Forward from: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
✝እንኳን አደረሳችሁ✝
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት=
✞ ሰማዕቱ በብኑዳ ✞
+ቅዱስ በብኑዳ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ በምድረ
ግብፅ ተባሕትዎን መርጦ የሚኖር ገዳማዊ አባት ነው::
በበርሃ
በጾምና በጸሎት ተወስኖ ለእግዚአብሔር የምስጋናን
መስዋዕት እየሠዋ አገልግሏል::
+በዘመነ ሰማዕታት ክርስቲያኖች በግፍ ሲገደሉ ቅዱሱ
ሰው በበርሃ ውስጥ ነበር:: አንድ ቀን የእግዚአብሔር
መልአክ መጥቶ
ሰማዕት እንዲሆን መከረው:: እርሱም ነጭ በነጭ ለብሶ
አምሮበት ወደ ንጉሡ ሔደ:: በፊቱም ቀርቦ በክርስቶስ
ስም ታመነ::
ብዙ ጸዋትወ መከራም ተቀበለ::
+ንጉሡ (መኮንኑ) "አመጣጥህ ወደ ሞት ሳለ ምነው
እንዲህ እንደ ሠርገኛ ማጌጥህ?" ቢለው "እኛ
ክርስቲያኖች ትልቁ
ሠርጋችን ሞታችን ነው:: ልንሔድ ከክርስቶስም ጋር
ልንኖር እንናፍቃለንና" ብሎታል::
+ቅዱስ በብኑዳ ብዙ ተሰቃይቶ: ተአምራትን ሰርቶ በዚሕች
ቀን ተሰይፏል:: የጽድቅን አክሊል ከሰማዕትነት ጋር ደርቦ
አግኝቷል::
❖ቸሩ አምላክ ከሰማዕቱ በረከትን ያካፍለን::
❖ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ በብኑዳ (ሰማዕት ወጻድቅ)
2.ቅዱስ ቄርሎስ: ሚስቱና 12 ልጆቹ ሰማዕታት (ከቅዱስ
በብኑዳ ጋር የተገደሉ)
በ 20 የሚከበሩ ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
6.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት
++"+ በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን
ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ
ብጹዓን ናችሁ::
ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ:: አትናወጡም:: ዳሩ ግን
ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ
ስላለ ተስፋ
ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር
የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት
ይሁን:: +"+ (1ዼጥ.3:13-16)
>
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠 /ማቴ ፫:፫/
🔷ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!
❇️ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)❇️
" 🔶ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::🔸
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት=
✞ ሰማዕቱ በብኑዳ ✞
+ቅዱስ በብኑዳ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ በምድረ
ግብፅ ተባሕትዎን መርጦ የሚኖር ገዳማዊ አባት ነው::
በበርሃ
በጾምና በጸሎት ተወስኖ ለእግዚአብሔር የምስጋናን
መስዋዕት እየሠዋ አገልግሏል::
+በዘመነ ሰማዕታት ክርስቲያኖች በግፍ ሲገደሉ ቅዱሱ
ሰው በበርሃ ውስጥ ነበር:: አንድ ቀን የእግዚአብሔር
መልአክ መጥቶ
ሰማዕት እንዲሆን መከረው:: እርሱም ነጭ በነጭ ለብሶ
አምሮበት ወደ ንጉሡ ሔደ:: በፊቱም ቀርቦ በክርስቶስ
ስም ታመነ::
ብዙ ጸዋትወ መከራም ተቀበለ::
+ንጉሡ (መኮንኑ) "አመጣጥህ ወደ ሞት ሳለ ምነው
እንዲህ እንደ ሠርገኛ ማጌጥህ?" ቢለው "እኛ
ክርስቲያኖች ትልቁ
ሠርጋችን ሞታችን ነው:: ልንሔድ ከክርስቶስም ጋር
ልንኖር እንናፍቃለንና" ብሎታል::
+ቅዱስ በብኑዳ ብዙ ተሰቃይቶ: ተአምራትን ሰርቶ በዚሕች
ቀን ተሰይፏል:: የጽድቅን አክሊል ከሰማዕትነት ጋር ደርቦ
አግኝቷል::
❖ቸሩ አምላክ ከሰማዕቱ በረከትን ያካፍለን::
❖ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ በብኑዳ (ሰማዕት ወጻድቅ)
2.ቅዱስ ቄርሎስ: ሚስቱና 12 ልጆቹ ሰማዕታት (ከቅዱስ
በብኑዳ ጋር የተገደሉ)
በ 20 የሚከበሩ ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
6.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት
++"+ በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን
ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ
ብጹዓን ናችሁ::
ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ:: አትናወጡም:: ዳሩ ግን
ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ
ስላለ ተስፋ
ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር
የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት
ይሁን:: +"+ (1ዼጥ.3:13-16)
>
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠 /ማቴ ፫:፫/
🔷ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!
❇️ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)❇️
" 🔶ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::🔸
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn