Ethiopian Business Daily


Channel's geo and language: Ethiopia, English


Stay ahead of the curve with EBD. We provides daily updates on business news and trends in Ethiopia, perfect for start-ups, entrepreneurs, businessmen, & anyone interested.
Contact us: @EBD_enquiries
Join Discussion Group:
https://t.me/+eq3KEXbX55s1YWQ0

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Statistics
Posts filter


The Ethiopian Railways Corporation (ERC) and Korea Railroad Corporation (KORAIL) have signed a Memorandum of Understanding (MOU) to advance railway development, technical exchange, and infrastructure modernization in Ethiopia.

Read More

Source: addisfortune
@Ethiopianbusinessdaily


በአዲስ አበባ የባቡር ትራንስፖርት ትኬት ሽያጭ በዲጂታል መልኩ ሊጀመር ነው።

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ከወረቀት ትኬት ሽያጭ ወደ ዲጂታል ሽያጭ አገልግሎት ሊሸጋገር መሆኑን ገልጿል።

የዲጂታል ትኬት ሽያጩ ለጊዜው በተመረጡ ቦታዎች ማለትም በሀያት፣ጦርሀይሎች ዳግማዊ ሚኒሊክና ቃሊቲ ጣቢያዎች እንዲሁም በስታዲየም የሽያጭ ቁጥጥር በማድረግ የሚተገበር ይሆናል ተብሏል፡፡

የክፍያ ሥርዓቱ በቴሌ ሱፐር አፕና በዩኤስ ኤስዲ (USSD) ኮድ አማካኝነት መቁረጥ የሚያስችል ነው።

ይህ የፓይለት ሙከራ ድርጅቱ የወረቀት ሽያጭን ሙሉ ለሙሉ በማስቀረት ወደ ዲጂታላይዝድ የክፍያ ስርዓት ለመሸጋገር ለሚያደርገው ስራ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን የድርጅቱ የበላይ አመራሮች ተናግረዋል።

በዲጂታል ሽያጭና ቁጥጥር ለሚሳተፉ ሰራተኞች በሁለት ዙር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን የፓይለት ሙከራው በቅርቡ እንደሚጀምር የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል።

ባለፉት 10 አመታት ደንበኞች በተዘጋጁት 39 የትኬት መቁረጫ ጣቢያዎች የወረቀት ትኬት በመግዛት የቀላል ባቡሩን አገልግሎት ሲያገኙ እንደነበር ተመላክቷል።

Source: tikvahethmagazine
@Ethiopianbusinessdaily


#ለመረጃ፦ የአሜሪካ መንግስት ከ6 ሳምንት ግምገማ በኋላ 5,200 የUSAID ኮንትራቶች ሰርዟል! ይህም ማለት የUSAID 83% ፕሮማራሞቹ ተሰርዘዋል።

"ቀሪው 18% ማለትም 1,000 የድርጅቱ ፕሮግራሞች በስቴት ዲፓርትመንቱ በአግባቡ እየተመሩ ይቀጥላሉ" ሲሊ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አስታውቀዋል።

Source: theethiopianeconomistview
@Ethiopianbusinessdaily


CBE increases loan rates, faces backlash from industry stakeholders

The Commercial Bank of Ethiopia (CBE), a state-owned financial institution, has adjusted its credit interest rates, a decision that has incited criticism from industry stakeholders. Critics argue that the bank is misunderstanding its responsibility to protect the nation’s economic stability. Simultaneously, CBE has expanded its range of loan offerings.

Earlier this week, CBE announced the adjustment of its loan interest rates, marking the first revision in four years.

Read More

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


#BREAKING : ከስድስት ሳምንት ግምገማ በኋላ አሜሪካ 83 በመቶ የሚሆነውን የUSAID ፕሮግራሞችን መሰረዟን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሮቢዮ በ X ገጻቸው አስታውቀዋል።

በቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደረግባቸው የነበሩ 5200 ኮንትራቶች ተቋርጠዋል ያሉት ሚኒስትሩ እነዚህ ለብሔራዊ ጥቅማችን ምንም የማያገለግሉ አንዳንዶቹ የሚጎዱ ጭምር ናቸው ሲሉ ነው የገለጹት።

ቀሪ 18 በመቶ የሚሆኑት ፕሮግራሞች (1000 የሚጠጉ) በስቴት ዲፖርትመንቱ በአግባቡ እየተመራ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።

Source: tikvahethmagazine
@Ethiopianbusinessdaily


#BeerMarket The arrival of Kegna Beverages on the beer scene is major development for the beverage market. This ambitious undertaking represents a $250 million investment, with the projection to become a major player in a competitive industry. A sprawling factory complex is under construction in Ginchi Town, in Oromia Regional State, all set to start operations by late April. With over 14 years of experience in the beer market, Project Manager Afework Legesse is optimistic despite constraints like foreign currency shortages and rising input costs.

Read More

Source: addisfortune
@Ethiopianbusinessdaily


#FinancialSector Ethiopian Insurance Corporation (EIC) gets a new CEO as Abel Tadesse steps in succeeding Netsanet Lemessa. With a mandate for modernisation, Abel plans to transform EIC into a customer-centric, technology-driven powerhouse, paving the way for a potential public listing. His appointment follows a comprehensive assessment of EIC's 50-year history, focusing on enhancing market share and exploring international opportunities.

Read More

Source: addisfortune
@Ethiopianbusinessdaily


#ForexAuction The state-owned Commercial Bank of Ethiopia (CBE) secured 40pc of the 60 million dollars at auction but continued to post the lowest buying rates. Its cautious strategy displayed the Bank's role in stabilising the foreign exchange market, coupled with its intent to manage liquidity.

Read More

Source: addisfortune
@Ethiopianbusinessdaily


የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ያላመኑበትን ግብርና ታክስ በተጨማሪ በሌሎች ችግሮች እየተፈተኑ እንደሚገኙ ተገለፀ

የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ፎረም በከተማው ውስጥ የሚገኙ ባለሀብቶች ከባድ ችግሮች እያጋጠሟቸው መሆኑን ገልጿል። ፎረሙ የባለሀብቶችን ቅሬታ በሰነድ የተደገፈ መረጃ ለመቀበል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።

የባለአብቶች ፕሬዝዳንት አቶ አሸናፊ ሙሴ አያሌው ለካፒታል እንደገለጹት፣ ባለሀብቶቹ ያላግባብ ድርጅቶቻቸው መታሸግ፣ መፍረስ፣ መነጠቅ (መቀማት)፣ ሥራ እንዲያቆሙ መደረግ፣ ያላመኑበትን ከፍተኛ ግብርና ታክስ ለማስከፈል ማስገደድ፣ የባንክ አካውንታቸው መታገድ፣ ከሀገር እንዳይወጡ ወይም እንዳይገቡ እየተደረጉ ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በስልክ ዛቻና ማስፈራሪያ ማድረስ፣ የማያምኑበትን አሰልቺና ተደጋጋሚ መዋጮዎች መጠየቅ፣ እንዲሁም ተረጋግተው ሥራቸውን እንዳይከውኑ ማዋከብ፣ የብድር አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ያለማግኘት እና የመሳሰሉት ችግሮች እየደረሱባቸው መሆኑን ሰምተናል ብለዋል።

ይህን ተከትሎ ፎረሙ ከመጋቢት 01 እስከ 27 ቀን 2024 ዓ.ም ድረስ የከተማውን ባለሀብቶች ቅሬታ በሰነድ የተደገፈ መረጃ ለመቀበል መዘጋጀቱንና ባለሀብቶችም መረጃቸውን በሰነድ በማቅረብ እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል።

የባለሀብቶቹ ቅሬታ ከተሰበሰበ በኋላ ለሚመለከተው አካል በማቅረብ ችግሮቹ እንዲፈቱ ፎረሙ እንደሚሰራ አቶ አሸናፊ ሙሴ አያሌው ለካፒታል ተናግረዋል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


ሰሌክታ ግሩፕ በፖለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ከኢትዮጵያ ወጣ

በስዊዘርላንድ ዋና መስሪያ ቤቱን ያደረገው ሰሌክታ ግሩፕ በሰሜን ኢትዮጵያ ኩንዚላ የሚገኘውን የምርት ማዕከሉን በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በወታደራዊ ሁኔታዎች ምክንያት ወደ ኬንያ እና ኡጋንዳ ማዛወሩን አስታዉቋል።

ኩባንያው የዚህ ውሳኔ ምክንያት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለሰራተኞች ደህንነት ስጋት መፍጠሩ እና የሎጂስቲክስ ችግሮች መከሰታቸው እንደሆነ ገልጿል።

የኩባንያዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ አንስጋር ክሌም ይህን ውሳኔ "አሳማሚ እርምጃ" ብለው የገለፁት ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ያደረጉትን ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እና ጥረት ከንቱ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ውሳኔ በኩንዚላ አካባቢ ከ1,000 በላይ የስራ እድሎችን የሚያሳጣ ሲሆን፣ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ወደ 10,000 የሚሆኑ ሰዎችን ይጎዳል። ኩባንያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ህይወት መስመር እንደነበር እና መውጣቱ ትልቅ ጉዳት እንደሚያስከትል ገልጿል።

ካፒታል ያገኘዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ሰሌክታ ግሩፕ በኬንያ እና ኡጋንዳ ያሉትን የምርት ማዕከላት በማጠናከር ለደንበኞች የምርት አቅርቦት እንዳይቋረጥ ማረጋገጡን ገልጿል። ወደፊት ሁኔታዎች ሲሻሻሉ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ተስፋ እንዳለውም አስታውቋል።

ሰሌክታ ግሩፕ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም የሆነ የአበባ እና የጌጣጌጥ እፅዋት አምራች ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ ያግዛል የተባለዉ አዲስ መመሪያ ወጣ

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ አዲስ መመሪያ አውጥቷል።

"የባዮኤክቫለንስ ጥናት ማዕከል እና የባዮአናሊቲካል ላብራቶሪ ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1043/2017" ተብሎ የሚጠራው ይህ መመሪያ፣ በገበያ ላይ የሚውሉ የመድኃኒት ምርቶች ተመሳሳይ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃዎችን ማሟላታቸውን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

በተለይም በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ተመሳሳይ የሆነ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃ እንዲኖራቸው ለማድረግ ያለመ ነው።

ይህ መመሪያ "ባዮኢኩዊቫለንስ" የተሰኘ ልዩ ጥናት በማድረግ በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ያላቸውን ተመሳሳይነት ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል።

በተጨማሪም፣ መመሪያው የመድኃኒት
ማምረቻ ተቋማትና ላቦራቶሪዎች ፈቃድና ቁጥጥር ላይ እንደሚያተኩር ካፒታል ለመረዳት ችሏል።

መመሪያው በኢትዮጵያ የመድኃኒት ቁጥጥር ላይ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ለመድኃኒት ኢንዱስትሪው ዕድገት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። በተጨማሪም፣ ለሕዝብ ተደራሽና ጥራት ያላቸውን መድኃኒቶች ለማቅረብ ያለመ ነው ተብሏል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


Ethiopia’s Health Ministry Onboards DFS Players on Digital Health Ambition

Ethiopia’s Ministry of Health has entered into a service-level agreement with eight digital financial service (DFS) providers as part of its national digital health strategy.

Read More

Source: shegamedia
@Ethiopianbusinessdaily


በወርቅ ማምረት ሥራ ላይ የተሠማሩ የ32 አምራቾች ፈቃድ መሰረዙ ተገለፀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ የማዕድን ዘርፉ አፈጻጸም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታውቋል።

በክልሉ ከሚገኙ 58 ልዩ አነስተኛና 12 ባሕላዊ የወርቅ አምራቾች መካከል አፈጻጸማቸው ደካማ የሆኑት 32ቱ ፈቃዳቸው መሰረዙ ተገለጿል ።

የክልሉ የማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረማርያም ሰጠኝ በስድስት ወራት ውስጥ ምንም ዓይነት ወርቅ ማምረት ያልቻሉ 12 ልዩ አነስተኛና ሁለት ባሕላዊ አምራቾች አሉ። አሳማኝ ምክንያት ካላቀረቡ በቀጣይ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቀዋል።

በድንጋይ ከሰል ማምረት ፍቃድ ከወሰዱ ከ20 በላይ ባለፍቃዶች መካከል፣ እስካሁን ወደ ማምረት የገቡት ስምንት ብቻ መሆናቸው ተጠቁሟል።

በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 150 ኪሎ ግራም ወርቅ ለማምረት ታቅዶ 75.525 ኪሎ ግራም፣ እንዲሁም 100 ሺህ ቶን ድንጋይ ከሰል ለማምረት ታቅዶ 50 ሺህ ቶን ብቻ ማምረት መቻሉ ተነገረ ሲሆን የምርት እጥረቱ ምክንያት ሕገወጥነት እና ወደ ሥራ ያልገቡ አምራቾች መኖራቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


#TaxReforms The alcohol industry, represented by the Alcohol Manufacturers Association, is eager to see the system implemented to fight unfair competition from illicit trade. Leaders of the National Tobacco Enterprise, too, claim contraband trade accounts for an alarming 53pc of the tobacco market. They believe the enforcement of stamping could help stem these illegal practices.

Read More

Source: addisfortune
@Ethiopianbusinessdaily


አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3.2 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር ያለባቸው 62 ግለሰቦች ከአገር እንዳይወጡ ከለከለ

እገዳው የተጣለባቸው ግብር ከፋዮች በተደጋጋሚ ግብራቸውን እንዲከፍሉ የተደረገላቸውን ጥሪ ችላ ያሉ ናቸው።

ቢሮው ይህንን እገዳ ለመጣል የግብር አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀጽ 44 (ንዑስ አንቀጽ 1-3) መሠረት በማድረግ ሲሆን የእነዚህ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መላኩ ተጠቁሟል።

ይህ እርምጃ የተወሰደው ቢሮው በ2017 በጀት ዓመት የዕዳ አሰባሰብና አስተዳደር ክፍሉን በማደራጀት ግብር ከመሰወር ጋር በተያያዘ የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ በመቀጠል መሆኑን አስታውቋል።

በድጋሚ በተዋቀረው ክፍል ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ6.4 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብን የገለፀዉ የገቢዎች ቢሮ ሁሉም ግብር ከፋዮች ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡና ለከተማዋ እድገት እንዲያግዙ አሳስቧል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


#ለመረጃ፦ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ባካሄደው የዶላር ጨረታ በጨረታው ተሳታፊ ከነበሩ 27 ባንኮች ውስጥ ዶላር ያገኙት #12_ባንኮች ብቻ ናቸው፡፡ እነዚህ 12 ባንኮች ለአንድ ዶላር ከ130 እስከ 141 ብር ዋጋ ሰጥተዋል።

Source: theethiopianeconomistview
@Ethiopianbusinessdaily


ብሔራዊ የንግድ ፖርታል ማስፋፊያ ተጠናቀቀ፣ ሶስት ከተሞች ተካተቱ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የንግድ ፖርታል (NBP) ማስፋፊያ ፕሮጀክት መጠናቀቁን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። በአዲሱ ማስፋፊያ የአዳማ፣ የባህር ዳር እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የተካተቱ ሲሆን፣ ይህም የግንባታ ፈቃድ መስጠትን ጨምሮ የመንግስት አገልግሎቶችን በመስመር ላይ እንዲሰጡ አስችሏቸዋል።

ይህ ፖርታል በርካታ የመንግስት አገልግሎቶችን በመስመር ላይ ለማግኘት የሚያስችል መድረክ ሲሆን፣ የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ አገልግሎቶች (ኢ-አገልግሎቶች) እና ይህን አገልግሎት የሚሰጡ የመንግስት ኤጀንሲዎች በአንድ ማዕከል እንዲሰባሰቡ ታስቦ የተሰራ ነው።

ፖርታሉ በመጀመሪያ የተገነባው እ.ኤ.አ በ2019 በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር (ሚንት) ሲሆን፣ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብቻ አገልግሎት ይሰጥ እንደነበር ተገልጿል።

በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የታየውን መሻሻል ተከትሎ፣ ሚንት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ ፕሮጀክቱን ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ለማስፋት መቻሉን ካፒታል ሰምቷል።

የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም. ይፋ የተደረገዉ የዚህ ፖርታል ዋና ዓላማ የኢትዮጵያን የንግድ ምቹ ሁኔታ ማሻሻልና የመንግስት አገልግሎቶችን በዲጂታል ማቅረብ እንደሆነ ተጠቁሟል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


ኢትዮጵያና ሶማሊያ የባህር በር ውዝግብን በሰላም ለመፍታት ተስማሙ

ኢትዮጵያና ሶማሊያ በሶማሊላንድ ወደብ ዙሪያ የነበረውን ውዝግብ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መስማማታቸውን አስታዉቀዋል።

የሁለቱ አገራት መሪዎች በቱርክ አደራዳሪነት ባደረጉት ስብሰባ፣ ኢትዮጵያ በሶማሊያ ሉዓላዊነት ውስጥ በመሆን የባህር በር ለመጠቀም የሚያስችል የጋራ ተጠቃሚነት ያለው የንግድ ስምምነት ላይ ለመድረስ ተስማምተዋል።

ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞቃዲሾን ጎብኝተው ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ ጋር ተወያይተዋል። በስብሰባው አጀንዳ ቀዳሚው የዓፍሪካ ቀንድ ደህንነት እንዲሁም ባለፈው ታኅሣሥ በአንካራ እንደተስማሙት የኢትዮጵያ ወደብ ተደራሽነት የቴክኒክ ድርድር መጀመር እንደነበር ተጠቁሟል።

የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዳስታወቁት፣ ድርድሩ ቀጥሏል፤ ግቡም እስከ ሰኔ ወር ድረስ የአሠራር ማዕቀፍ ላይ መድረስ ነው። ይህ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ የምትጠቀምበትን ወደብ የሚገኝበትን ቦታና ወጪውን ይወስናል።

ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ፍላጎቷን በሰላማዊ መንገድ እንድታሳካ ትልቅ እድል የሚፈጥር ነው። ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ በሶማሊላንድ በኩል የባህር በር ለመጠቀም ያደረገችው ጥረት ውዝግብ አስነስቶ ነበር።

አሁን ግን ሁለቱ አገራት በመደራደርና በመስማማት የጋራ ጥቅምን ለማስጠበቅ ቁርጠኝነታቸውን ማሳየታቸውን ዘ ማሪታይም ኤክስኪዩቲቭ ዘግቧል።

ኢትዮጵያ ከኤርትራ መገንጠል በኋላ የባህር በር አልባ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ የራሷን የባህር በር ለመገንባት ጥረት ስታደርግ ቆይታለች። ይህ ስምምነት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያግዝና በክልሉ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily


☄️ከንግድ ባንክ ብድር ከወሰዱ አንዴ ያድምጡን

የሀገሪቱ ግዙፍ ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ወለድ ጭማሪ አደርጓል።


የኮንደሚንየም፣ የወጪ ንግድና ችርቻሮ ፤ግብርና ተበዳሪዎች ተካተዋል።

ባንኩ እስከ 6 በመቶ የብድር ወለድ ጭማሪ ሊያደርግ እድነሆነ ሰሌዳ ከምንጮቿ ተረድታለች።

ለባንኩ ሰራተኞች እና የውጭ ምንዛሬ ለሚያመጡ ደንበኞች የሚሰጠው የነበረው የ 7% ወለድ ወደ 11 -13% ከፍ እንደተደረገ ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል።

ለግብርና ተበዳሪዎች ደግሞ መጠነኛ ቅናሽ እንደተደረገም ነው ሰሌዳ የሰማችው።

የኮንደሚኒየም ተበዳሪ ደንበኞች ብድር ደግሞ ባለበት 12% እንደሚቀጥል ነው ምንጮች የገለጹት።

ባንኩ ሙሉ መረጃውን እስከ ሳምንቱ መጨረሻ ድረስ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

Source: seleda
@Ethiopianbusinessdaily


Economist Turned Engineer Secures 18.6 million Br for Tigray-Based Manufacturing Enterprise

A manufacturing enterprise based out of Tigray Regional State secures $150,000 in equity financing from Impacc, a philanthropic venture capital investment firm.

Read More

Source: shegamedia
@Ethiopianbusinessdaily

20 last posts shown.