የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ሚዲያ ውስጥ አጀንዳ ፍሬሚንግ ወሳኝ ዘርፍ ነው። የተነሳህለትን አላማ በሚገባ ወደ ተከታይህ ለማስረጽ ከቃላት ጀምሮ እስከ ርዕሰ ጉዳይ በጥንቃቄ የምትመርጥበት መንገድ ነው። በሀገራችን ቋንቋ ከሚሰራጩ ሚዲያዎች ውስጥ የቢቢሲን አላማና የትኩረት ነጥብ ብዙ ሰው ያውቀዋል። ከስሙ ጀምሮ ብዙም ከማይለዩ አፍቃሬ ጽዮናውያን ሚዲያዎች መካከል ግን አል አይንን የሚወዳደር ያለ አይመስለኝም።

በሙስሊሙ አለም ዙሪያ የኢማራት አቋምና አላማ የሚታወቅ ቢሆንም ብዙውን ጊዜ ለተዛቡት መረጃዎች ግን በየሀገሩ ያሉ የተቀጣሪ ሰራተኞችን የግል እምነትና አመለካከትን ምክንያት ማድረግ እመርጥ ነበር። ዜናዎችን የመምረጥ፣ አጀንዳዎችን ፍሬም ማድረግ፣ ለዘገባ የሚወሰነውን የቃላት አጠቃቀም ወዘተ የሚዲያው ፖሊስ እንዳለ ሁኖ የሰራተኞችም የግል ፍላጎት ሊንጸባረቅበት ይችላል።

የጋዛው ኹነት ግን ከብዙው ሚዲያ ጀርባ ያለውን ፍላጎትና ማንነት ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል። ከግለሰቦቹ የግል አመለካከት በተጨማሪ እንደ ሚዲያ የቆመለትን አላማም ጭምር ይኸው መሆኑን ብዙ ሰው የተረዳ ይመስለኛል። ሚዲያዎቹ ሜንትስሪምና በብዙ በጀት የሚደጎሙ ቢሆንም እድሜ ለማኅበራዊ ሚዲያው በጥቂት አቅም የሚሰሩ ተኣማኒ ሚዲያዎች ተቀራራቢ ተደራሽነትን በመፍጠር እኩይ አላማቸውን ማሳየት ችለዋል። ዛሬ ትላንት አይደለም..!

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/Yahyanuhe


إلى رحمة الله ورضوانه

ለጅሀድ የተኖረ ሙሉ ህይወት፣ እስከ ፍጻሜው ድረስ..! ይህ ጋዛ ከከፈለቻቸው ውድ መስዋዕትነቶች ውስጥ ነው።

አላህ ይዘንላችሁ፣ ምትካችሁን ያበርክት።


በነገራችን ላይ ሰልዋን ሞሚካ በኢራቅ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው የክርስቲያን ሚሊሻ ቡድን መሪ ነበር። በሰራቸው አስከፊ ወንጀሎች ሳቢያ በህግ ሲፈለግ አምልጦ ስዊድን የገባ ሲሆን ጥገኝነት ቢጠይቅም ጥያቄው ተቀባይነት አላገኘም ነበር።

በስዊድን መንግስት ጥገኝነት ከተከለከለ በኃላ ይህንን ጥያቄየን ያሳካልኛል በሚል የቁርኣን ማቃጠል ስራ ውስጥ በስፋት መንቀሳቀስ ጀመረ። ተግባሩ የስዊድንን ዜግነት ባያስገኝለትም የጀሀነምን ግን አላሳጣውም..!


ቁርኣንን በአደባባይ በማቃጠል የሚታወቀው ኢራቃዊው ክርስቲያን ሰልዋን ሞሚካ በስዊድን በቲክቶክ የቀጥታ ስርጭት ላይ እያለ በተተኮሰበት ጥይት ተገድሏል።

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/Yahyanuhe


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
እስልምና ላይ የሚቀርቡ ጥያቄዎችንና በሀይማኖት ንጽጽር ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎችን ጥልቅ በሆነ መልኩ ስራዎችን ለመስራት እንዲያግዝ በማሰብ ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል በስሩ የጥናትና ምርምር ዘርፍ አቋቁሟል።

በዚህ ዘርፍ ውስጥ የንጽጽር ዱዓቶችን ጨምሮ ተተኪ ወንድምና እህቶች ሰፊ ጊዜዎችን በመውሰድ ስራዎችን እንዲያጠኑ፣ በየቋንቋቸው የጥናት ውጤታቸውን እንዲያዘጋጁ በማመቻቸት ላይ ይገኛል።

ለስራውም በአማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ አረብኛ እና እንግሊዝኛ የተጻፉ መጽሀፍትን ለማሟላት ጥረት እየተደረገ ሲሆን ለዚህ የሚያግዙ እናንተ ጋር የተቀመጡና ለተቋማችን ይጠቅማል የምትሏቸው መጽሀፍት ካሉ በሚከተለው ስልክ ቁጥር ለአስተባባሪዎች በመደወል መስጠት የምትችሉ ሲሆን ቢሮ መጥቶ መስጠት የሚችሉም ይበረታታሉ።

አድራሻ፦ ቤተል
ስልክ፦ 0910858830


በትግራይ የፋይናል ማጠቃለያ ቢጀመርም የአክሱም ሙስሊሞች መፈተን እንደማይችሉ ተነግሯቸው ከበር ተመልሰዋል። ይህ እምነትን መሠረት ያደረገ አድልኦ ብቻ አይደለም። የህዝብና የመንግስት መገልገያዎችን በእኩልነት እንዳይጠቀም አንድን የህብረተሰብ ክፍል በእምነቱ ምክንያት የመከልከል የአፓርታይድ ስርኣት ነው። ህዝቡ እኩል ግብር በሚከፈልበትና ተወልዶ ባደገበት ቀዮ "እኛ ከፍ ያልን ነን" ባሉ ጥቂት እቡዮች ሳቢያ ባይተዋር የተደረገበት አስቀያሚ ስርኣት ነው። በዚህ የግፍ ሒደት ውስጥ መታገል ከምትችሉት መጠን አፈግፍጋችሁ ከዳር ቁማችሁ በቸልታ የምታዩ "ባለኃላፊነቶች" ሁሉ የዚህ ግፍ ታሪክ አንዱ አካል መሆናችሁን ግን ለሰከንድም እንዳትዘነጉት..!


Forward from: ሒዳያ ንጽጽር /Hidaya Comparative/
ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ከጉረባዕ ኢስላማዊ ድርጅት ጋር በመተባበር ላለፉት 6 ሳምንታት ሲሰጥ የነበረው የአሰልጣኞች ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል። በስልጠናው መሠረታዊ የንጽጽር አስተምህሮ የተዳሰሰ ሲሆን በቀጣይ በትብብር ስለሚሰሩ ስራዎችም ውይይትና ስምምነት ላይ ተደርሷል። ማዕከሉ ከሌሎች ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጣቸው ስልጠናዎችም በአላህ ፍቃድ ተጠናክረው ይቀጥላሉ።

© ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል


ይህ ፕሮግራም ወደ ሰኞ ምሽት ተዛውሯል። በአላህ ፍቃድ በዚያው ቀን እንገናኝ። ባለማወቅ ፕሮግራም ያዛባንባችሁ ካለን ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን።


በቴሌግራም ቡት አማካኝነት ለላካችሁልን ጥያቄዎች ዛሬ ምሽት በአላህ ﷻ ፍቃድ መልስ መስጠት የምንጀምር ይሆናል። በቲክቶክ በወንድማችን ኢምራን ቤት ይጠብቁን..!

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/Yahyanuhe


📌 ዳዕዋ ቲቪ ከ2 ሺህ በላይ ደርሶች እና ፕሮግራሞች የነበሩት የዩቲዩብ ቻናል በመጠለፉ አዲስ የዩቲዩብ ቻናል ከፍቷል!

የዳዕዋ ቲቪ ቤተሰቦች ከ2ሺ በላይ የሚሆኑ የኪታብ ደርሶች፣ ፈትዋዎች እንዲሁም የሸይኽ ሙሐመድ ሓሚዲን የቁርአን ተፍሲርና የተለያዩ ኢስላማዊ እውቀትን የሚያስጨብጡ ትምህርቶችን ሲተላለፉበት የነበረው የዩቲዩብ ገፅ ማንነታቸው ባልታወቁ አካላት በመጠለፉ በምትኩ አዲስ ቻናል ተከፍቷል።

ስለሆነም እርስዎም ከዚህ በታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን አዲሱን የዳዕዋ ቲቪ የዩቲዩብ ገፅ ሰብስክራይብ እንዲያደርጉና ለሌሎችም እንዲያስተላልፉ ጥሪ ቀርቧል።
https://youtube.com/@daewatv1?si=AyREhvSL0jc-JgSn


የትግራይ ህዝበ ሙስሊምና መሪው የክልሉ መጅሊስ የሒጃብ ክልከላውን በተመለከተ ያደረጉት ትግል እጅግ የሚያኮራ ነው። የክልሉ መጅሊስ በዚህ ዙሪያ ያደረገው ትግል ቀላል አይደለም። እኛ ግን እህቶቻችን "ሒጃብ ይልበሱ" ብለን የምንጠይቅበት ዘመን ላይ ደርሰናል፣ ከከልካዮቹ አዳፋነት በላይ እንደ ግል ሁላችንም የሚያሸማቅቅ ነው..!


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ተቀባይነት ባለው ድርሳን ውስጥ አንድ ሙስሊም በሰይፍ ክርስቲያን ስለመደረጉ የሚተርከውን ምንባብ አስመልክቶ አጭር ቪዲዮ፦

https://vm.tiktok.com/ZMk9dNc9c/


ጺም ያሳደገ ሙስሊምን በክፋት ማየትና አለፍ ሲልም ካልተላጨ ከስራው አልያም ከትምህርቱ ማባረር የተለመደ ክስተት ነው። ይህ ተግባር በሌላው ቢደረግ ላይገርም ይችላል፣ መጽሀፋቸው ጺማቸውን እንዲያሳድጉ በሚያዛቸው ኦርቶዶክሶች ሲሆን ግን ያሳዝናል። አስቡት አንድ ሙስሊም ጸጉሯን የሸፈነች ካቶሊክን ጸጉሯን ካልገለጠች ብሎ ሲያሰቃያት..?! የኦርቶዶክስ ሰማንያ አሀዱ መጽሀፍ ቅዱስ በዚህ ዙሪያ ምን እንደሚል በዚህ አጭር ቪዲዮ አስቀምጨላችኃለው።

https://vm.tiktok.com/ZMkHvvwGs/


የስራ ሰው ብርቱ ናት፣ በጀመረችው ስራ ላይም ጽኑ ናት። ለተለያዩ ግልጋሎት የሚውሉ የወረቀት ዘንቢሎችን/Paper Bag/ ታዘጋጃለች። ለድርጅቶቻችሁና ለሱቃችሁ የምትፈልጉ ደውሉና እዘዟት፣ ካሻችሁ በባልሽ በኩል ነው የመጣነው በሉና ዋጋ አስቀንሱ 😀

📌 0910632233


Forward from: ሒዳያ ንጽጽር /Hidaya Comparative/
ወንድማችን ኡስታዝ ወሒድ ዑመር አዲሱን መጽሀፉን (አልገደሉትም፣ አልሰቀሉትም) ሶስት ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ እህቶች ወጭውን እንዲሸፍኑ በማስተባበር 100 መጽሀፍትን ለሒዳያ ላይብረሪ አስረክቦናል። በተጨማሪም በራሱ በኩል የእሱን መጽሀፍ የኦሮምኛ ትርጉም 100 ፍሬ የለገሰን ሲሆን ኡስታዝ ጀማል ደግሞ የአህመዲን ጀበልን "ክርስቶስ ማነው?" መጽሀፍ የኦሮምኛ ትርጉም ስራውን 100 ፍሬ አበርክቶልናል። እያንዳንዳቸው 100 መጽሀፍ በድምሩ 300 መጽሀፍትን ተለግሰውናል። አላህ ጀዛቸውን ይክፈላቸው፣ ከዚህ የበለጠ የሚተጉበትን ብርታትም ይወፍቃቸው።

© ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል

https://t.me/Hidayaic8212


እስልምና ላይ የሚቀርቡ ጥያቄዎችንና በሀይማኖት ንጽጽር ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎችን ጥልቅ በሆነ መልኩ ስራዎችን ለመስራት እንዲያግዝ በማሰብ ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል በስሩ የጥናትና ምርምር ዘርፍ አቋቁሟል።

በዚህ ዘርፍ ውስጥ የንጽጽር ዱዓቶችን ጨምሮ ተተኪ ወንድምና እህቶች ሰፊ ጊዜዎችን በመውሰድ ስራዎችን እንዲያጠኑ፣ በየቋንቋቸው የጥናት ውጤታቸውን እንዲያዘጋጁ በማመቻቸት ላይ ይገኛል።

ለስራውም በአማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ አረብኛ እና እንግሊዝኛ የተጻፉ መጽሀፍትን ለማሟላት ጥረት እየተደረገ ሲሆን ለዚህ የሚያግዙ እናንተ ጋር የተቀመጡና ለተቋማችን ይጠቅማል የምትሏቸው መጽሀፍት ካሉ በሚከተለው ስልክ ቁጥር ለአስተባባሪዎች በመደወል መስጠት የምትችሉ ሲሆን ቢሮ መጥቶ መስጠት የሚችሉም ይበረታታሉ።

አድራሻ፦ ቤተል
ስልክ፦ 0910858830


ከ464 የግፍ ቀናት በኃላ የጋዛ ንጹሀን ሰላማዊ ሌሊትን በአላህ ፍቃድ ዛሬ ምሽት ያሳልፋሉ። ሰማዕቶቻችሁን አላህ ይቀበል፣ ቅዋችሁንም የበለጠ ኃያል ያድርገው..!


አንዷ ፕሮቴስታንት ደግሞ የዛሬ አመት አካባቢ ካሊፎርኒያ ላይ እሳት ይታየኛል የሚል "የትንቢት ንግግር" ተናግራለች ብለው ፕሮቴስታንቶቹ በመደነቅ ሲያዘዋውሩት አየሁ። የካሊፎርኒያ ግዛት ማለት በየአመቱ እሳት የማይጠፋበት ግዛት ነው። ይህ የተለመደ ኹነት ከመሆኑ ጋር ትንበያ የሚፈልግም አይደለም። አስቡት "ሀገራችን ላይ የኑሮ ውድነቱ በሚቀጥለው አመት ካሁኑ ይብሳል" ብየ ተናግሬ የሚቀጥለው አመት ላይ ጠብቃችሁ በንግግሬ ስትደነቁ..!በሁሉም ነገር "አሜን" አትበሉ..!

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/Yahyanuhe


ከጅል ሰው ጋር መሟገት፣ ጅሎቹ ሁለት መሆናቸውን ከማረጋገጥ የዘለለ ፋይዳ የለውም።

https://t.me/Yahyanuhe


Forward from: አቡ ዩስራ - ንጽጽራዊ አስተምህሮ
ክርስቲያን የሆነ ሀኪም ብለህ የስራ ማስታወቂያ ከምታወጣ፣ የሆስፒታሉን ራዕይ፣ተልእኮ እና እሴቶች የሚቀበል ብለህ ታለዝበዋለህ።

ትርጉሙ ግን ያው ነው።

ምስሎቹን ይመልከቱ‼

https://t.me/Abuyusra3

20 last posts shown.