#የእመቤታችን_የስደት_ታሪክ_ክፍል_4
#ርዕስ ፦ ተአምረ ማርያም በምድረ ጋዛ
➯እመቤታችን ዮሴፍ እና ሰሎሜ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ሀገር ሲዘዋወሩ #ጋዛ ከተባለ ሀገር ደረሱ፡፡ በጋዛ የሚኖሩ ሰዎች እጅግ ክፉዎች ነበሩ፡፡ ዮሴፍ በጋዛ የሚኖሩትን ሰዎች እንዲሀ አላቸው። "በአገራችሁ ውሃ የለምን?" የጋዛ ሰዎችም እንዲህ አሉ "በሀገራችን ውሃ የለም ውሃ የምንቀዳበት ቦታ ርቀት በእግር 27 ቀን ይወስዳል፡፡ 27 ቀን ተጉዘን በግመል ጭነን አምጥተን ትንሽ ትንሽ እንጠጣለን አሉት።" የጋዛ ሰዎች ክፉዎች ስለሆኑ እንዲህ አሉ እንጂ በሀገራቸው ውሃ የሌለ ሆኖ አይደለም፡፡ የጋዛ ሰዎች ውሃ ከቀዱ በኋላ የውሃውን ጉድጓድ ዝግባ በተባለ ታላቅ እንጨት ይገጥሙታል፡፡ መንገደኞች ውሃ ሲጠይቋቸው ወይም ሲለምንዋቸው ውሃ የለንም ይላሉ፡፡ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ሕይወት ይሆን ዘንድ የፈጠረውን ውሃ የሚከለክሉ ጨካኞች ነበሩ፡፡
➯የውሃ ልመናው ያልተሳካለት ዮሴፍ እመቤታችንን እንዲህ አላት፡፡ በዚህ ሀገር የምንጠጣው ውሃ የለም፡፡ እመቤታችንም አተር የአሚወቁ የሚያበራዩ! ሰዎችን አየች። አተር ወደ ሚወቁት ሰዎች እንሂድና አተር ስጡን እንበላቸው አለችው ዮሴፍን እመቤታችን የጋዛን ሰዎች ጭካኔና ርኅራኄ ማወቅ ፈልጋለች ፡ አተር ወደሚያበራዩት / ወደሚወቁት ሰዎች ሄደው "ይህን ሕፃን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለራው ትንሽ አተር ስጡት ብለው ለመንዋቸው። የጋዛ ሰዎች ውሃ እያላቸው ውሃ የለንም እንዳሉ ሁሉ የአተሩን ልመናም አልተቀበለትም። ይልቁንም "ይህ የምታዩት አተር ሳይሆን ድንጋይ ነው" በማለት ቀለዱባቸው።"
➯ከዚህ በኋላ ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱን "እንደቃላችሁ ይሁንላችሁ በያቸው አላት፡፡" እመቤታችንም "እንደቃላችሁ ይሁን አለቻቸው።" ወዲያው የሚወቁት አተር ድንጋይ ሆነ፡፡ ውሃ እያላቸው ውሃ የለንም ስላሉ ውሃቸውም ደረቀ። አገራቸውም እህልን ዕፅዋትን የማያበቅል ደረቅ ሆነ። ምንጊዜም ቢሆን ለከፉ ሰዎች የተንኮላቸው ዋጋ ይከፈላቸዋል፡፡
➯ኢየሱስ ክረስቶስ ወንጌልን በሚያስተምርበት ጊዜ ተንኮለኞች በተንኮላቸው እንደሚጠፉ እንዲህ ሲል ተናግሯል ፡ "ወራት ይመጣብሻልና ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል ይከቡሻልም በየበኩሉም ያስጨንቁሻል" (ሉቃ 19፥43-44) ኢየሱስ ክርስቶስን ግብዞች ፈሪሳውያን ስለአሉባት ከተማ የተነገረ ቃል ነው። ኢየሱስ ክርስቶስን ሰቅለው የገደሉ የአይሁድ ከተማ ኢየሩሳሌም ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ በ10 ዘመን በሮማውያን ጠፍታለች።
https://t.me/Abalibanos333
#ክፍል_አምስት_ይቀጥላል.....
#ርዕስ ፦ ተአምረ ማርያም በምድረ ጋዛ
➯እመቤታችን ዮሴፍ እና ሰሎሜ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ሀገር ሲዘዋወሩ #ጋዛ ከተባለ ሀገር ደረሱ፡፡ በጋዛ የሚኖሩ ሰዎች እጅግ ክፉዎች ነበሩ፡፡ ዮሴፍ በጋዛ የሚኖሩትን ሰዎች እንዲሀ አላቸው። "በአገራችሁ ውሃ የለምን?" የጋዛ ሰዎችም እንዲህ አሉ "በሀገራችን ውሃ የለም ውሃ የምንቀዳበት ቦታ ርቀት በእግር 27 ቀን ይወስዳል፡፡ 27 ቀን ተጉዘን በግመል ጭነን አምጥተን ትንሽ ትንሽ እንጠጣለን አሉት።" የጋዛ ሰዎች ክፉዎች ስለሆኑ እንዲህ አሉ እንጂ በሀገራቸው ውሃ የሌለ ሆኖ አይደለም፡፡ የጋዛ ሰዎች ውሃ ከቀዱ በኋላ የውሃውን ጉድጓድ ዝግባ በተባለ ታላቅ እንጨት ይገጥሙታል፡፡ መንገደኞች ውሃ ሲጠይቋቸው ወይም ሲለምንዋቸው ውሃ የለንም ይላሉ፡፡ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ሕይወት ይሆን ዘንድ የፈጠረውን ውሃ የሚከለክሉ ጨካኞች ነበሩ፡፡
➯የውሃ ልመናው ያልተሳካለት ዮሴፍ እመቤታችንን እንዲህ አላት፡፡ በዚህ ሀገር የምንጠጣው ውሃ የለም፡፡ እመቤታችንም አተር የአሚወቁ የሚያበራዩ! ሰዎችን አየች። አተር ወደ ሚወቁት ሰዎች እንሂድና አተር ስጡን እንበላቸው አለችው ዮሴፍን እመቤታችን የጋዛን ሰዎች ጭካኔና ርኅራኄ ማወቅ ፈልጋለች ፡ አተር ወደሚያበራዩት / ወደሚወቁት ሰዎች ሄደው "ይህን ሕፃን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለራው ትንሽ አተር ስጡት ብለው ለመንዋቸው። የጋዛ ሰዎች ውሃ እያላቸው ውሃ የለንም እንዳሉ ሁሉ የአተሩን ልመናም አልተቀበለትም። ይልቁንም "ይህ የምታዩት አተር ሳይሆን ድንጋይ ነው" በማለት ቀለዱባቸው።"
➯ከዚህ በኋላ ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱን "እንደቃላችሁ ይሁንላችሁ በያቸው አላት፡፡" እመቤታችንም "እንደቃላችሁ ይሁን አለቻቸው።" ወዲያው የሚወቁት አተር ድንጋይ ሆነ፡፡ ውሃ እያላቸው ውሃ የለንም ስላሉ ውሃቸውም ደረቀ። አገራቸውም እህልን ዕፅዋትን የማያበቅል ደረቅ ሆነ። ምንጊዜም ቢሆን ለከፉ ሰዎች የተንኮላቸው ዋጋ ይከፈላቸዋል፡፡
➯ኢየሱስ ክረስቶስ ወንጌልን በሚያስተምርበት ጊዜ ተንኮለኞች በተንኮላቸው እንደሚጠፉ እንዲህ ሲል ተናግሯል ፡ "ወራት ይመጣብሻልና ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል ይከቡሻልም በየበኩሉም ያስጨንቁሻል" (ሉቃ 19፥43-44) ኢየሱስ ክርስቶስን ግብዞች ፈሪሳውያን ስለአሉባት ከተማ የተነገረ ቃል ነው። ኢየሱስ ክርስቶስን ሰቅለው የገደሉ የአይሁድ ከተማ ኢየሩሳሌም ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ በ10 ዘመን በሮማውያን ጠፍታለች።
https://t.me/Abalibanos333
#ክፍል_አምስት_ይቀጥላል.....