አዲስ ሪፖርተር - NEWS


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !
=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !
🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addis_reporter_bot
#ADDIS ABABA, ETHIOPIA

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


"ህውሃትን ከትግራይ ታግለን እናስወግዳለን"TPF

በነፃ መሬት የሚገኙ የትግራይ ሃይሎች ህውሃትን ታግለው ከክልሉ እንደሚያስወግዱ በገለፁበት የሰሞኑ ቃለ ምልልስ ሂደቱን ስረድተዋል።

ዛሬ በተሰማ መረጃ ደግሞ ከሃምሌ 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት 3 ቀናት ብቻ  689 በላይ የህወሃት ተዋጊዎች ካምፓቸውን ከድተው ወደ እነሱ ማለትም ወደ የትግራይ ሰላም ሰራዊት/TPF/ መቀላቀላቸውን ተናግረዋል። 

ወደ TPF የተቀላቀሉ ወታደሮች ቁጥር:-

1. ከአርሚ 24:  65 ወታደሮች
2. ከአርሚ 43:  57
3. ከአርሚ 44:  205
4. ከአርሚ 22:  34
5. ከአርሚ 26:  12
6. ከአርሚ 50:   31
7. ከአርሚ 60:   9
8. ከአርሚ 92:   86
9.ከአርሚ 15:    27
10.ከአርሚ 31:   22 ወታደሮች
11.ከአርሚ 33:   36
12.ከአርሚ 35:   19
13.ከአርሚ 42:   15 ወታደሮች
14.ከአርሚ 11:    26
15.ከአርሚ 13:-    7
16. ከአርሚ 17:    11
17. ከአርሚ 70 (ከሱዳንን ሸረሪና): 5 ወታደሮች
18. ከአርሚ 8: 13
19. 9 ወታደራዊ ኮማንድ በድምሩ 689 ተዋጊዎች ህወሃትን ከድተው ህወሃትን ለመታገል የተመሰረተውን የትግራይ ሰላም ሰራዊትን መቀላቀላቸው ታውቋል።

Via : sheger press

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የኤምሬትስ አየር መንገድ ከደንበኞቹ ክፍያ በክሪፕቶ ከረንሲ ሊቀበል ነው።

ግዙፉ የኤምሬትስ አየር መንገድ ክፍያ በክሪፕፖ መቀበል የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከCrypto. Com ጋር መፈራረሙ የተገለፀ ሲሆን በቀጣይ ዓመት ወደ ተግባር ይገባልም ተብሏል።

አየር መንገዱ የስምምነቱ በቴክኖሎጂ ለሚሳቡ ወጣቶች እና ክፍያን በዲጂታል የመገበያያ የገንዘብ አማራጮች መፈፀም ለሚፈልጉ ደንበኞችን ያገናዘበ ነው ብሏል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በአሁኑ ወቅት የዲጂታል መገበያያ ገንዘቦች ማዕከል ስትሆን የትምህርት ክፍያ፣ የትራንስፖርት እና የቤት ክፍያ በክሪፕቶከረንሲ እንዲከፈል ከዚህ በፊት መፍቀዷም ይታወሳል።

በአካባቢው ያሉ አየር መንገዶች ክሪፕቶከረንሲን እንደ አንድ የመገበያያ አማራጭ እየተቀበሉ ሲሆን ኤይር አረቢያም የጉዞ ትኬት ክፍያን በክሪፕቶከረንሲ መቀበል እንደሚጀምር ማስታወቁ ይታወሳል።

Source: Al Arabiya

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ሎሚ መጠጣት ለጤና ያለው ጥቅም‼️

ሎሚ የቫይታሚን ሲ ምንጭ ከመሆኑም በላይ ለሰውነታችን በርካታ የጤና ጥቅሞችን ይሰጣል። ከነዚህም ውስጥ ጥቂቶቹ:
* የበሽታ የመከላከል አቅምን ያጠናክራል፡ በቫይታሚን ሲ የበለፀገ በመሆኑ ሰውነታችንን ከጉንፋንና ከሌሎች በሽታዎች ይከላከላል።
* ክብደትን ለመቀነስ ይረዳል፡ ሎሚ በውስጡ pectin የተባለ ፋይበር ስላለው የረሃብ ስሜትን ይቀንሳል።
* ቆዳን ያድሳል፡ በሎሚ ውስጥ የሚገኘው አንቲኦክሲደንት (antioxidant) ቆዳችንን ከብጉርና ከሌሎች የቆዳ ችግሮች ይከላከላል።
* ምግብን ለማዋሃድ ይረዳል፡ ሎሚ የምግብ መፈጨት ሂደትን ያፋጥናል።
* ኩላሊት ጠጠርን ይከላከላል፡ ሎሚ በውስጡ ሲትሬት (citrate) ስላለው የኩላሊት ጠጠር እንዳይፈጠር ይከላከላል።

የሎሚ ጭማቂን በየቀኑ በመጠጣት ጤናማ ኑሮ ይኑሩ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


አሳዛኝ መረጃ‼️

በሰሜን ወሎ ፍላቂት ገረገራ የመድኃኔዓለም ገዳም የመሬት መንሸራተት አደጋ ደረሰበት!

በሰሜን ወሎ ዞን በፍላቂት ገረገራ ከተማ አስተዳደር፣ 02 ቀበሌ ገረገራ ከተማ የሚገኘው የ ገረገራ ቀራንዮ መድኃኔዓለም አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባ ሳሙኤል አንድነት ገዳም ከክረምት መግባት ጋር ተያይዞ የመሬት መንሸራተት አደጋ ደርሶበታል።

ይህ ህንፃ ቤተክርስቲያን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር በሚኖሩ ህዝበ ክርስቲያን ከፍተኛ ወጪና ጥራት ባለው መልኩ እየተገነባ ይገኛል።

ምዕመናን እና ካህናት በቀጣዩ 2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት ለማስመረቅ በጉጉት ሲጠባበቁ በነበረበት ወቅት፣ ያልተጠበቀው የመሬት መንሸራተት አደጋ ደርሶበታል።

የቤተክርስቲያኑ አሰሪ ኮሚቴ ይህንን አደጋ ለመታደግ ሁሉም አካል ርብርብ እንዲያደርግ አስቸኳይ ጥሪ አቅርቧል።

መረጃዉ ለብዙዎች እንዲደርስ እባካችሁ ሼር አድርጉት።

Via Meket Communication.

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ለአንዴ ውሃ ሽንት 20ብር‼️
ለአንድ ውሀ ሽንት ቫትን ጨምሮ 20 ብር‼️
አዲስ አበባ – የሽንት ቤት አገልግሎት ዋጋ ንረት የበርካቶችን ኪስ እያሳሰበ ነው። በአዲስ አበባ በተለይም በመርካቶ አካባቢ የሚገኙ ነጋዴዎች እና የህብረተሰብ ክፍሎች በቀን እስከ 100 ብር ለሽንት ቤት አገልግሎት እንደሚያወጡ እየገለጹ ነው።
አንዳንድ የሽንት ቤት አገልግሎት ሰጪዎች የዋጋ ጭማሪ በማድረግ አንዴ ለመሸናት 20 የኢትዮጵያ ብር (ከቫት ጋር) እያስከፈሉ ይገኛሉ።
ይህ የዋጋ ጭማሪ ብዙዎችን አስገርሟል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የሩሲያ ሩብል ከኢትዮጵያ ብር ጋር ያለው የምንዛሪ ተመን ይፋ ተደረገ

100 የኢትዮጵያ ብር በ57.5872 የሩሲያ ሩብል እንዲመነዘር ተመን ወጥቶለታል፡፡

የሁለቱ ሀገራት ገንዘቦች የእርስ በእርስ የምንዛሪ ተመን መቀመጡ በመካከላቸው ያለውን የንግድና ሌላውንም ልውውጦች በቀጥታ ለማከናወን እንዲችሉ ያደርጋቸዋል ተብሏል፡፡

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያ ብር የምንዛሪ ተመን ይፋ ሲያደርግ ለኢትዮጵያ ብር ኮድ 230 የመለያ ቁጥር ሰጥቷል፡፡

ከዚህ በኋላም የኢትዮጵያ ብር ከሩሲያ ሩብል ያለው የምንዛሪ ተመን በየጊዜው ማሻሻያ እየተደረገበት ይቀጥላል ተብሏል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


"የባሕር በር ካለህ ዓለም ሁሉ ገበያህ ነው"

የኢኮኖሚ ጫና ያለባቸው ሀገራት የባሕር በር አማራጭ ከሌላቸው በልማት ማነቆዎች የተጠፈነጉ እንደሚሆኑ የምጣኔ ሀብት እና የሕዝብ ፖሊሲ ፕሮፌሰር የሆኑት ፖል ኮሊየር ይገልፃሉ።

"የባሕር በር ካለ ዓለም ሁሉ ገበያህ ነው፤ ከሌለ ግን ከጥቂቶች ጋር ብቻ ትገበያያለህ" በማለት ሃሳባቸውን ያስቀምጣሉ፤ ይህንኑ ሃሳብም በርካቶች ይስማሙበታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "በቀይ ባሕር ዙሪያ ያሉ የጎረቤት ሀገራትን ሉዓላዊነት እናከብራለን፤ ነገር ግን ኢትዮጵያ ሉዓላዊ ሀገር ሆና እንድትቀጥል የባሕር በር እንደሚያስፈልጋት እነርሱም ሊያምኑ እና ሊያከብሩ ይገባል" ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው።

በታሪክ ብሎም በሕግ የባሕር በር አማራጭ የማግኘት መብት ያላት ኢትዮጵያ፣ ቀይ ባሕርን የማስተዳደር ተሳታፊነት ላይ ልትካተት ይገባል የሚሉት የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተመራማሪ አበራ ሃኢብሳ ናቸው።

ተመራማሪው ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ያለው መረጋጋት እና ሰላም ዘላቂ እንዲሆን በማድረግ ሂደት ውስጥ ኢትዮጵያ የባሕር በር አማራጭ እንድታገኝ መስራት አስፈላጊ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ያላትን ሀገር ቆልፎ ማቆየት አግባብ እንዳልሆነ በመግለፅ፤ ይህንንም ለማስቀረት የትውልዱን ጥያቄ ማስመለስ ይገባል ሲሉ ያስረዳሉ፡፡

የፖለቲካ ተመራማሪው አስራት ኤርሜሎ በበኩላቸው፤ በኢኮኖሚ ለመጠንከር ማምረት ብቻ ሳይሆን የተመረተውን ወደ ወጪ የገበያ ንግድ የሚቀርብበት አማራጭ ያስፈልጋል ይላሉ፡፡

አክለውም ሉዓላዊነትን በማጎልበት በባሕር በር ጉዳይ መነጋገርና እና ተጠቃሚነትን ማሳደግ አማራጭ የሌለው ምርጫ ነው ብለዋል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


"የትምህርት ቤቶች ግንባታ ምርጫ በዘርና ፖለቲካዊ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ የነበረ ቢሆንም ይህንን የሚያስቀር አሰራር ተዘርግቷል" - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ባለፉት ዓመታት በነበረው አሰራር የትምህርት ቤቶች ግንባታ ምርጫ የሚወሰነው በገለልተኝነትና በበቂ መረጃ ሳይሆን በዘር፣ በትውወቅና ፖለቲካዊ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ ነበር ሲሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው፣ ይህን ለማስቀረት የትምህርት ቤቶችን ሥርጭት የሚያሳይ የዲጂታል ካርታ አዘጋጅቷል ብለዋል፤ በአገሪቱ ተመጣጣኝና ፍትሃዊ የትምህርት ዘርፍ ልማትን ለማምጣት እየተሰራ ነው ሲሉም አስታወቀዋል።

በሀገሪቱ ተመጣጣኝ የሆነ የትምህርት ዘርፍ ልማትን ለማምጣት ትምህርት ቤቶች ግልጽና ትክክለኛ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ እንዲገነቡ የሚያስችል ዲጅታል የትምህርት ቤቶች ስርጭት የሚያሳይ ካርታ ተዘጋጅቷል ማለታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።አክለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዳለበት አንስተው ለሁሉም ዜጎች ትምህርትን በፍትሃዊነት ለማድረሰ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የትምህርት ቤቶች ስርጭት ካርታ ከቀበሌ ጀምሮ በየደረጃው የትምህርት ቤቶችን ወቅታዊ ስርጭት፣ የመሰረተ ልማት፣ የህዝብ ብዛት እና ሌሎች መረጃዎችንም አካቶ የያዘ መሆኑን ተጠቁሟል።በመሆኑም ለጋሾችም ሆኑ ሌሎች የዘርፉ ባለድርሻዎች መረጃውን በመጠቀም ትምህርት ቤቶችን መገንባትና የድርሻቸውን ማበርከት እንደሚችሉ ተገልጿል።በዚህ የትምህርት ስርጭት ካርታ ትምህርት ቤቶቹ የሚገነቡት በተዘጋጀው ስታንዳርድ መሰረት ሲሆን የት ይገነባሉ የሚለውን ምላሽ የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251967903299
     +251923782580

WhatsApp. +251967903299
Telegram :  0923782580


ዜና ዕረፍት ‼️

በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ የነበሩት የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ዶ/ር ምናሴ እሸቴ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል።

ዶክተር ምናሴ እድሜ ዘመናቸውን በደሴ ከተማ ለእናቶች እና ህፃናት ጤና ሲያገለግሉ የኖሩ ጠንካራ ሃኪም ነበሩ።ብዙዎች "መድሃኒቴ" ይሏቸዋል።ዶ/ር ምናሴ የግል የጤና ተቋም ከመመስረታቸው በፊት በመንግስት ሆስፒታል ጭምር በቅንነት ያገለገሉ እሳቸውን ለመግለፅ ቃል የሚታጣላቸው ምስጉን ሀኪም ነበሩ።

ከሞት የሚያመልጥ የለምና ዛሬ ሃምሌ 4/2017 አረፉ።አስክሬናቸው ወደ አዲስ አበባ እየመጣ ነው።ቤተሰብ እዚህ ስለሆነ ቀብራቸው አዲስ አበባ ይፈፀማል ተብሏል።ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው መፅናናቱን እመኛለሁ።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የሶሻል ሚዲያ ግብር‼️
መንግስት ሶሻል ሚዲያ ላይ ግብር ሊጥል ነው‼️

ዩቲዩብ ፣ ቲክቶክና ከሌሎች የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ሊጣል ነው

በኢትዮጵያ ለዘጠኝ ዓመታት ስራ ላይ የቆየውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ፣ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ለመጣል የሚያስችል ንዑስ አንቀጽ መካተቱ ታውቋል።

በታቀደው የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ መሰረት፣ ከማህበራዊ ሚዲያ የሚገኝ ገቢ (ለምሳሌ ከዩቲዩብ፣ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም፣ ቲክቶክ እና ሌሎችም መድረኮች) ፣ በኢንተርኔት ከሚሰራጩ መረጃዎች እንደሚሁም ከሚፈፀሙ ግብይቶች፣ ከስፖንሰርሺፕ እና ከመሳሰሉት የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ ግብር እንደሚጣልባቸው በዝርዝር ያስቀምጣል።

በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዉይይት እየተደረገበት የሚገኘዉ ይህ ረቂቅ አዋጅ ፤ እነዚህ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች በመደበኛነት የሚከናወኑ ከሆነ፣ የሚገኘው ገቢ በንግድ ስራ ገቢ ስር የሚመደብ ሲሆን፣ የንግድ ስራ ገቢ ግብርም የሚከፈልበት መሆኑን ይገልጻል።

ሆኖም፣ በአዋጁ የተቀመጡትን መስፈርቶች የማያሟላ ከሆነ፣ ገቢው “ሌሎች ገቢዎች” በሚለው ስር ተመድቦ ከጠቅላላ ገቢው ላይ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ግብር እንዲከፈልበት ይደረጋል ይላል።

ከዚህ በተጨማሪም፣ ለዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ክፍያ የሚያመቻቹ መድረኮች ለእያንዳንዱ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪ የተከፈለውን ገንዘብ የሚያሳይ ሪፖርት ለታክስ ባለስልጣኑ የመላክ ግዴታ እንደሚኖርባቸው ያስቀምጣል።

ይህን ተከትሎም፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የማውጣት፣ ገቢያቸውን የማስታወቅ እና ሌሎች የታክስ ከፋይ ግዴታዎችን የመወጣት ሃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው ያስገድዳል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ኤርትራ እና ግብፅ‼️
የኤርትራ እና የግብፅ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች የግብፅ የወደብ ከተማ በሆነችው ሻርም ኤል ሼክ/Sharm El sheikh/በቀይ ባህር ደህንነት ዙሪያ ወታደራዊ ትብብር ላይ ያተኮረ በቅርቡ ውይይት ሊያደርጉ መሆኑን ተሰምቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የተወደዳችሁ ቤተሰቦቼ

1.ለሀብት
2.ለገበያ ብዙ ደንበኛ እንዲኖረን
3.ለመስተፋቅር
4.ለማንኛውም በሽታ

የምንሰራው ጥበብ
============

5.ለሰብስብ
6. ለሰላቢ በሌላ አማርኛ ነገሮችን ለመሰወር
7.ለግርማ ሞገስ
8.ለትምህርት ዘኢያገድፍ
9.ለዐቃቤ ርዕስ ለመከላከያ
10.ሰው እንዲወደን ማድረግያ
11.ብልት ማሳደጊያ ዕፀ አብይ
12.ለስንፈተ ወሲብ
13.ለዐደበተ ርቱዕ ጥሩ ተናጋሪ እንድንሆን
14.ለቁመት መጨመርያ ዕፀ (ኤግኤል)
15.በግለ ወሲብ ለምትሰቃዩ ወይም በሴጋ
16.ለመልክ ውበት እንዲኖረን ማድረጊያ
17. ስራ እንድንቀጠር ማድረግያ
18.ፈተና አሪፍ ውጤት እንድናመጣ ማድረግያ
19.ለሴቶች ትልቅ ዳሌ እንዲኖረን ማድረግያ በዕፀዋት ብቻ
20.ፀጉር እንዲረዝም ማድረጊያ ..... ወዘተ
21.ለውፍረት
22.ለቅጥነት
23.ለስልጣን መጨመርያ
24.ለጥላ ወጊ
25.ለህዝብ ፍቅር
26.ብር እንዳይባክን ማድረግያ
27.ለገርጋሪ መንፈስ
28.ለቁማር
29.ደፋር ለመሆን
30. ትዳር ላይ ማትስማሙ እድትስማሙ ለማድረግ

እያንዳዱ ችግር እኛጋ መፍትሄ አለ
0952400019 ይደውሉልን።


መረጃ‼️

ግብፅ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ከኢትዮጵያ የጽሑፍ ስምምነት ጠየቀች!

የግብፅ መንግስት ኢትዮጵያ የታላቁን የህዳሴ ግድብ በተመለከተ የሰጠችውን የቃል ማረጋገጫ በጽሑፍ ስምምነት እንድታጠናክር በይፋ ጠይቋል።

ይህ ጥያቄ የመጣው የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ግድቡ በመስከረም ወር እንደሚመረቅ ከገለጹ በኋላ ነው።

ምን ተፈጠረ?

* የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ በቅርቡ ብራዚል ውስጥ በተካሄደው የብሪክስ ስብሰባ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል።

* በዚህ ስብሰባ ወቅት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ግድቡን "ግብፅንና ሱዳንን ሳይጎዳ" የማጠናቀቅ እና ትብብርን የመቀጠል ፍላጎታቸውን አረጋግጠው ነበር።

* ማድቡሊ እነዚህ የቃል ማረጋገጫዎች በሁለቱ ሀገራት ወይም በናይል ተፋሰስ ሀገራት መካከል ያለውን የወደፊት ግንኙነት በሚያደራጅ የጽሑፍ ሰነድ ውስጥ መካተት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

"የግብፅ አቋም በፍጹም አልተለወጠም፤ በአባይ ውሃ ድርሻዋ ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንዲደርስ አትፈቅድም" ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል። ግብፅ ልማትን ባትቃወምም፣ በአባይ ውሃ ላይ ያላትን ህጋዊ መብት እንደምትጠብቅም አስረድተዋል።

* ኢትዮጵያና ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ለረጅም ጊዜ አለመግባባት የነበራቸው ሲሆን፣ ግድቡን ስለመሙላትና ስለማስኬድ እስካሁን ስምምነት ላይ አልደረሱም።

* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፣ ግድቡ በመስከረም ወር እንደሚመረቅ እና ፕሮጀክቱ ለቀጠናው ትብብር "ዕድል" እንጂ "አደጋ" እንደማይሆን ገልጸዋል።

ከግብፅ ጋር ውይይት ለመቀጠልም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

* ከ2011 ጀምሮ በተደጋጋሚ በአፍሪካ ህብረት እና በአለም አቀፍ ሽምግልና ድርድሮች ቢደረጉም፣ ሦስቱ ተፋሰስ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ) በውሃ አያያዝ ላይ ህጋዊ አስገዳጅ ስምምነት ላይ መድረስ አልቻሉም።

Via : Capital

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የኬንያው ፕሬዚዳንት ፖሊሶቻቸው በተቃውሞ በወጡ ሰዎች እግር ላይ እንዲተኩሱ ትዕዛዝ ሰጡ።

ፕሬዚዳንቱ ውሳኔውን ያስተላለፉት ቢዝነሶችን የሚያስተጓጉሉ ተቃዋሚዎች ላይ ሲሆን የፀጥታ ኃይሎች እግራቸው ላይ እንዲተኩሱ ማዘዛቸው ነው የተነገረው።

በኬንያ ከሳምንታት በፊት የጀመረው ተቃውሞ ቀጥሎ እስካሁን ከ31 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።

ከሰኞ ጀምሮ በናይሮቢ አብዛኛው ሱቆች ዝግ ሆነው ቆይተዋል። በተቃውሞ ወቅትም ሱፐር ማርኬቶች እና ሆስፒታሎች መጎዳታቸውና መዘረፋቸው ተነግሯል።

ፕሬዚዳንት ሩቶ "የሰዎችን ንብረት የሚያቃጥል ሰው በጥይት እግሩ መመታት አለበት" ያሉ ሲሆን የፀጥታ ኃይሎቻቸው ሰዎችን እንዳይገድሉ አስጠንቅቀዋል።

ባለፈው ዓመት በኬንያ ከታክስ ጭማሪ ጋር ተያይዞ በርካቶች መሞታቸው የሚታወስ ሲሆን በዚህ ወር ደግሞ ታዋቂው ፀሐፊ በእስር ቤት ውስጥ መሞቱን ተከትሎ ተቃውሞ ዳግም መቀስቀሱ ይታወሳል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የሩሲያ ወታደራዊ ኃይል በዩክሬን ጊዜያዊ የሠራዊት የስምሪት ሥፍራ ላይ ጥቃት መፈጸሙን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ

ጥቃቱ የተፈጸመው በኢስካንደር ተንቀሳቃሽ የአጭር ርቀት ባላስቲክ ሚሳኤል ሥርዓት ነው።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


መተከል ዞን ዳግም በተቀሰቀሰ የጸጥታ ችግር አንድ ሰው ሲገደል ከሰባት በላይ ቤቶች በታጣቂዎች ተቃጠሉ

በቤኒሻንጉል_ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ከሚገኙ ሰባት ወረዳዎች መካከል አምስቱ ውስጥ ዳግም በተቀሰቀሰ የጸጥታ ችግር አንድ ሰው መገደሉ እና ከሰባት በላይ ቤቶች በታጣቂዎች መቃጠላቸውን ነዋሪዎችና በክልሉ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ አመራር ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁ ድባጤ ወረዳ ዶንቦን ቀበሌ ነዋሪ በአከባቢው ከግንቦት ወር ጀምሮ ጥቃቶች ሲፈጸም እንደነበረ ገልጸው፤ አብዛኛውን ጊዜ የወርቅ ነጋዴዎች እና ባለሀብቶች፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም የጸጥታ አካላት የጥቃቱ ኢላማ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ነዋሪው፤ በድባጤ ወረዳ ዶንቦን ቀበሌ እሁድ ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም  "የሸኔ ታጣቂዎች" ሲሉ የጠሯቸው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት ፈጸሙት ባሉት ጥቃት አንድ ሰው መገደሉንና "አስገድዶ መድፈር እና ዝርፊያ" መፈጸሙንም አመልክተዋል።

የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አመራር በበኩላቸው በክልሉ መተከል ዞን ውስጥ በሚገኙ ሶስት ወረዳዎች ማለትም ወንበራ፣ ቡለን እና ድባጤ ውስጥ "የሸኔ ታጣቂዎች"  በስፋት ይንቀሳቀሳሉ ብለዋል። ታጣቂዎቹ  እሁድ ዕለት በድባቴ ወረዳ ዶንቦን ቀበሌ ገብተው፤ "ዝርፊያ እና አሰቃቂ የሆነ አስገድዶ መድፈር ጥቃት" መፈጸማቸውን ጠቁመዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


አዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ‼️
ከሃምሌ ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠበቀው አዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ረቂቅ ከላይ ተያይዟል።
የገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጁ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ያለባቸውን የግብር ጫና መቀነስ አንዱ አላማው ቢሆንም፤ በውስጡ የያዛቸው ድንጋጌዎች ግን እሱን አንደማያመለክቱ እንደራሴዎች ተናግረዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁ በአለም ባንክ መስፈርት መሰረት የድሃ ድሃን የገቢ ግብር የሚያስከፍል ነው በሚል ተተችቷል፡፡

አንድ ሰው ከ30,000 ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ ማንኛውንም ነገር ከተገበያየ መቶ በመቶ እጥፍ ቅጣት እንዲከፍል የገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ ያስገድዳል፤ ይህም በፓርላማ ጥያቄ አስነስቷል፡፡

እንደራሴዎቹ በረቂቅ አዋጁ ላይ ትችት እና ቅሬታ ያቀረቡት ትናንት ከሰዓት በኋላ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት ባካሄዱበት ወቅት ነው፡፡

በረቂቅ አዋጁ ላይ ሀሳባቸውን የሰጡት አንድ የምክር ቤት አባል በማሻሻያው ላይ የቀረበው፤ ሰራተኛ ከሚያገኘው ወርሃዊ ደመወዝ ላይ ተቆራጭ የሚደረግበት መነሻ የግብር ምጣኔ ምንን መሰረት ተደርጎ እንደተወሰነ ለእኔ ግልጽ አልሆነልኝም ብለዋል፡፡

ቢያንስ በደመወዝ ማሻሻያው በተደረሰበት ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን 4570 ብር ያለውን ለምን ከታክስ ነጻ መደረግ እንዳልተቻለ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ ለምን ከ2000 በላይ የሚያገኙ ተቀጣሪ ሰራተኞች የገቢ ግብር እዲከፍሉ ተደረገ? ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ዝቅተኛ ገቢ ለሚያገኘው ሰራተኛ እኛ እና የገንዘብ ሚኒስቴር ነን እንጂ የምናስብለት ሌላ አካል ያለ አይመስለኝም ያሉት ተወካዩ ለምን የግብር መነሻ ከገንዝብ የመግዛት አቅም ጋር የሚመጣጠን አልሆነም? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ገቢ እንዳይቀርብን እንፈልጋለን ያሉት እንደራሴው ግን ገቢውን ማሳደግ ያለብን በዚህ መንገድ መሆን የለበትም ብለዋል፡፡

አስተዳደራዊ ክፍሉን በአግባቡ ከያዝን ማካካስ አይቻልም ወይ ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ ይሄ ነገር ቅሬታ ያስነሳብናል ይሄን እንዴት አይታችሁታል? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

መሆን የሚገባውን ነው ማድረግ ያልብን ያሉት የምክር ቤት አባሉ እኔ እያልኩ ያለሁት ዝቅተኛውም ሰው አይጎዳብን፣ የመንግስት ገቢም መቅረት የለበትም ነው ብለዋል፡፡ 

አቶ ወንደሰን አድማሴ የተባሉ ሌላ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ግብር መክፈል ያለበት ማነው? የሚል ጥያቄ ከጠየቁ በኋላ የድሃ ድሃ ወይም ( #Absolute_Poverty ) ውስጥ ያለ ሰው ግብር መክፈል አለበት ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

እ.ኤ.አ በ2022 በአለም ባንክ በተሰራ ጥናት አንድ ሰው በቀን ከ2.15 ዶላር በታች የሚያገኝ ከሆነ ድሃ እንደሆነ ያሳያል ያሉት አቶ ወንደሰን፤ የኢትዮጵያውን ግን አሁን ባለው የምንዛሪ ተመን ከዚያ ከፍ ያለ ስለ ሆነ absolute poverty ውስጥ ያለ ሰው ግብር መገበር አለበት ወይ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ሌላው የምክር ቤት አባሉ እና ቋሚ ኮሚቴው የጠየቀው ጥያቄ በጥሬ ገንዘብ ግብይት ላይ የተጣለውን ገደብ የተመለከተ ነው፡፡

በማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ መሰረት ከ30,000 ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ የሚደረግ ግብይትን የሚከለክል ሲሆን ሲገበያይ የተገኘ ሰው ደግሞ የከፈለውን ገንዘብ በእጥፍ እንዲከፍል ያስገድዳል፡፡

Via :- Sheger fm

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251967903299
     +251923782580

WhatsApp. +251967903299
Telegram :  0923782580

20 last posts shown.