“ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” የግጥም መድበል አርብ ይመረቃል
በገጣሚት መሠረት አዛገ “ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የግጥም መድበል፣ ከነገ ወዲያ አርብ 4 ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት፣ አንጋፋ የኪነጥበብ ሰዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሥነጽሑፍ ቤተሰቦች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡
በምረቃው ሥነስርዓት ላይ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ አያልነህ ሙላቱ፣ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ሥዩም ተፈራ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ፣ ደራሲና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕል፣ መምህር የሻው ተሰማ (የኮተቤው) እና ወጣት ገጣሚያን ሥራቸውን ያቀርባሉ፡፡
ገጣሚ መሠረት አዛገ፣ የ”መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት” መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ስትሆን፣ ላለፉት 14 ዓመታት በህጻናትና በእናቶች ድጋፍና እገዛ ላይ በሠራቻቸው ሥራዎች በርካታ ሽልማቶችን ከሀገር ውስጥና ከተለያዩ የውጪ ሀገራት እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት ማግኘት የቻለች እንስት ናት፡፡
በገጣሚት መሠረት አዛገ “ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የግጥም መድበል፣ ከነገ ወዲያ አርብ 4 ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት፣ አንጋፋ የኪነጥበብ ሰዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሥነጽሑፍ ቤተሰቦች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡
በምረቃው ሥነስርዓት ላይ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ አያልነህ ሙላቱ፣ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ሥዩም ተፈራ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ፣ ደራሲና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕል፣ መምህር የሻው ተሰማ (የኮተቤው) እና ወጣት ገጣሚያን ሥራቸውን ያቀርባሉ፡፡
ገጣሚ መሠረት አዛገ፣ የ”መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት” መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ስትሆን፣ ላለፉት 14 ዓመታት በህጻናትና በእናቶች ድጋፍና እገዛ ላይ በሠራቻቸው ሥራዎች በርካታ ሽልማቶችን ከሀገር ውስጥና ከተለያዩ የውጪ ሀገራት እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት ማግኘት የቻለች እንስት ናት፡፡