያ ብር ምንዛሪ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መውደቁን ተከትሎ መሆኑ ተዘግቧል።

Read More

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


25ኛ ዓመት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ህዳር 14 / 2018 ዓ.ም. ይካሔዳል

የብር ኢዮቤልዩ ላይ የደረሰው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አለም አቀፍ 10ኪ.ሜ. ሊከናወን ሰባት ወራት ቀሩት።  ህዳር 16 ቀን 1994ዓ.ም. ጅማሮውን ያደረገው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በቀጣይ ህዳር 14 ቀን 2018ዓ.ም. 25ኛ ዙር ውድድሩን ያከናውናል።

ከአፍሪካ ትልቁ የ10ኪ.ሜ. የጎዳና ላይ ውድድር የሆነው ዝግጅቱ ባለፉት 24 የውድድር ዓመታት ወደ 760ሺህ አካባቢ ሰው በ10ኪ.ሜ. ውድድሩ ላይ አሳትፏል።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የዘንድሮ ውድድር በተጠናቀቀ ማግስት የ25ኛ ዓመት ክብረበዓሉን አስመልክቶ ለቀጣዩ ዓመት 500 ቀዳሚ ተሳታፊዎች በነጻ ምዝገባ ያከናወነ መሆኑ ይታወሳል። ለሌሎች የውድድሩ ተሳታፊዎች ምዝገባ ሐምሌ ወር ላይ እንደሚከናወን ተገልጿል።

“25ኛ ዓመታችንን አብረውን በመሆን ካበረቱን ሁሉ ጋር ለማክበር ተዘጋጅተናል ፤ ደስታችንን ከራሳችን ለመጀመር በዚህ እሁድ ኬንያ በሚደረገው ኤልዶሬት ማራቶን ላይ ተሳትፈን እና ሩጫችንን አስተዋውቀን እንመለሳለን።” ያሉት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ ዳግማዊት አማረ “ከወዲሁ ከሩጫችን ጋር የተያያዙ የተሳታፊዎቻችንን ልዩ ልዩ ታሪኮች እና ገጠመኞች መሰብሰብ ስለጀመርን በማህበራዊ ሚድያ ገጾቻችን ላይ ቢነገር የሚሉትን ትውስታቸውን ያካፍሉን” ሲሉ ለተሳታፊዎች ጥሪ አቅርበዋል።

ከ24 ዓመታት በፊት ውድድሩ ሲጀመር ኃይሌ ገብረስላሴ እና ብርሃኔ አደሬ የመጀመሪያውን ዓመት ውድድር ያሸነፉ አትሌቶች ሲሆኑ ፤ በዘንድሮ ውድድር ላይ ወጣቶቹ አትሌቶች ቢንያም መሃሪ እና አሳየች አይቸው ማሸነፋቸው ይታወሳል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


የግብዓት ዋጋ እስከ 400 በመቶ በመጨመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች እንዲጓተቱ ምክንያት ሆኗል ተባለ

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እንደገለፀው የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ እስከ 400 በመቶ መጨመሩ የመንገድ ግንባታው የሚፈለገውን ደረጃ ላይ እንዳይደርስ ምክንያት ሆኗል።

ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ እንደተናገሩት ይህንን ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በማቆም ነባሮችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ቃል የተገቡ ሁሉም የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይጠናቀቁ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

የምክር ቤት አባላትም ከ1980 ጀምሮ በጥናት የተለዩ መንገዶች እንዳልተገነቡ፣ የተጀመሩት በጊዜያቸው አለመጠናቀቃቸውንና የተሰሩትም ሳይገለገሉ መበላሸታቸውን አንስተዋል። በተጨማሪም ለመንገድ ልማት የተነሱ ዜጎች ለዓመታት ካሳ ሳይከፈላቸው መቆየታቸውንም ካፒታል ሰምቷል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው የመንገድ ግንባታ መጓተት የካሳ ክፍያና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግር መሆኑን አምነዋል። ችግሩን ለመፍታትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


የከተማ መሬት አቅርቦት 69% ቢጨምርም የጨረታ አፈጻጸም 6 በመቶ ብቻ ነዉ ተባለ

በከተሞች የልማት መሬት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ጭማሪ ቢታይም፣ በጨረታ የቀረበው መሬት መጠን እጅግ አነስተኛ መሆኑን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አስታውቋል።

እንደሚ ተቋሙ መረጃ ከሆነ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 17.6 ሺህ ሄክታር መሬት ለልማት የቀረበ ሲሆን ይህም ከታቀደው 14,000 ሄክታር በልጦ እንዲሁም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ69 በመቶ (7,200.14 ሄክታር) ብልጫ አሳይቷል።

ይሁን እንጂ መንግስት ከቀረበው መሬት ውስጥ 30 በመቶውን በጨረታ ለማቅረብ እቅድ ቢኖረውም፣ እስካሁን ለጨረታ የቀረበው 971 ሄክታር ብቻ ሲሆን ይህም ከጠቅላላው የቀረበ መሬት 6 በመቶውን ብቻ ይይዛል።

የ2017 በጀት ዓመት  የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረበዉ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በእነዚህ ወራት በአጠቃላይ በከተሞች ከሚገኙ 6.5 ሚሊዮን ቁራሽ መሬቶች መካከል እስካሁን ከ 1 ሚሊየን 757 ሺህ 272 (27.03%) የሚሆኑት ተመዝግበዋል ብሏል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


ቦይንግ ከአቀደው ከስድስት ወራት በኋላ የአፍሪካ ዋና ቢሮዉን በአዲስ አበባ ከፈተ

የአሜሪካው ግዙፍ የኤሮስፔስ ኩባንያ ቦይንግ የአፍሪካ ዋና ጽ/ቤቱን በአዲስ አበባ ዛሬ ከፈተ። ኩባንያው ቀደም ሲል ይህንን ቢሮዉን በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ለመክፈት እቅድ የያዘ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቶ ነበር። ይሁን እንጂ ከስድስት ወራት መዘግየት በኋላ ዛሬ ስራ መጀመሩ ተገልጿል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር ዓለሙ ስሜን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና የኩባንያው አመራሮች ተገኝተዋል። ሚኒስትሩ ይህ እርምጃ በአለም አቀፍ አቪዬሽን ውስጥ የኢትዮጵያን ሚና እንደሚያሳድግና ለአህጉሪቱ እድገት ወሳኝ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

ከአስራ አንድ ወራት በፊት የአሜሪካው ግዙፍ ኩባንያ ቦይንግ የአፍሪካ ዋና ቢሮዉን በኢትዮጵያ ለመክፈት በዝግጅት ላይ መሆኑን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል ። ይህ ውሳኔ ኬንያ ወይም ደቡብ አፍሪካ ለዚህ መስፋፋት ተመራጭ ቦታዎች ይሆናሉ የሚለውን ግምት ያቆመ ነበር።

ቦይንግ በ2023 ከኢትዮጵያ ጋር የነበረውን የንግድ ግንኙነት ለማጠናከር በኢትዮጵያ የተወሰኑ የአውሮፕላን ክፍሎችን በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ መድረሱ ይታወሳል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


Deposit Insurance Fund welcomes rising T-Bill yields

The Ethiopian Deposit Insurance Fund (EDIF), aimed at enhancing confidence in the financial sector, has embraced the recent surge in Treasury bill (T-bill) yields, identifying it as a crucial factor for revenue growth.

Since becoming operational in 2023, EDIF has increasingly favored the rising T-bill rates at National Bank of Ethiopia (NBE) auctions for investments.

Read More

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


Saudi-Ethiopian Business Council Inaugurated in Riyadh

The first session of the Saudi-Ethiopian Business Council convened in Riyadh, marking a step towards enhanced economic cooperation between the Kingdom and Ethiopia, the Ethiopian Embassy in Riyadh announced.

Read More

Source: 2merkato
@Ethiopianbusinessdaily


As Ethiopia Eyes a Plastic Ban, Paper Entrepreneurs Like Kirtas See a Green Opportunity

Kirtas, a local company specialized in repurposing Addis Ababa's paper waste into homeware and packaging, eyes a boom in demand for its recycled paper bags as policy phases out plastic.

Read More

Source: shegamedia
@Ethiopianbusinessdaily


የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሩቢዮ ያቀዱትን የአዲስ አበባ ጉብኝት ሰረዙ

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በአዲስ አበባ እና በናይሮቢ ለማድረግ ያቀዱትን ጉብኝት መሰረዛቸው ተዘግቧል። ይህ የሆነው የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በዛሬዉ ዕለት ለአምስት ቀናት ጉብኝት ወደ ቻይና ካቀኑ ከሰዓታት በኋላ ነው።

እንደ አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘገባ ከሆነ ሩቢዮ
በአፍሪካ በሚያደርጉት በዚህ የመጀመሪያ ጉብኝት የፀጥታ እና የንግድ ጉዳዮችን የሚሸፍን እንደነበር የተገለፀ ሲሆን አሁን ግን ላልተወሰነ ጊዜ አራዝመዋል።

ኢትዮጵያ በዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በተጣለው አስከፊ የንግድ ታሪፍ  ከተጣለባቸው 185 ሀገራት መካከል አንዷ ነች። ከኤፕሪል 5 ቀን 2025 ጀምሮ ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ለሚገቡ ሁሉም ምርቶች 10 በመቶ የመነሻ ታሪፍ መጣሉ ይታወቃል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


Insurance sector set for transformation as NBE issues landmark governance directive

The National Bank of Ethiopia (NBE) has unveiled a sweeping new directive aimed at overhauling corporate governance across the country’s insurance sector, in a move widely hailed as a turning point for industry transparency, accountability, and stability.

Directive No. SIB//2025, released this month, introduces far-reaching reforms to the management and oversight of Ethiopia’s insurance companies. The NBE’s initiative comes as the sector faces mounting pressure to modernize, improve consumer trust, and align with international best practices amid broader regulatory changes sweeping across East Africa.

Read More

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


The East African Securities Exchanges Association (EASEA) has launched the EAE 20 Share Index to facilitate and strength the stock exchange of the East African Region. This index tracks the performance of 20 leading publicly listed companies on the stock exchanges of Kenya, Tanzania, Uganda, and Rwanda.

Source: linkupbusiness
@Ethiopianbusinessdaily


Turkish, Ethiopian logistics associations forge partnership to boost sector collaboration

The Turkish Forwarding and Logistics Association (UTIKAD), a prominent logistics association and a vital sector lobbying group, has signed a cooperation agreement with Ethiopia’s FIATA-member association, the Ethiopian Freight Forwarders and Shipping Agents Association (EFFSAA).

This agreement was formalized during a side event at the International Civil Aviation Organization’s (ICAO) Global Air Cargo Summit in Antalya, Türkiye, on April 9.

Read More

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily

20 last posts shown.