አዲስ ሪፖርተር - NEWS


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !
=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !
🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addis_reporter_bot
#ADDIS ABABA, ETHIOPIA


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


መንግስት በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች እየተፈጸሙ ላሉት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በቂ ትኩረት አልሰጠም!

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ ) የተሰጠ መግለጫ;

መስከረም 17/2016 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት የጸጥታ አካላትና በታጠቁ ሀይሎች የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ዘርፈ ብዙ የሆነ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን እያስከተሉ በመሆናቸው መፍትሔ እንዲያገኙ በተከታታይ ጋዜጣዊ መግለጫዎችን በማውጣት
የሚመለከታቸው አካላት መፍትሄ እንዲሰጡት ሲያሳስብ ቢቆይም ችግሩ ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ ዜጎች ከፍተኛ ለሆነ የሰው ህይወት መጥፋት፣ የአካል ጉዳት፣የንብረት ዝርፊያና መውደም ፤ ለእገታና መፈናቀል እየተዳረጉ ይገኛሉ፡፡

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ ወረዳ ኤጀሬ ቀበሌ በቀን 02/01/16ዓ.ም በታጣቂዎች በተፈጸመ
ጥቃት የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ 4 ሰዎች መገደላቸውን እና በኪራሙ ወረዳ በቀን 02/01/16 የአንድ ሰው
ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰው መቁሰሉን እንዲሁም በቀን 04/01/16 ወደ ጊዳ ከተማ ይጓዙ የነበሩተሳፋሪዎችን የታጠቁ ኃይሎች መንገድ ላይ አዉርደው ወንዶችን በመለየት "ጋራ ዲቾ"(ዲቾ ዳገት) በሚባል
ቦታ በርካታ ሰዎች መግደላቸውንና ማቁሰላቸውን በተመሳሳይ በቄለም ወለጋ ዞን አንፍሎ ወረዳ ሱዲ
ቀበሌ በቀን 27/12/15ዓ.ም በመንግስት የጸጥታ አካላት በተፈጸመ ጥቃት የሰው ህይወት ማለፉን እና
የአካል ጉዳት መድረሱን ኢሰመጉ ከአካባቢው ባገኘው መረጃ ለማወቅ የቻለ ሲሆን ኢሰመጉ ስለጉዳዩ መረጃ
እንዲሰጠው የምስራቅ ወለጋ ዞን ፖሊስ መምሪያ፣ የአስተዳደርና ጸጥታ እና የሚሊሻ ዘርፍ በቀን
11/1/2016ዓ.ም በደብዳቤ ቁጥር GMNIDL 01-348/14 የጠየቀ ሲሆን የምሰራቅ ወለጋ ዞን ኃላፊ የሰውህይወት መጥፋቱንና የአካል ጉዳት መድረሱን ትክክለኛነት በቃል ያረጋገጡ ቢሆንም መረጃውን ግን
በደብዳቤ መስጠት እንደማይችሉ ገልጸዋል፡፡

ተያያዥ የህግ ግዴታዎች፡
ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች መግለጫ (UDHR) አንቀጽ 3፣ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ
ቃል-ኪዳንም (ICCPR) በአንቀጽ 6(1) እና 9(1) ላይ እያንዳንዱ ሰው በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነቱ
የመጠበቅ መብት እንዳለው ያረጋግጣል።

ይህንኑ መብት በማረጋገጥ፣ መንግሥታት በቃል-ኪዳኑ (ICPR) የተረጋገጡትን መብቶች በግዛታቸው የማክበር፣ የማስከበርና የማሟላት ግዴታ እንዳለባቸውም በአንቀጽ
2(1) እና 2(2) ይደነግጋል።

የአፍሪካ ቻርተር በሰዎች እና ህዝቦች መብቶች (ACHPR) አንቀጽ 4 ማንኛውም ግለሰብ በሕይወት የመኖር መብቱና የአካሉ ደህንነት መብቱ ሊከበርለትና ሊጠበቅለት እንደሚገባና እነዚህን መብቶቹን በዘፈቀደ ሊነፈግ እንደማይችል ተመላክቷል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 14 “ማንኛውም
ሰው ሰብዓዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሰስ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነትና የነጻነት መብት አለው”
ሲል ይደነግጋል።

በተመሳሳይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 15 ማንኛውም ሰው በሕይወት የመኖር
መብት እንዳለውና በሕግ ከተደነገገው ውጪ ሕይወቱን ሊያጣ እንደማይችል በግልፅ ደንግጓል፡፡

በተመሳሳይ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት በአንቀጽ 16 ላይ ማንም ሰው በአካሉ ላይ ጉዳት እንዳይደርስበት የመጠበቅ
መብት አለው ሲል ያስቀምጣል፡፡

የኢሰመጉ ጥሪ፡
 የኦሮሚያ ክልል መንግስት በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት የጸጥታ አካላትና በታጠቁ
ኃይሎች በንጹሃን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ዘርፈ ብዙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በአስቸኳይ
እንዲያስቆም፣

 መንግስት የዜጎቹን የሰብዓዊ መብቶች የማስከበር ሀላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ፣

 የፌደራል እና የኦሮምያ ክልል መንግስታት በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ማህበረሰቦች በነጻነት ተንቀሳቅሰው የእለት ተግባራቸውን እንዲፈጽሙ እና በሰላም ወጥተው እንዲገቡ ዜጎችን የመጠበቅ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ፣

 በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በተደጋጋሚ በመንግስት የጸጥታ አካላት እና የታጠቁ ኃይሎች በሚፈጸሙ ጥቃቶች ውስጥ እጃቸው ያለበትን አካላት መንግስት በህግ አግባብ ተጠያቂ እንዲያደርግ ኢሰመጉ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ላዳ መኪኖች በኢትዮጵያ ሊመረቱ ነው

የሩሲያዎቹን ላዳ መኪኖች በኢትዮጵያ ለማምረትና ለአፍሪካ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ሥምምነት መደረሱን ታስ የተሰኘው የሩሲያ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡

ከስምምነት ላይ የደረሰው አቭቶቫዝ የተሰኘው መንግስታዊው የቤት መኪና አምራች ኩባንያ መሆኑ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረቱት ላዳ መኪኖች÷ ሱዳንን፣ ደቡብ ሱዳንን እንዲሁም ኬንያን እና ሶማሊያን ጨምሮ ወደ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ይላካሉም ተብሏል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


Ethiopian Airline Jobs 2023💯✔️
---—----------------------------     
♨️ እንኳን ደስ አላችሁ ለመላው ለስራ ፈላጊ ኢትዮጲያዊያን!

✅ ከ 5,000- በላይ ክፍት ቦታዎች በ0 አመት  እና በልምድ

✅ Number of Positions: 5,000+     positions 0 EXP and with Exp

🔺የትምህርት ደረጃ: በሁሉም የትምህርት ደረጃ
🔺የትምህርት አይነት: በተለያዩ ዲፓርትመንቶች
🔺ቦታ: በሁሉም የኢትዮጲያ ከተማዎች
🔺የስራ ልምድ: በ 0 ዓመትና በልምድ
🔺 የቅጥር ሁኔታ: በቋሚ ቅጥር
🔺 ብዛት: ከ5,000+ በላይ
🔺ደሞዝ:  ማራኪ

🟥 ፈጥነው ታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ

⁉️ ማሳሰቢያ:- VPN ወይም Psiphon መጠቀም ይኖርባችሗል

👇👇👇👇👇Apply Now👇👇👇👇👇👇
                        👇👇👇👇         
https://addiszemenvacancy.com/2023/08/21/ethiopian-airlines-job-vacancy-5000-vacancies-for-fresh-graduates/


--------Follow Our Website--------
                     👇👇👇👇👇👇
         https://addiszemenvacancy.com


ሰላም ጤና ይስጥልኝ ኑሮ የጨለመባችሁ መፍትሔ አለን የምንሠጣቸው አገልግሎቶች 0938234097
1 ,ለባል እና ሌሎች ማህበረሰብ የሚያዋድድ
2 ,ለህመም
3, ለሀብት
4, ለገበያ
5,ለሥራ
6,ለአጋንንት
7 ,ለግርሜ ሞገስ
8 ,ለብልት
9,ለበረከት
10 ,ለኤችአይቪ ፈዋሽ መድሀኒት
11 ,ለጠላት
12 ,ለጭንቀት
13 ,ለዕድል
14 ,በግብረ ስጋ ግንኙነት ጥሩ እና ያማረ ስሜት እንድኖር
15 ,ብር እንዳይባክን
16,ለእጅ ስራ እንዲቀናህ
17,ከትንሽ እስከ ትልቅ ህመ
18,ለግርማ ሞገስ
    19.ትዳር አስማም ቶ የሚያኖር                   
     20,   ለረደት በረከት ሰርቶ ገንዘብ አልበረክት ላለበት                    
21,ሌባ ጠላት የመሳሠሉ ከባድ ፈተና እንዳይደፍርህ ለአገልግሎት ይደውሉ እያንዳንዱ ችግር እኛጋ መፍትሄ አለ የባህል መድህኒት ፈውስ  የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል
☟☟☟☟☟ ☟☟☟☟☟

☞  ለመፍትሄ ሀብት
☞  ለህመም
☞  ለመስተፋቅር
☞  ቡዳ ለበላው
☞  ለገበያ
☞  ሚስጥር የሚነግር
☞  ለቀለም(ለትምህርት)
☞  ለመፍትሔ ስራይ
☞  ፍቅረኛ ላጣ ወይም ላጣች የሚሰራ
☞  ሌባ የማያስነካ
☞  ለበረከት
☞  ለጠላት (ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ)
☞  ለግርማ ሞገስ
☞  መርበቡተ ሰለሞን
☞  ለዓይነ ጥላ
☞  ለሁሉ መስተፋቅር
☞  ጸሎተ ዕለታት
☞  ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
☞  ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
☞  ለትዳር
☞  ለድምፅ
ይደውሉ መፍትሄ አለን
🌿🌿🌿🌿🌿🌿
           0938234097


በትግራይ ክልል በ27 ወረዳዎች አስከፊ ድርቅ መከሰቱ ተገለጸ

በትግራይ ክልል በሦስት ዞኖች በሚገኙ 27 ወረዳዎች እና ከ180 በላይ በሚሆኑ ቀበሌዎች ድርቅ መከሰቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል፡፡

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ሚካኤለ ብሩክ፤ "በክልሉ በሦሰት ዞኖች በሚገኙ 27 ወረዳዎች እንዲሁም ከ180 በላይ ወረዳዎች ላይ አስከፊ ድርቅ በመከሰቱ ሰብሎች እየወደሙ ነው።" ብለዋል፡፡

"በክልሉ ምስራቃዊ፣ ደቡብ ምስራቅ እና ደቡባዊ አካባቢዎች በተያዘው የክረምት ወቅት ዝናብ ባለመዝነቡ ተዘርቶ የነበረ ሰብል በመውደሙ እና በርካታ ሄክታር መሬት ሳይዘራ በመቅረቱ አርሶአደሮች ችግር ላይ ወድቀዋል።" ሲሉ ነው የገለጹት፡፡

ለአብነትም በምስራቃዊ የትግራይ ዞን ጨርጨር፣ ጸኣዳ አምባ፣ ጽራአወምበርታ እና ሌሎች አካባቢዎች ከ4 ሺሕ 400 ሄክታር መሬት በላይ ሰብል ወድሟል ብለዋል፡፡

እንዲሁም በድርቅ ከተጠቁ ከ180 በላይ ቀበሌዎች ውስጥ ምንም ዓይነት ዘር ያልተዘራባቸው መኖራቸውን ጠቅሰው፤ "በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ጤፍ፣ ማሽላ እና ባቄላ ተዘርቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ሁሉም ሰብል ወድሟል።" ነው ያሉት።

"በክልሉ በአጠቃላይ ምን ያክል ሄክታር መሬት እንደወደመ ለማወቅ ጥናት እየተደረገ ነው።" ያሉት ዳይሬክተሩ፤ "በድርቁ አማካኝነት ሰብላቸው የወደመባቸው አርሶአደሮች በቀላል ዝናብ እና በአጭር ጊዜ ሊደረሱ የሚችሉ እንደ ሽንብራ፣ ገብስና የመሳሰሉ አዝረቶችን እየዘሩ ነው።" ብለዋል።

አክለውም፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ የቤት እንስሳት መሞታቸውን ጠቁመው፤ በሕይወት ያሉትንም የተሻለ የዝናብ መጠን ወዳለባቸው አካባቢዎች የማሸሽ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


Via :አዲስ ማለዳ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


አቦል Fm

አቦል Fm መረጃዎችን ከማድረስ በተጨማሪ በማህበረሰብ  ዉስጥ ያሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ፣ የሙስና ወንጀሎች ፣ የወንጀል ድርጊቶች ፣ ለበርካታ ዓመታት መሰራት የነበረበት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ትኩረት ካልተደረገባቸዉ እና በአጠቃላይ የሚዲያ ሽፋን ማግኘት ይኖርባታል የሚባሉ ጉዳዮችን ትኩረት በማድረግ ለመስራት የተቋቋመ ሚዲያ ነው።ሰብስክራይብ ላይክ ሼር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://youtube.com/@abolnews605?si=DSdcIbqfWRjB-ERW


በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያዎች ከ3 ሺሕ 500 በላይ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አለማግኘታቸው ተገለጸ

በደብረ ብርሃን ከተማ በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች አንዱ በሆነው ቻይና ካምፕ እስከ 3 ሺሕ የሚደርሱ ተማሪዎች የደብተር፣ ቦርሳና እስክብሪቶ ድጋፍ እንዳልተደረገላቸው የቻይና ካምፕ ኮሞቴ ጸሃፊ ንጉሴ ዉበቱ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።

በዚህም ምክንያት ተማሪዎች ትምህርታቸውን መከታተል እንደማይችሉ ነው የጠቆሙት።

በቻይና ካምፕ ኹለት ዓመታት የቆዩ እና ባለቤታቸው የት እንዳሉ አላውቅም ያሉ የኹለት ልጆች እናት፤ "ለልጄ ደብተር መግዛት የምችልበት አቅም የለኝም። ልጄ ግን እንዲማርልኝ እፈልጋለው ብቸኛው ተስፋው ትምህርት ነው።" ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

የኮሚቴው ጸሃፊ "እነዚህ ልጆች ትምህርታቸውን መማር የሚችሉበት መንገድ ሊመቻችላቸው ይገባል።" ሲሉ ገልጸው፤ የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

በተመሳሳይም 4 ሺሕ 123 ተፈናቃዮች ባሉበት ባቄሎ ካምፕ 860 የሚሆኑ ከሦስተኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል እንዲሁም ከ150 በላይ የሚሆኑ የዘጠነኛ እና የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች የተመዘገቡ ቢሆንም፤ ምንም ዓይነት የትምህርት መገልገያ ቁሳቁስ የላቸውም ሲሉ የመጠለያ ጣቢያው ኮሚቴ አስተባባሪ እሸቴ ሙላቱ ገልጸዋል።

ከግለሰብም ሆነ ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች ምንም ዓይነት የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አልተደረገም ያሉት አስተባባሪው፤ ቤተሰቦቻቸው ምንድነው የምናደርገው የሚል ተደጋጋሚ ጥያቄ እያነሱ ነው ብለዋል።

በከተማዋ ባሉ መጠለያ ጣቢያዎች የሚኖሩ የኹለተኛ ደረጃ ተማሪዎችም ለመማር የተመዘገቡት ከአካቢያቸው ራቅ ያለ ቦታ በመሆኑ የትራንስፖርት እና የቤት ኪራይ ችግር ስላጋጠማቸው ትምህርታቸውን ከማቋረጣቸው በፊት አስፈላጊው እገዛ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።

አዲስ ማለዳ የዞኑን ትምህርት መምሪያ በጉዳይ ላይ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ጥረት ብታደርግም ሳይሳካ ቀርቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ለመላው ኢትዮጵያውያን የእስልም እና የክርስትና ዕምነት ተከታዮች  እንኳን ለ1498ኛው የመውሊድ በአል ☪️ እና ✝️ ለደመራ በአል አደረሳቹ በማለት መልካም በዓል እንዲሆንላቹ ተመኘን።
✝️🤝☪️   ✝️🤝☪️  ✝️🤝☪️


ግለሰቦቹ ወደ ማረሚያ ቤት ወርደዋል‼

የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በማቅረብ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አምቦ ዲስትሪክት የስራ ቅጥር ፈጽመዋል የተባሉ ግለሰቦች ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ አዘዘ።

የኦሮሚያ ክልል ፍትህ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ተከሳሾቹ የሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ድንጋጌን ተላልፈዋል በማለት ሀሰተኛ መንግስታዊ ወይም ህዝባዊ ሰነዶችን አዘጋጅቶ በመጠቀም የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦባቸዋል።

ተከሳሾቹ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አምቦ ዲስትሪክት በወጣ የስራ ማስታወቂያ የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ማስረጃ በማቅረብ የስራ ቅጥር ውል ስምምነት መፈጸማቸው በክሱ ተጠቅሷል።

ተከሳሾቹ 12 ሲሆኑ 10 ሩ የቅጥር ውል ከፈጸሙ በኋላ ለ10 ወራት በየደረጃው በተለያየ መጠን ወርኃዊ ደመወዝ መውሰዳቸውን ነው  ዐቃቤ ሕግ በክሱ ያመላከተው።

ቀሪዎቹ ሁለት ተከሳሾች ደግሞ የስራ ቅጥር ውል ስምምነት ከፈጸሙ በኋላ  የማስረጃ ማጣራት ስራ ሲጀመር መሰወራቸውን ነው ዐቃቤ ሕግ በክሱ ያመላከተው።

በዚህም ዐቃቤ ሕግ ያቀረበባቸው ሀሰተኛ መንግስታዊ ወይም ህዝባዊ ሰነዶችን አዘጋጅቶ መጠቀም የሙስና ወንጀል ክስ ዝርዝር ለ 10 ግለሰቦች በችሎት እንዲደርሳቸው ተደርጓል።

የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ በነበረው ቀጠሮ በችሎት የቀረቡት 10 ተከሳሾች ማረሚያ ቤት እንዲወርዱና ቀሪ ሁለት ተከሳሾችን ደግሞ የኦሮሚያ ፖሊስ አፈላልጎ በቀጣይ ቀጠሮ እንዲያቀርባቸው አዟል።

የተከሳሾችን የዕምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ለጥቅምት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ መያዙም ተገልጿል፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ልማት ባንክ ከ20 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ለመስጠት መዘጋጀቱን ገለጸ!

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ2016 በጀት ዓመት ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ከ20 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ለመስጠት ዕቅድ መያዙን አስታወቀ።የባንኩ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር የአብሥራ ከበደ÷ ካለፉት ሦስት ዓመታት ጀምሮ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲፈጠሩ ባንኩ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በእውቀትና ክህሎት የሚመሩ ጠንካራ ኢንተርፕራይዞች እንዲፈጠሩ ተከታታይ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸው፤ ባለፉት አራት ዙር ሥልጠናዎችም 133 ሺህ ዜጎች መሳተፋቸውን ጠቅሰዋል።ሥልጠናውን ለመውሰድ ተመዝግበው ከሚጠባበቁ 320 ሺህ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች መካከል በበጀት ዓመቱ እስከ 75 በመቶ ያህሉን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን አብራርተዋል።

ሥልጠና የወሰዱ የብድር አገልግሎት ፈላጊ ዜጎችም የገበያ አዋጭነት ሃሳባቸውን ለባንኩ ማቅረብ እንዳለባቸው የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፤ ባንኩ ብድር በመስጠት ሥራቸውን እንዲጀምሩ ይሰራል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በኢንተርፕራይዝ የተደራጁ አንቀሳቃሾች 20 ከመቶ የስራ ማሟላት ያለባቸው ሲሆን÷ ባንኩ የቴክኒክና የምክር አገልግሎትን ጨምሮ 80 ከመቶ ብድር እንደሚያቀርብ አረጋግጠዋል።እስካሁን ስልጠናውን ተከታትለው የንግድ እቅዳቸውን ላቀረቡ ዜጎች 20 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ብድር ባንኩ መስጠቱንም ጠቅሰዋል።

በ2016 በጀት ዓመትም የባንኩን ስልጥና በአግባቡ ለተከታተሉና ዝርዝር የንግድ ስራ እቅድ ለሚያቀርቡ ኢንተርፕራይዞች 20 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ብድር ለመስጠት መታቀዱን ይፋ አድርገዋል።የባንኩ የፋይናነስ አካታችነትን ለማረጋገጥ አማራጮችን እያሰፋ መሆኑን ገልጸው፤ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ለሚጠቀሙ ዜጎች የብድር አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀመርም ጠቁመዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


በወይዘሪት ዚምባቡዌ ውድድር ነጭ የቆዳ ቀለም ያላት ቆንጆ ማሸነፏ ተቃውሞ አስነሳ

በሀረሬ ተወልዳ ያደገችው “ወይዘሪት ዚምባቡዌ” በአለም የቁንጅና ውድድር ሀገሯን ወክላ ትሳተፋለች
የ21 አመቷ ብሮክ ጃክሰን በዚምባቡዌ የተካሄደውን የቁንጅና ውድድር አሸንፋለች።
ከ22 አመት በተካሄደው ውድድር ከ10ሩም የዚምባቡዌ ግዛቶችና የሀገሪቱን ዲያስፖራ ማህበረሰብ የወከሉ 25 ቆነጃጅት በተሳተፉበት ውድድር በመዲናዋ ሀረሬ ተወልዳ ያደገችው ብሮክ ማሸነፏ አነጋጋሪ ሆኗል።
አሸናፊዋ በቀጣይ በሚካሄደው የአለም የቁንጅና ውድድር ዚምባቡዌን እንድትወክል መመረጧ ተገቢነት የሌለው ነው የሚሉ ተቃውሞች የተደመጡት ብሮክ የቆዳ ቀለሟ ነጭ በመሆኑ ነው።

አብዛኛውን የዚምባቡዌ ህዝብ የሚወክል የቆዳ ቀለም ሳይኖራት የአፍሪካዊቷን ሀገር ወክላ በአለማቀፍ መድረክ መሳተፍ የለባትም የሚሉ ተቃውሞዎችም በማህበራዊ ሚዲያዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ።
ብሮክ ያሸነፈችው የተለየ ውበት ስላላት ሳይሆን ነጭ በመሆኗ ነው ያሉ አስተያየት ሰጪዎች የውድድሩ ውጤት እንዲሰረዝ እየጠየቁ ነው።
“አውሮፓዊት እንስት የጥቁሮች የቁንጅና ውድድር አሸነፈች” እስከማለት የደረሰ ተቃውሟቸውን ያሰሙ አስተያየት ሰጪዎችም አሉ።
“ጥቁር ህዝቦች በራሳቸው የቆዳ ቀለም እንዲኮሩና ራሳቸውን እንዲያከብሩ አሸናፊዋን (ብሮክ) ወደ አለም ቁንጅና ውድድር ባለመላክ አስተማሪ ተግባር መከወን ይገባል” ብሏል አንድ አስተያየት ሰጪ።
ብሮክ ነጭ የቆዳ ቀለም ኖሯት በቁንጅና ውድድር አሸናፊ የሆነች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት አይደለችም። 
በደቡብ አፍሪካም በዚህ አመት በተደረገ ተመሳሳይ ውድድር ያሸነፈችው ነጭ የቆዳ ቀለም ያላት እንስት ናት።
የዚምባቡዌዋ ብሮክ ጃክሰን ከ25 ተወዳዳሪዎች ብቸኛዋ ነጭ ሆና የማሸነፏ ዜና ግን በርካቶችን ለጥርጣሬ ዳርጓል።
ብሮክ ከዚምባቡዌ ቴሌቪዥን ጋር ባደረገችው ቆይታ "በቆዳ ቀለም ምክንያት ማንም ተጽዕኖ ሊያደርግብኝ አይገባም፤ ሁላችንም አንድ ነው፤ ሀገሬን በአለማቀፍ መድረክ ወክዬ የተሻለ ውጤት ለማምጣት እሞክራለው" ብላለች።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter




Ethiopian Airline Jobs 2023💯✔️
---—----------------------------     
♨️ እንኳን ደስ አላችሁ ለመላው ለስራ ፈላጊ ኢትዮጲያዊያን!

✅ ከ 5,000- በላይ ክፍት ቦታዎች በ0 አመት  እና በልምድ

✅ Number of Positions: 5,000+     positions 0 EXP and with Exp

🔺የትምህርት ደረጃ: በሁሉም የትምህርት ደረጃ
🔺የትምህርት አይነት: በተለያዩ ዲፓርትመንቶች
🔺ቦታ: በሁሉም የኢትዮጲያ ከተማዎች
🔺የስራ ልምድ: በ 0 ዓመትና በልምድ
🔺 የቅጥር ሁኔታ: በቋሚ ቅጥር
🔺 ብዛት: ከ5,000+ በላይ
🔺ደሞዝ:  ማራኪ

🟥 ፈጥነው ታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ

⁉️ ማሳሰቢያ:- VPN ወይም Psiphon መጠቀም ይኖርባችሗል

👇👇👇👇👇Apply Now👇👇👇👇👇👇
                        👇👇👇👇         
https://addiszemenvacancy.com/2023/08/21/ethiopian-airlines-job-vacancy-5000-vacancies-for-fresh-graduates/


--------Follow Our Website--------
                     👇👇👇👇👇👇
         https://addiszemenvacancy.com


ሰላም ጤና ይስጥልኝ ኑሮ የጨለመባችሁ መፍትሔ አለን የምንሠጣቸው አገልግሎቶች 0938234097
1 ,ለባል እና ሌሎች ማህበረሰብ የሚያዋድድ
2 ,ለህመም
3, ለሀብት
4, ለገበያ
5,ለሥራ
6,ለአጋንንት
7 ,ለግርሜ ሞገስ
8 ,ለብልት
9,ለበረከት
10 ,ለኤችአይቪ ፈዋሽ መድሀኒት
11 ,ለጠላት
12 ,ለጭንቀት
13 ,ለዕድል
14 ,በግብረ ስጋ ግንኙነት ጥሩ እና ያማረ ስሜት እንድኖር
15 ,ብር እንዳይባክን
16,ለእጅ ስራ እንዲቀናህ
17,ከትንሽ እስከ ትልቅ ህመ
18,ለግርማ ሞገስ
    19.ትዳር አስማም ቶ የሚያኖር                   
     20,   ለረደት በረከት ሰርቶ ገንዘብ አልበረክት ላለበት                    
21,ሌባ ጠላት የመሳሠሉ ከባድ ፈተና እንዳይደፍርህ ለአገልግሎት ይደውሉ እያንዳንዱ ችግር እኛጋ መፍትሄ አለ የባህል መድህኒት ፈውስ  የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል
☟☟☟☟☟ ☟☟☟☟☟

☞  ለመፍትሄ ሀብት
☞  ለህመም
☞  ለመስተፋቅር
☞  ቡዳ ለበላው
☞  ለገበያ
☞  ሚስጥር የሚነግር
☞  ለቀለም(ለትምህርት)
☞  ለመፍትሔ ስራይ
☞  ፍቅረኛ ላጣ ወይም ላጣች የሚሰራ
☞  ሌባ የማያስነካ
☞  ለበረከት
☞  ለጠላት (ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ)
☞  ለግርማ ሞገስ
☞  መርበቡተ ሰለሞን
☞  ለዓይነ ጥላ
☞  ለሁሉ መስተፋቅር
☞  ጸሎተ ዕለታት
☞  ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
☞  ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
☞  ለትዳር
☞  ለድምፅ
ይደውሉ መፍትሄ አለን
🌿🌿🌿🌿🌿🌿
           0938234097


የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ የኢትዮጵያ መንግሥትና ረድዔት ድርጅቶች በአማራ ክልል መተማ ወረዳ "አውላላ" በተባለ መንደር 16 ሺህ ስደተኞችን የሚያስተናግድ አዲስ የስደተኞች መጠለያ ለመገንባት ዝግጅት እያደረጉ መኾኑን አስታውቋል። ቢሮው፣ በኩመር የስደተኞች ጣቢያ በኮሌራ አዲስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን መቀነሱንም ገልጧል። ባለፈው ሳምንት ወደ ኮሌራ ሕክምና ማዕከል የገቡት ተማሚዎች በቀደመው ሳምንት ከገቡት በሦስት እጥፍ ቀንሶ 54 ታማሚዎች ብቻ ለሕክምና መግባታቸውን ቢሮው ጠቅሷል። በጠቅላላው ወረርሽኙ ከተቀሰቀሰበት ነሃሴ ጀምሮ፣ 447 ሰዎች ለኮሌራ ሕክምና እንደገቡ የገለጠው ቢሮው፣ 90 በመቶዎቹ እንዳገገሙና ዘጠኝ ታማሚዎች ሕይወታቸው እንዳለፈ አመልክቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ዕሁድ'ለት በጎንደር ከተማ በመንግሥት ወታደሮችና በፋኖ ሚሊሻዎች መካከል በተደረገ ውጊያ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች እንደተገደሉ ወይም እንደቆሰሉ የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ነዋሪዎች ቆስለው ሆስፒታል የገቡ ሰዎችን ወታደሮች ወዳልታወቀ ሥፍራ እንደወሰዷቸው መናገራቸውን የዘገበው ደሞ ቢቢሲ አማርኛ ነው። የፋኖ ታጣቂዎች ከከተማዋ ኹለት ፖሊስ ጣቢያዎች አባሎቻቸውን ጨምሮ "በመቶዎች የሚቆጠሩ" እስረኞችን አስፈትተናል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት ትናንት እንደተቋረጠ መኾኑንና አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ዝግ መኾናቸውን ዘገባው ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


እጁ እየታኘከ የተጫዋች ህይወት ከሞት ያዳነው የሲዳማ ቡናው የህክምና ባለሙያ ብሩክ ደበበ በልዩ ተሸላሚ ሆነዋል።

የኪንዳ ቦይሱ አጥቂ ካልውሌ ምላሱን በመዋጡ በርካቶችም ባዘኑበት በዚህ ጊዜ ከባድ ዝናብ ሳይበግረው ከትሪቩኑ ዘሎ በመውረድ የሲዳማ ቡናው የህክምና ባለሙያ ብሩክ ደበበ ተስፋ አጥቶ የነበረውን ዩጋንዳዊ ተጫዋች ሁለቱን ጣቶቹን አፉ ውስጥ በመክተት እየታኘከ ፣ ጣቶቹም እየደሙ የተጫዋቹን ነብስ ከእግዚአብሔር በታች ማዳኑ የሚታወስ ነው

በትላንትናው የሲዳማ ጎፈሬ ካፕ ላይ ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


እየተገነባ ባለ አፓርታማ ላይ የተከሰተ የእሳት አደጋ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ፡፡

ትላንት መስከረም 14 2016 ዓ.ም ምሽት 1:05 ሰዓት ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ሀጫሉ ሁንዴሳ መንገድ ትራኮን ሪል እስቴት እየገነባ ባለዉ አፓርታማ  5ኛና 6ኛ ፎቅ ላይ የተነሳዉ የእሳት አደጋ በሁለት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ሲያደርስ በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል።

አደጋዉ የደረሰባቸዉ ሁለቱም  የእሳት አደጋ ሰራተኞች ሲሆኑ  አንደኛዉ ሰራተኛ እሳቱን በማጥፋት ሂደት ከህንጻዉ ላይ ወድቆ ከባድ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በአሁን ሰዓት በአለርት ሆስፒታል ህክምና እየተደረገለት ይገኛል ተብሏል።

የእሳት አደጋዉ  በአካባቢዉ ባሉ  መኖሪያ ቤቶች ተዛምቶ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን  እሳቱን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር 9 ሰዓት ፈጅቷል።

የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር የዉሀ ቦቴዎችን ጨምሮ 18 የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎች ከ94 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ተሰማርተዋል።የአዲስ አበባ መንገዶችና የአዲስ አበባ ዉሀና ፍሳሽ ባለስልጣን ዉሀ የጫኑ ቦቴዎችን በማቅረብ ድጋፍ አድርገዋል።መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ነው፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


Ethiopian Airline Jobs 2023💯✔️
---—----------------------------     
♨️ እንኳን ደስ አላችሁ ለመላው ለስራ ፈላጊ ኢትዮጲያዊያን!

✅ ከ 5,000- በላይ ክፍት ቦታዎች በ0 አመት  እና በልምድ

✅ Number of Positions: 5,000+     positions 0 EXP and with Exp

🔺የትምህርት ደረጃ: በሁሉም የትምህርት ደረጃ
🔺የትምህርት አይነት: በተለያዩ ዲፓርትመንቶች
🔺ቦታ: በሁሉም የኢትዮጲያ ከተማዎች
🔺የስራ ልምድ: በ 0 ዓመትና በልምድ
🔺 የቅጥር ሁኔታ: በቋሚ ቅጥር
🔺 ብዛት: ከ5,000+ በላይ
🔺ደሞዝ:  ማራኪ

🟥 ፈጥነው ታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ

⁉️ ማሳሰቢያ:- VPN ወይም Psiphon መጠቀም ይኖርባችሗል

👇👇👇👇👇Apply Now👇👇👇👇👇👇
                        👇👇👇👇         
https://addiszemenvacancy.com/2023/08/21/ethiopian-airlines-job-vacancy-5000-vacancies-for-fresh-graduates/


--------Follow Our Website--------
                     👇👇👇👇👇👇
         https://addiszemenvacancy.com


ሰላም ጤና ይስጥልኝ ኑሮ የጨለመባችሁ መፍትሔ አለን የምንሠጣቸው አገልግሎቶች 0938234097
1 ,ለባል እና ሌሎች ማህበረሰብ የሚያዋድድ
2 ,ለህመም
3, ለሀብት
4, ለገበያ
5,ለሥራ
6,ለአጋንንት
7 ,ለግርሜ ሞገስ
8 ,ለብልት
9,ለበረከት
10 ,ለኤችአይቪ ፈዋሽ መድሀኒት
11 ,ለጠላት
12 ,ለጭንቀት
13 ,ለዕድል
14 ,በግብረ ስጋ ግንኙነት ጥሩ እና ያማረ ስሜት እንድኖር
15 ,ብር እንዳይባክን
16,ለእጅ ስራ እንዲቀናህ
17,ከትንሽ እስከ ትልቅ ህመ
18,ለግርማ ሞገስ
    19.ትዳር አስማም ቶ የሚያኖር                   
     20,   ለረደት በረከት ሰርቶ ገንዘብ አልበረክት ላለበት                    
21,ሌባ ጠላት የመሳሠሉ ከባድ ፈተና እንዳይደፍርህ ለአገልግሎት ይደውሉ እያንዳንዱ ችግር እኛጋ መፍትሄ አለ የባህል መድህኒት ፈውስ  የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል
☟☟☟☟☟ ☟☟☟☟☟

☞  ለመፍትሄ ሀብት
☞  ለህመም
☞  ለመስተፋቅር
☞  ቡዳ ለበላው
☞  ለገበያ
☞  ሚስጥር የሚነግር
☞  ለቀለም(ለትምህርት)
☞  ለመፍትሔ ስራይ
☞  ፍቅረኛ ላጣ ወይም ላጣች የሚሰራ
☞  ሌባ የማያስነካ
☞  ለበረከት
☞  ለጠላት (ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ)
☞  ለግርማ ሞገስ
☞  መርበቡተ ሰለሞን
☞  ለዓይነ ጥላ
☞  ለሁሉ መስተፋቅር
☞  ጸሎተ ዕለታት
☞  ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
☞  ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
☞  ለትዳር
☞  ለድምፅ
ይደውሉ መፍትሄ አለን
🌿🌿🌿🌿🌿🌿
           0938234097

20 last posts shown.