Jimma University በአባ ጅፋር ሃገር ላይ የሙስሊም ተማሪዎችን ድምፅ በማፈን ለማሸማቀቅ እየሄዳችሁት ያለውን ርቀት የማንሰማ እንዳይመስላችሁ።
ሰላማዊ የተማሪን ጥያቄ በተገቢው መልኩ መመለስ እንጂ ድምፅን ማፈንና ማሸማቀቅ ከባሰ አመፅና ሁከት ውጭ ሌላ ትርፍ የለውም።
አሁንም ጉዳዩ በውድም ሆነ በግድ መፈታቱ ላይቀር ነገር አላስፈላጊ መስዋዕትና እሰጣ ገባ ውስጥ ባትገቡ መልካም ነው።
እንደ አንድ የትምህርት ተቋም ሰላማዊ ጥያቄውን በተገቢው መልኩ በመመለስ አርዓያ መሆን ሲገባችሁ፤ እንደማንኛውም ጽንፈኛ እጅ በመጠምዘዝ ለሁከት ነጋሪት ጎሳሚ መሆናችሁ፤ ተቋሙ በስሩ የተሰገሰጉና ከጀርባው የሚዘውሩት ስውር እጆች እንዳሉ ያሳብቃል።
በቀላሉ መፈታት የሚችልን ነገር ዙሩን አታክሩት!
የአባ ጅፋር ልጆች በምድራችሁ ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ዩኒቨርስቲው እየፈፀመ ያለውን ነገር በቅርበት ተከታተሉ። ከጎናቸው ቁሙ።
ሳይቃጠል በቅጠል‼
Cc:
====
Ministry of Education Ethiopia
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
MuradTadesse
@islam_in_school