አዲስ ሪፖርተር - NEWS


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !
=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !
🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addis_reporter_bot
#ADDIS ABABA, ETHIOPIA

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


በካቴድራሉ ዙሪያ ያሉት ህንፃዎች ንብረትነታቸው የቤተክርስቲያኗ አይደለም ያለዉ አስተዳዳሪዉ በዚህ ምክንያት ለእድሳቱ አስፈላጊውን ገንዘብ እንዳይገኝ ማድረጉን ገለፀ

ከ 90  ዓመታት በላይ ያስቆጠረው ታሪካዊና አለም አቀፋዊ ካቴድራል የሆነዉ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን የህንፃ እድሳት ሲጀመር የነበረዉ የገንዘብ መጠን 500 ሺህ ብር ገደማ መሆኑን የገለፀው የቤተክርስቲያኗ አስተዳደር የካቴድራሉ የገቢ ምንጭ ከሌሎች ገዳማትና አድባራት ሲነፃፀር እጅግ ያነሰ መሆኑን አስታዉቋል።

ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን የህንፃ እድሳት ሲጀመር የነበረዉ ተቀማጭ ገንዘብ 500 ሺህ ብር ብቻ መሆኑን ያስታወቀዉ አስተዳደሩ ለዚህም በሰዎች ዘንድ ያለዉ የተሳሳተ ግምትና ይህን ለመረዳት ፍቃደኝነት አለማሳየታቸው እንደሆነ ገልጿል።

የገቢ ምንጩ አነስተኛ እንዲሆን አድርገዉታል ካላቸዉ ምክንያቶች መካከል በካቴድራሉ ዙሪያ የነበሩ ነዋሪዎች በልማት ምክንያት መነሳታቸው እንዲሁም አብዛኞቹ ሰዎች በካቴድራሉ ዙሪያ ያሉ ህንፃዎች  የካቴደራሉ ንብረት እንደሆነ በማሰባቸው ምክንያት ለእድሳቱ የገንዘብ አሰባሰብ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ አድርጎታል ብለዋል።

የቤተ ክስርስቲያኗ አስተዳዳሪ ሊቀ ስልጣን ቆሞስ አባ ሲራክ አድማሱ እንደገለጹት የካቴደራሉ እድሳት ከተጀመረ አንድ ዓመት ከግማሽ ገደማ ያስቆጠረ ሲሆን መጋቢት 30 ቀን 2016 እንደሚጠናቀቅ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በገንዘብ እጥረት ሳቢያ ለሦስት ወራት እንዲራዘም መደረጉን አስረድተዋል ።

የህንፃ እድሳቱ እስካሁን 65 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ለፕሮጀክቱ 90 ሚሊዮን ብር ገደማ በተለያዩ መንገዶች ማሰባሰብ እንደተቻለ ካፒታል ከመግለጫው ተከታትሏል ።

በኢትዮጵያ የፓትሪያርክ ሹመት የሚፈጸምበቱ በቸኛ ስፍራ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን በ1924 ከተመሰረተ ጀምሮ ከ90 ዓመታት በላይ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

Via:Capital

@Addis_Reporter


ኬፕ ታውን ኤርፖርት የአፍሪካ ምርጥ አየር ማረፊያ ተብሎ ሲሰየም ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል

በደቡብ አፍሪካ ኬፕ ታውን የሚገኘው አየር ማረፊያ በደንበኞች ደረጃ አሰጣጥ ድርጅት ስካይትራክስ ባደረገው ጥናት የአህጉሪቱ ምርጥ አየር ማረፊያ ተብሎ ተሰይሟል።በአለም አቀፍ ደረጃ ኬፕ ታውን 54ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዝርዝሩ ላይ ያለው ቦታ አየር ማረፊያዉ የቀነሰበት ሲሆን በ 2020 23 ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡

በአህጉራዊ ዝርዝሩ ውስጥ ሌሎች ሁለት የደቡብ አፍሪካ አየር ማረፊያዎች ደርባን እና ጆሃንስበርግ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን እንደ ቅደም ተከተላቸዉ ተቀምጠዋል።በኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ የሚገኘው ቦሌ አየር ማረፊያ ከአፍሪካ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ የናይሮቢው ጆሞ ኬንያታ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 10ኛ ደረጃን አግኝቷል።በሌላ በኩል የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ጎረቤት ሀገራት እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ ተከትሎ በዱባይ አየር ማረፊያ ስራው በእጅጉ አስተጓጉሏል፡፡አውሎ ነፋሱ ማክሰኞ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችን በመምታቱ መንገዶችን እና  የአለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ክፍሎች በጎርፍ ተይዘዋል፡፡ድንገተኛ የጎርፍ አደጋዉ በኦማን 20 ሰዎችን እና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ደግሞ የአንድ ሰው ህይወት ነጥቋል፡፡

አንዳንድ በረራዎች ሐሙስ እለት ቢደረጉም የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ዋና የጉዞ ማዕከል ቢሆንም እምብዛም አገልግሎት እየሰጠ አይደለም፡፡የዓለማችን ሁለተኛዉ አውሮፕላን ማረፊያ ባለስልጣናት ሐሙስ እለት እንደተናገሩት በውጭ አገር አጓጓዦች በሚጠቀሙበት ተርሚናል 1 ወደ ውስጥ የሚደረጉ በረራዎችን መቀበል መጀመራቸውን፣ ነገር ግን ወደ ውጭ የሚደረጉ በረራዎች መጓተታቸውን ቀጥለዋል ሲሉ ተደምጠዋል።የዱባይ አውሮፕላን ማረፊያ ኃላፊ ፖል ግሪፊስ "አሁን በጣም ፈታኝ ጊዜ ነው፤ በህይወቱ ማንም ሰው እንደዚህ አይነት ሁኔታዎችን አይቶ አያውቅም" ብለዋል፡፡አየር ማረፊያው ለመድረስ በሚሞክሩ ሰዎች መጨናነቅ ምክንያት በዙሪያው ያሉት መንገዶች ተዘጋግተዋል።ረቡዕ እለት ብቻ ወደ 300 የሚጠጉ በረራዎች ሲሰረዙ ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ዘግይተዋል ።

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በታሪክ ከፍተኛውን የዝናብ መጠን ተመዝግቦባታል፡፡የመንግስት የዜና ወኪል የዝናብ መረጃ መሰብሰብ ከጀመረበት ከ1949 ዓመት ጀምሮ ከተመዘገቡት ሁሉ የበለጠ ታሪካዊ የአየር ሁኔታ ክስተት ሲል ጠርቶታል።

@Addis_Reporter


ኔስትሊ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት በሚልካቸው የወተት ምርቶቹ ላይ ስኳር እንደሚጨምር ተሰማ!

የስዊዘርላንዱ የምግብና መጠጥ አምራች ኩባንያ ኔስትሊ ወደ አፍሪካ፣ እስያ እና ደቡብ አሜሪካ በሚልካቸው የጨቅላ ህጻናት ወተት እና ሌሎች ምርቶቹ ላይ ስኳር እና ማር እንደሚጨምር "ፐብሊክ አይ" የተሰኘ ስዊዘርላንድ ውስጥ የሚገኝ የምርመራ ትቋም አጋልጧል።

ቡድኑ ከላይ ወደተጠቀሱት ክፍለ አህጉራት የሚላኩ የኒዶ(Nido) እና ሴሪላክ(Cerelac) ምርቶችን ቤልጄም ወደሚገኝ ላብራቶሪ ልከው ያስመረመሩ ሲሆን በውስጡ በአለም የጤና ድርጅት መመሪያ መሰረት አለቅጥ መወፈርን እና ተያያዝ በሽታዎችን ለመከላከል ለጨቅላ ህጻናት የተከለከለ የስኳር መጠንን ይዞ መገኘቱ ተዘግቧል። በአንጻሩ ኩባንያው ለአውሮፓ ደምበኞቹ የሚልከው ስኳር የሌለበት እንደሆነ የዘ ጋርዲያን ዘገባ ያመለክታል።

ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ የተባለው ጋዜጣ እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ በሴሪላክ ምርት ላይ የሚጨመረው ስኳር መጠን ከፍተኛ ከሆነባቸው ሀገራት አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗን ያመለክታል።የመረጃው ይፋ መሆንን ተከትሎ የአለም ጤና ድርጅት ባለሙያዎች የተቹት ሲሆን እስካሁን ኩባንያው ያለው ነገር የለም።

@Addis_Reporter


መንግሥት ጦርነት የሚጎስመውን የሕወሓት ስብስብ በፕሪቶሪያው ሥምምነት መሠረት ትጥቅ እንዲፈታ በማድረግ ሕግ እና ሥርዓት እንዲያስከብር በአፅንዖት እንጠይቃለን ሲል ኢዜማ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል።
ኢዜማ በመግለጫው በሌሎች ክልሎች ልዩ ኃይልና ታጣቂዎች ሲበተኑ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰጠው መብት ለአሁኑ ቀውስ መነሻ ነው ብሏል።


ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

@Addis_Reporter


ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ዙሪያ የአቋም ለውጥ አድርጋለች?

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ፣ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ስለተደረገው የወደብ መግባቢያ ስምምነት እና ሌሎቹም ተጠቃሽ ናቸው።

አቶ ነብዩ እንዳሉት የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ በድንበር አካባቢ ያሉ ማህበረሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መንገድ በሁለቱ ሀገራት በሚዋቀር ኮሚቴ ይፈታል ብለዋል።

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ በኤርትራ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ድንበር ሊቀየር በማይችል ኹኔታ ለመጨረሻ ጊዜ ተሠምሯል ማለቱ አይዘነጋም።

የኤርትራ ጦር በርካታ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን እንደተቆጣጠር እና አካባቢዎቹን ወደ ኤርትራ ማካለሉን እንዴት ኢትዮጵያ እንዴት ታየዋለች? በሚል ለቃል አቀባዩ ለቀረበላቸው ጥያቄም "ጥያቄው ጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አህመድ ከትግራይ ክልል ከተውጣጡ የማህበረሰብ ጋር በተወያዩበት ወቅት እንደተነሳ እና ጉዳዩ በውይይት ይፈታል ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፣ አሁንም ማለት የምችለው ይህንን ነው" ብለዋል።

ከአራት ወር በፊት በአዲስ አበባ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና ራስ ገዟ ሶማሊላንድ መካከል የተካሄደው የወደብ መግባቢያ ስምምነት ጉዳይ ሌላኛው በዛሬው መግለጫ የተነሳ ጉዳይ ሲሆን ኢትዮጵያ ከሶማሊያ እና ሌሎች ሀገራት ባደረሱት ጫና ምክንያት የአቋም ለውጥ ወይም ሌላ አዲስ ነገር ይኖር ይሆን? በሚል ጥያቄ ተነስቷል።

ቃል አቀባዩ በሰጡት ምላሽም " ከሶማሊላንድ ጋር በተደረገው የወደብ መግባቢያ ስምምነት ዙሪያ የተቀየረ አቋም የለም" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

በሳውዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔት የሚኖሩ 70 ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ለመመለስ የተጀመረው ጥረት እንደቀጠለ ነው የተባለ ሲሆን በሳምንት 12 በረራዎች እየተደረጉ እንደሆነም ተገልጿል።

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብን ለመቀላቀል የጀመረችው ድርድር በጥሩ መልኩ እየሄደ ነው የተባለ ሲሆን በተለይም ምርቶችን በመሸጥ ዙሪያ ጥሩ መሻሻል ሲያሳይ በቀጣይ ደግሞ በንግድ አገልግሎቶች ዙሪያ ተጨማሪ ድርድር እንደሚደረግ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።

ከ24 ዓመት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስር ለማሳለጥ የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጥምረት በየጊዜው አዳዲስ አባላትን በመሳብ ላይ ይገኛል።

ጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ከአንድ ዓመት በፊት ይህን ጥምረት ለመቀላቀል በይፋ ከጠየቀች በኋላ ባሳለፍነው ሕዳር ወር ጀምሮ ስምነኛዋ አባል ሀገር መሆኗ ይታወሳል፡፡
የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ የ300 ሚሊዮን ህዝብ መገበያያ መድረክ ሲሆን ኢትዮጵያ አባል ከሆነች የአባል ሀገራቱን ቁጥር ወደ ዘጠኝ የግብይት መጠኑንም ከ400 ሚሊዮን በላይ በማድረስ በአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪ የኢኮኖሚ ትስስር ወደ መሆን ይሸጋገራል ተብላል።

በድርቅ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ለተጎዱ ኢትዮጵያዊያን አንድ ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ለማሰባሰብ በስዊዘርላንድ ጀኔቭ በተካሄደው እርዳታ ላይ የታሰበውን ያህል ገንዘብ መሰብሰብ እንዳልተቻለም ተገልጿል።

በዚህ የገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም ላይ የታሰበውን ያህል ገንዘብ ማግኘት ያልተቻለው አፍሪካን ጨምሮ በሌሎችም አካባቢዎች በተመሳሳይ እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች እና ተቋማት በመኖራቸው እንደሆነ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።

Via:አል ዓይን

@Addis_Reporter


የሙዚቃ ሮያሊቲ ክፍያን ለማስጀመር መሥማማታቸውን የጋራ ማህበራት አስታወቁ 

የኢትዮጵያ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች የጋራ አስተዳደር ማኅበር እና የኢትዮጵያ የሙዚቃ የቅጂና ተዛማጅ መብቶች የጋራ አስተዳደር ማኅበር የጥበብ ሥራዎች የሮያሊቲ ክፍያ የሚፈፀምበት ሥርዓት ላይ በጋራ ለመስራት ሥምምነት ላይ ደርሰዋል። 

የጋራ አስተዳዳር ማኅህበራቱ ይህ ዘርፍ 4 ነጥብ 5 በመቶ ለጠቅላላ የሃገር ውስጥ ምርት እድገት አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል። 

Via:Arada Fm

@Addis_Reporter


የውጭ ባለሀብቶች በጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቀደ

ከዚህ ቀደም ለአገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩ የወጪ፣ የገቢ፣ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ለውጭ ባለሃብቶች ከፍት እንዲሆኑ ተደረገ፡፡ 

በዚህም መሰረት የውጭ ባለሀብቶች በጥሬ ቡና፣ በቅባት እህሎች፣ ጫት፣ ጥራጥሬ፣ ቆዳ እና ሌጦ፣ የደን ውጤቶች እና የቁም እንስሳት የመላከ የወጪ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቅዷል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን እና የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጉዳዩ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫው ላይ እንደተገለፀው፤ የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሟሉ የውጭ ባለሃብቶች ከማዳበሪያ እና ነዳጅ በስተቀር በሁሉም የገቢ ንግድ ኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ይችላሉ፡፡

የጅምላ ንግድን በተመለከተ ከማዳበሪያ ጅምላ ንግድ በስተቀር በሁሉም አይነት የጅምላ ንግድ መስኮች መሰማራት ይችላል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች ቅድመ ሁኔታዎችን ሲያሟሉ ለአገር ውስጥ ባለሃብት በተከለሉ ሁሉም የችርቻሮ ንግድ ስራዎች መሳተፍ እንዲችሉ መፈቀዱም ተጠቅሷል። 

በጉዳዩ ላይ በባለድርሻ አካላት የተካሄዱ ዝርዝር ጥናቶች ላይ በመመርኮዝ መሠረታዊ የፖሊሲ ለውጥ ያደረገው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድም አዲስ የአፈፃፀም መመሪያ አፅድቋል።

Via:ኢቢሲ

@Addis_Reporter


#Update

ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደ

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ፡፡

የፌደራል ፖሊስ መርማሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ከትናንት በስቲያ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ በአካል ቀርበው ሀሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመያዝ ለ3 ግለሰቦች እና ለአንድ የግል ድርጅት ሒሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሊያዘዋውሩ ሲሉ በአፍሪካ ህብረት ሴኪዩሪቲዎች ተይዘው ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ተላልፈው መሰጠታቸውን ጠቅሶ የጥርጣሬ መነሻውን ለችሎቱ አቅርቧል።

በዚህ መነሻ መሰረትም መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ሥራ ለማከናወን የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

ተጠርጣሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ድርጊቱ መፈጸሙን አምነው፤ ይሁን እንጂ ወንጀል አለመፈጸማቸውን አስረድተዋል፡፡

ስለሆነም የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።

@Addis_Reporter


በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ በአዲስ አበባ ከተማ መሠረተ ልማትና የመሬት አጠቃቀም ዙሪያ ከከንቲባ አዳነች አቤቤ ጋር ትናንት መወያየታቸውን ገልጸዋል።

ማሲንጋ፣ በአሜሪካ "ውስብስብና አንገብጋቢ" የፖለቲካ ጉዳዮች በኾኑት በከተማ እቅድና የከተማ መሠረተ ልማት ዙሪያ ገጥመዋት የነበሩትን ተግዳሮቶች ለአዳነች እንዳብራሩላቸው ጠቅሰዋል። በከተማ እቅድ ዙሪያ ከዜጎች ጋር ግልጽ ውይይት ማድረግን፣ ኅብረተሰቡን ያሳተፈ እቅድ መንደፍንና በእቅድ አፈጻጸም ትዕግስት አስፈላጊ መኾኑን አሜሪካ ከልምዷ መማሯን አምባሳደሩ ገልጸዋል።

@Addis_Reporter


የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ምክር ቤት፣ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ለመወያየት ጥያቄ አቅርቤያለሁ ማለቱን ዶይቸቨለ ዘግቧል።

ምክር ቤቱ፣ ዐቢይ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሶ፣ ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ጋር ጭምር እንዲወያዩ ጥያቄ እንዳቀረበ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። ምክር ቤቱ ይህንኑ ጥያቄውን ከሦስት ሳምንት በፊት ለጠቅላይ ሚንስቴር ጽሕፈት ቤት ማስገባቱንና እስካኹን ምላሽ እየተጠባበቀ እንደኾነ ተናግሯል ተብሏል። ምክር ቤቱ ለውይይት ካነሳቸው አጀንዳዎች መካከል፣ የጋዜጠኞች እሥርና እንግልትና የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የገጠሟቸው ችግሮች እንደሚገኙበት መጥቀሱንም ዜና ምንጩ አመልክቷል። ዐቢይ ላለፉት ስድስት ዓመታት ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች ጋር ተወያይተው አያውቁም።

@Addis_Reporter


በአዲስ አበባ ከተማ ተቋርጦ የነበረው የመታወቂያ መስጠት እና እድሳት አገልግሎት በቀጣዩ ሳምንት ዳግም ይጀመራል ተባለ

በአዲስ አበባ ከተማ ከአንድ ሳምንት በላይ ተቋርጦ የቆየውን የመታወቂያ መስጠት እና እድሳት አገልግሎትን በሚቀጥለው ሳምንት ለመጀመር የጥገና ስራ እያከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ገለጸ። ኤጀንሲው ይሰጣቸው የነበሩ መደበኛ አገልግሎቶች የተቋረጡት፤ ከመረጃ ማከማቻ ቋቱ ጋር በተገናኙ “የቴሌኮም ኬብሎች” ላይ ጉዳት በመድረሱ መሆኑን ገልጿል።

በአዲስ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ፤ የመታወቂያ ስርጭት፣ የልደት እና የሞት ምዝገባ፣ ያላገባ የምስክር ወረቀት፣ የማስረጃ የማረጋገጥ ስራን እንዲሁም የጋብቻ እና የፍቺ ምዝገባን የሚከውን ተቋም ነው። ኤጀንሲው በመዲናዋ የሚገኙ 106 ወረዳዎችን “በዲጂታል” ስርዓት” በማስተሳሰር ይሰጣቸው የነበሩ አገልግሎቶች፤ ካለፈው አንድ ሳምንት ወዲህ በመቋረጣቸው በተገልጋዮች ላይ መጉላላትን አስከትሏል።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሶስት የሚገኝ የነዋሪነት ምዝገባ ጽህፈት ቤትን በትላንትናው ዕለት በአካል ተገኝቶ የተመለከተው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ፤ ለወትሮ በሰው ብዛት ይጨናነቅ የነበረው አገልግሎት መስጪያ ባዶ መሆኑን ታዝቧል። አገልግሎት መቋረጡን ባለመስማት ወደ ጽህፈት ቤቱ የመጡ ሁለት ነዋሪዎችም እምብዛም ሳይቆዩ መመለሳቸውንም ተመልክቷል።

በኤጀንሲው የ“ዲጂታል ስርዓት” ላይ ችግር ያጋጠመው፤ መስሪያ ቤቱ ከሚጠቀምባቸው የመረጃ ቋቶች መካከል አንደኛውን በሚያገናኙ የቴሌኮም መስመሮች ላይ ጉዳት ከደረሰ በኋላ መሆኑን በኤጀንሲው የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አእምሮ ካሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በተለምዶ “ማዘጋጃ ቤት” ተብሎ በሚጠራው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ህንጻ ውስጥ ከሚገኘው የመረጃ ቋት ጋር የተያያዘው የቴሌኮም መስመር ጉዳት የደረሰበት፤ በአካባቢው የ“ኮሪደር ልማት” በሚከናወንበት ወቅት መሆኑንም አብራርተዋል።

@Addis_Reporter


ሊቅ አዕላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን መጠኑ ከፍተኛ የኾነ ገንዘብ ወደ ግል ሒሳባቸው ሊያስገቡ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ዋሉ ተባለ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ የኾኑት ሊቅ አዕላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን በጸጥታ አካላት ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዋዜማ ከታማኝ ምንጮች ሰምታለች።

ምክትል ሥራ አስኪያጁ ትላንት ማክሰኞ ሚያዚያ 9 ቀን በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ አፍሪካ ኅብረት ዋና መስሪያ ቤት አካባቢ በሚገኝ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ መጠኑ ከፍተኛ የኾነ ገንዘብ ወደ ግል ሒሳባቸው ሊያስገቡ ሲሉ መሆኑን ምንጮች ለዋዜማ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ከዘገባዉ ተመልክቷል። ሊቀ አዕላፍ በላይ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ልደታ ወደሚገኘው አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዳቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ተረድታለች።

ሊቀ አዕላፍ በላይ ከዓመታት በፊት ከቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ልዩነት ከፈጠሩ በኋላ፣ በእርቅ ወደ ቤተክህነት ተመልሰው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ኾነው እንደተሾሙ ይታወሳል።

Via ዋዜማ

@Addis_Reporter


🍀🍀መርጌታ ይልቃል ከፍተኛ የባህል  ህክምና    
        ☎️📞
0952400019
የአባቶቻችንን ጥበብ ይፈልጋሉ?
ከምንሰጣቸው በትንሹ
🍀ለመስተፋቀር
🍀ለጥይት መከላከያ
🍀 ለገበያ
🍀 ለበረከት
🍀ለስንፈተ ወሲብ
🍀ለሀብት
🍀ለቁማር
🍀ስልጣን ለመጨመር
🍀ለቀለም (ለትምህርት)
🍀 ገንዘብ ለማስመለስ
🍀ቡዳ ለበላው
🍀 እራስን ስቶ ለሚወድቅ
🍀ለህማም(ለማንኛውም)
🍀ለመድፍነ ፀር
🍀ሌባ የማያስነካ
🍀ለግርማ ሞገስ
🍀ለዓይነ ጥላ
🍀ለሁሉ መስተፋቅር
🍀ጸሎተ ዕለታት
🍀ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
🍀ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
🍀ለድምፅ
🍀ጋኒን ለያዘው

ከሀገር ውጪ ለሚኖሩ

🍀 የመኖሪያ ፍቃድ ላላገኙ  መፍትሄ
🍀 ከሀገር ውጪ ስራ እድል ላጡ
🍀 ለንግድ
🍀 ገንዘብ ለሚያባክኑ
🍀 ሰውፊት መቆም መናገር ለሚፈሩ 
🍀 ለሀብት 
🍀  ለስንፈተ ወሲብ
🍀 ፍቅረኛ አልያዝ ላላቸውም አለን
🍀 ትምህርት አልገባ ላለው
🍀 መስተፋቅር ፣የህዝብ መስተፋቅር
🍀 ከሀገር መውጣት እየፈለጉ ላልተሳካላቸው ። ከሀገር ውጪ ላላችውም መፍትሄ አለን  ይደውሉ ያማክሩን ::ባላቹህበት እንሰራለን
በአካል መምጣት ለማትችሉ መዳኒቱን ባሉበት ቦታ እናደርሳለን::
🇪🇹
0952400019
በimo አና Telegram ማውራት ለምትፈልጉ በውስጥ መስመር ያውሩኝ!


በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ሰርጀሪ ለማድረግ እስከ ሶስት ዓመት ወረፋ እንደሚጠብቁ ተገለጸ

7ሺህ የሚሆኑ ህጻናት የልብ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ወረፋ እየተጠባበቁ ይገኛሉ


በኢትዮጵያ የልብ ህክምና ክትትል  እያደረጉ ያሉ እና ቀዶ ጥገና ለማድረግ 7ሺህ የሚሆኑ ህጻናት ወረፋ እየተጠባበቁ እንደሚገኝ   ኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማእከል ገለጸ፡፡

በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ  የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ክፍል   ባልደረባ   የሆኑት አቶ ዶክተር ዳዊት እሸቱ በተለይም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደገለጹት ማእከሉ በዓመት ለ1500 ታካሚዎች አገልግሎት መስጠጥ ቢችልም በአሁን ሰዓት ለ500 ህሙማን ብቻ አገልግሎት እንሚሰጥ ገልጸዋል፡፡

ተቋሙ ላለፉት አራት አመታት በዓመት ውስጥ  በሺዎች የሚቆጠሩ ታማሚዎች ህክምና ለማግኘት እንደሚጠብቁ የተገለጸ ሲሆን  ለ500  ታካሚዎች  ብቻ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ለህክምናው የሚያስፈልጉ  እቃዎች አለመሟላት በተለይም መድሃኒቶች በበቂ ሁኔታ አለመኖራቸው  በታቀደው ልክ ህክምና መስጠት እንዳይቻል  ተግዳሮት መሆኑንም ባለሙያው ነግረውናል፡፡

ይሁን እና ልማት ባንክ ባመቻቸው  እድል አማካኝነት  አስፈለጊ  የሆነው  የልብ እና የሳምባን ስራ  ተክቶ የሚሰረው መሳሪያ ወደ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት በመቻሉ ለዓንድ ዓመት ጥሩ የሆነ አስተዋጽኦ  እንደሚያደርግላቸው አክለዋል፡፡

በ2016 ዓመት 40 ታካሚዎች   ወደ ውጪ ሀገር   ተልከው  እንዲታከሙ ማድረግ ተችሏል። ታካሚዎች ወደ ውጪሄደው ህክምና እንዲያገኙ የሚደረገው  ሀገር ውስጥ ባሉ  የህክምና  መሳሪያዎች  ህክምናውን መስጠት የማቻልበት የጤና ሁኔታ ላይ ሲሆኑ ብቻ መሆኑንም ነግረውናል።  

ማዕከሉ ምንም እንኳን ነጻ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ቢሆንም  አንድ ሰርጀሪ ለመስራት ተቋሙ የሚያወጣው ወጪ ከ100ሺህ ብር በላይ እንደሚሆንም ተጠቁሟል፡፡   አንድ ታካሚ መጀመሪያ ከታየበት ቀን ሰርጀሪ እስከሚሰራበት ቀን ድረስ ለሶስት ዓመት ወረፋ ሊጠብቅ የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ እና በአሁን ሰዓት 20 ሺህ ታካሚዎች አገልግሎቱን ለማግኘት ወረፋ በመጠበቅ ላይ እንደሆኑ ዶክተር ዳዊት እሸቱ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡

Via:Bisrat radio

@Addis_Reporter


ሃማስ ፍልስጥኤማውያን እስረኞችን ማስፈታት 'ቀዳሚ ጉዳይ ነው' ሲል አስታወቀ

በዛሬው እለት የፍልስጤም እስረኞች ቀን ታስቦ የዋለ ሲሆን ቀኑ የፍልስጤም እስረኞችን ለማስፈታት እና ለመብታቸው ድጋፍ የሚያደርጉበት ብሔራዊ ቀን ነው። ሃማስ ቀኑን ባከበረበት ወቅት በሰጠው መግለጫ እስረኞቹን ከእስራኤላውያን ማረሚያ ቤቶች ማስፈታት “ቀዳሚ ተቀዳሚ ጉዳይ ነው” ሲል አፅንዖት ሰጥቷል።

እስራኤል "በእስር ቤቶች እና በማቆያ ማእከላት ውስጥ በሚገኙ እስረኞች ላይ እጅግ አሰቃቂ ወንጀሎችን፣ የህክምና ቸልተኝነትን፣ ማሰቃየትን እና ቀጥተኛ ግድያዎችን መፈፀሟንን ቀጥላለች" ሲል ሃማስ  አስታውቋል። ከጥቅምት 7 ጀምሮ እስራኤል በዌስት ባንክ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጥኤማውያን አፍና በመውሰድ በህይወታቸው እና ደህንነታቸው ላይ ለሚደርሰው ጥፋት ሙሉ ሀላፊነት እንደምትወስድ ሀማስ አክሏል።

እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ባካሄደችው የስድስት ወራት ጦርነት የተገደሉት ፍልስጤማውያን ቁጥር 33 ሺ 8 መቶ 99 መድረሱን የሃማስ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 56 ፍልስጤማውያን ሲገደሉ 89 ቆስለዋል ሲል ሚኒስቴሩ አክሎ ገልጿል። ቢያንስ 76,664 ሰዎች በማያቋርጥ ጥቃቶች ቆስለዋል። ከሟቾች መካከል ከ14,520 በላይ ህጻናት እና 10,000 ሴቶች ይገኙበታል። የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊልቅ እንደሚችል የሚገመት ሲሆን በህንጻ ፍርስራሾች ውስጥ የተቀበሩት ሊኖሩ እንደሚችል ይገለጻል።

@Addis_Reporter


ዱባይ በጎርፍ ተጥለቀለቀች

በዱባይ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መጠን ነፋስ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ መዝነቡን ተከትሎ ከተማዋ በጎርፍ ተጥለቅልቃለች።

ጎርፉን ተከትሎ የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያን ጨምሮ የከተማዋ ዋና ዋና ጎዳናዎች ከባድ ጎርፍ እያስተናገዱ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይም ከዚህ ቀደም በርከታ በረራዎችን ሲያስተናግድ በነበረው የዱባይ አየር መንገድ በረራዎች ተስተጓጉለዋል።

ነፋስ የቀላቀለው ከባድ ዝናብ በኦማን ተከስቶ 18 ሰዎች ህይወታቸው ካለፈ በኋላ አሁን ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና በባህሬን ጉዳት እያስከተለ እንደሚገኝ የአልጀዚራ ዘገባ ያመለክታል።

@Addis_Reporter


በአዲስ አበባ 1.5 ሚሊዮን የቤት እጥረት መኖሩ ተነገረ።

አልሚዎች በየአመቱ 200 እና ከዚያ በላይ ቤቶች እየገነቡ የከተማዋ የቤት ችግር መቅረፍ አይቻልም ተብሏል።

በመሆኑም ባለሀብቶች በቤት ልማት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ የከተማ አስተዳደሩ ጠይቋል።

በቤት ልማት መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ከተማ አስተዳደሩ ማበረታቻ እንደሚያደርግም አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ግርማ ሰይፊ እንደተናገሩት በከተማው ያለው የቤት ፍላጎት እና አቅርቦቱ የተመጣጠነ አይደለም ብለዋል።

ከተማዋ በልማት ምክንያት በርካታ ቤቶች በልማት እያፈረሰች ከመሆኑ ጋር በተያያዘም የቤት ፍላጎቱ እየጨመረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከፍተኛ ፍላጎት የሚታይበት የቤት ችግር ለመቅረፍ ከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮች እያቀረበ ይገኛልም ብለዋል።

የሪልዕስቴት አልሚዎች በአመት 200 እና ከዚያ በላይ ቤት እየሰሩ የከተማው የቤት ፍላጎት ማሟላት አይቻልም ሲሉም ተናግረዋል።

ባለሀብቶች ከሪል ዕስቴት ከፍ ብለው በቤት ልማት ውስጥ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።

ከዚህ በፊት በዘርፉ የነበሩ ማነቆዎች ከተማ አስተዳደሩ እየቀረፈ እንደሚገኝ የተናገሩት ኮሚሽነር ግርማ ባለሀብቶች ዕድሉን መጠቀም አለባቸው ብለዋል።

ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት በቤት ልማት ዘርፍ ላይ የተሰማራው ዋልያ ሆምስ ባዘጋጀው መድረክ ነው።

ዋልያ ሆምስ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የገነባቸው ቤቶች በተመለከተ የማስተዋወቂያ ዝግጅት አድርጓል።

ኩባኒያው ኡቡንቱ ዴሉክስ አፓርትመንት እና አጃንባ ቪላስ የተሰኙ ሁለት ፕሮጀክቶቹ ለዘርፉ ተዋናዮች እና ለመንግስት ሀላፊዎች አስተዋዉቋል።

የዋልያ ሆምስ አፓርትመንቶች የሚገኙት በላንቻና በቅሎ ቤት አካባቢ መሆኑ ተነግሯል።

@Addis_Reporter


ከአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

የክልሉ መንግሥት ፥ " ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ከሷል።

" ህወሓት የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት ማወጁና መቀስቀሱ ይታወቃል " ሲል አስታውሷል።

የአማራ ክልል መንግሥት ህወሓትን " የመላ ኢትዮጵያ ጠላትና የደኅንነት ስጋት " እንደሆነ ገልጾ " ባለፉት 3 ዙሮች ከተደረገው ደም አፋሳሽ ጦርነት ትምህርት ሊወስድ ይችል ይሆናል በሚል ጭላንጭል ተስፋ የፌዴራል መንግሥት እጅግ እልህ አስጨራሽ ትዕግስት ተላብሶ ውይይቶች እንዲካሄዱ ተደጋጋሚ ጥረት ሲያደረግ ቆይቷል " ብሏል።

" የአማራ ክልል መንግሥትም በተደጋጋሚ ከትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር ጋር በፌዴራል መንግሥት አማካኝነት ውይይት ለማድረግ በርካታ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም ህወሓት ይህን የሰላም አማራጭ ወደ ጎን በመተው የማንነት ጥያቄ ያለባቸውን የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረምና ዛታ አካባቢዎች ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ገልጿል።

" ህወሓት ወረራ የፈፀመባቸው ፦
- የራያ አላማጣ፣
- ራያ ባላ፣
- ኦፍላ፣
- ኮረምና ዛታ እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት አካባቢዎች የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት ከመፅደቁ በፊት በነበሩ አሥተዳደራዊ መዋቅርና አደረጃጀት በኀይል ጠቅልሎ ከመውሰድ ጀምሮ የዘር ማጥፋት ወንጀል እስከመፈፀም ድረስ አሰቃቂ ጥፋት የፈፀመባቸው አካባቢዎች  ናቸው " ብሏል።

" ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ህወሓት በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ ከተቀሰቀሰው ጦርነት በኃላ አካባቢዎቹ በጉልበት ተገፎባቸው የነበረውን ራሳቸውን የማሥተዳደር ነጻነት መቀዳጀት እንደቻሉ " የአማራ ክልል መንግሥት ገልጿል።

በኃላም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ፤ ህወሓት ግን ስምምነቱን በማክበር በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የድርሻውን ከመወጣት ይልቅ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ በመጣስ የተለያዩ ጥፋቶችን ሲፈጽም እንደቆየ አመላክቷል።

" አሁንም እየፈጸመ ይገኛል " ብሏል።

የአማራ ክልል መንግሥት ፥ ህወሓት ደም አፋሳሽ የሆነ ጦርነት ለማድረግ ከመሞከር እንዲታቀብ እና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲያከብር አሳስቧል።

" በአጭር ጊዜ በወረራ የያዛቸውን አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ " ሲል ጠይቋል።

" ይህ የማይሆን ከሆነ የአማራ ክልል መንግሥት እና ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ በመሆን ሀገርን ከማፍረስ መታደግናረ ሕዝባችንንም ከጥቃት ለመከላከል እንገደዳለን " ሲል አስጠንቅቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@Addis_Reporter


የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ አገልግሎት፣ በመጋቢት ወር አገር ዓቀፍ የዋጋ ግሽበቱ 26 ነጥብ 2 በመቶ እንደነበር ትናንት ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።

በመጋቢት ወር የምግብ ነክ ሸቀጣ ሸቀጦች የዋጋ ግሽበት 29 በመቶ ድርሻ እንደነበረው አገልግሎቱ ገልጧል። ምግብ ነክ ያልኾኑ ሸቀጦች የዋጋ ግሽበት ደሞ 22 በመቶ ኾኖ እንደተመዘገበ ተገልጧል። አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ በየካቲት ወር 28 ነጥብ 2 በመቶ ነበር ተብሏል።

@Addis_Reporter


የተመድ ሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ትናንት ጀኔቫ ውስጥ ባካሄደው የሰብዓዊ እርዳታ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ከ630 ሚሊዮን ዶላር በላይ ቃል እንደተገባለት አስታውቋል።

ቢሮው፣ በዕለቱ ከዓለማቀፍ ለጋሾች ለማሰባሰብ ያቀደው የገንዘብ መጠን ግን ለቀጣዮቹ አምስት ወራት ለአስቸኳይ እርዳታ የሚውል 1 ቢሊዮን ዶላር ነበር። አሜሪካ 154 ሚሊዮን ዶላር ለመለገስ ቃል የገባች ሲኾን፣ ብሪታንያ 124.58 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም አውሮፓ ኅብረት 139 ሚሊዮን ዶላር ለመለገስ ቃል ገብተዋል።

@Addis_Reporter

20 last posts shown.