የአሜሪካ ትምህርት ዲፓርትመንት 1 ሺ 300 ሰራተኞችን አባረረ
• 60 ዩኒቨርስቲዎች በመብት ጥሰት ወንጀል ምርመራ እየተደረገባቸው ነው
የአሜሪካ የትምህርት ዲፓርትመንት 1ሺ 300 ሰራተኞቹን በማባረር የሰው ሃይሉን በ50 በመቶ ገደማ መቀነሱን አስታወቀ፡፡ የትራምፕ አስተዳደር አዲሷ የትምህርት ዲፓርትመንት ሃላፊ ሊንዳ ማክማዎን፣ "የአሜሪካን የትምህርት ሥርዓት ወደ ታላቅነቱ ለመመለስ ጉልህ እርምጃ ነው" ብለውታል፤ የሰው ሃይል ቅነሳውን፡፡
የትምህርት ዲፓርትመንት ሃላፊዋ ስለጉዳዩ በx ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ፤ "የሰው ሃይል ቅነሳው ለውጤታማነት፣ ለተጠያቂነትና ሃብቶች እጅጉን አስፈላጊ ወደሆኑበት ቦታ መመራታቸውን ለማረጋገጥ ያለንን ቁርጠኝነት ያንፀባርቃል፡- ለተማሪዎች፣ ለወላጆችና ለአስተማሪዎች።" ብለዋል፡፡
አክለውም፤ "የትጉህ የመንግሥት ሰራተኞችን ሥራና ለዲፓርትመንቱ ያበረከቱትን አስተዋፅዖ አደንቃለሁ። እርምጃው የአሜሪካ የትምህርት ሥርዓት ታላቅነትን ለመመለስ ጉልህ እርምጃ ነው።" ብለዋል፡፡
ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው፤ የትምህርት ዲፓርትንቱ በቅርቡ ካደረገው የሠራተኛ ቅነሳ በኋላ፣ የሰው ሃይሉ ከቀድሞው 4ሺ100 ሰራተኞች ወደ 50 በመቶ ገደማ የሚቀንስ ይሆናል፡፡ የዲፓርትመንቱ መረጃ እንደሚጠቁመው፤ ባለፉት 7 ሳምንታት ተጨማሪ 572 ሰራተኞች 'በፈቃደኝነት የመልቀቂያ እድሎችንና ጡረታን' ተቀብለዋል፡፡.
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የአሜሪካ ትምህርት ዲፓርትመንት፣ 60 የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች. የሲቪል መብት ጥሰት ወንጀል ምርመራ እየተካሄደባቸው ስለመሆኑ ከትላንት በስቲያ ሰኞ አስታውቋል።
የትራምፕ አስተዳደር እስራኤል በጋዛ ላይ የምታደርገውን ጦርነት በመቃወም የሚካሄዱ ሰልፎችን በአይሁድ ተማሪዎች ላይ ያነጣጠረ “ፀረ-ሴማዊ ትንኮሳና መድልዎ” ሲል ፈርጇል።
• 60 ዩኒቨርስቲዎች በመብት ጥሰት ወንጀል ምርመራ እየተደረገባቸው ነው
የአሜሪካ የትምህርት ዲፓርትመንት 1ሺ 300 ሰራተኞቹን በማባረር የሰው ሃይሉን በ50 በመቶ ገደማ መቀነሱን አስታወቀ፡፡ የትራምፕ አስተዳደር አዲሷ የትምህርት ዲፓርትመንት ሃላፊ ሊንዳ ማክማዎን፣ "የአሜሪካን የትምህርት ሥርዓት ወደ ታላቅነቱ ለመመለስ ጉልህ እርምጃ ነው" ብለውታል፤ የሰው ሃይል ቅነሳውን፡፡
የትምህርት ዲፓርትመንት ሃላፊዋ ስለጉዳዩ በx ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ፤ "የሰው ሃይል ቅነሳው ለውጤታማነት፣ ለተጠያቂነትና ሃብቶች እጅጉን አስፈላጊ ወደሆኑበት ቦታ መመራታቸውን ለማረጋገጥ ያለንን ቁርጠኝነት ያንፀባርቃል፡- ለተማሪዎች፣ ለወላጆችና ለአስተማሪዎች።" ብለዋል፡፡
አክለውም፤ "የትጉህ የመንግሥት ሰራተኞችን ሥራና ለዲፓርትመንቱ ያበረከቱትን አስተዋፅዖ አደንቃለሁ። እርምጃው የአሜሪካ የትምህርት ሥርዓት ታላቅነትን ለመመለስ ጉልህ እርምጃ ነው።" ብለዋል፡፡
ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው፤ የትምህርት ዲፓርትንቱ በቅርቡ ካደረገው የሠራተኛ ቅነሳ በኋላ፣ የሰው ሃይሉ ከቀድሞው 4ሺ100 ሰራተኞች ወደ 50 በመቶ ገደማ የሚቀንስ ይሆናል፡፡ የዲፓርትመንቱ መረጃ እንደሚጠቁመው፤ ባለፉት 7 ሳምንታት ተጨማሪ 572 ሰራተኞች 'በፈቃደኝነት የመልቀቂያ እድሎችንና ጡረታን' ተቀብለዋል፡፡.
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የአሜሪካ ትምህርት ዲፓርትመንት፣ 60 የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች. የሲቪል መብት ጥሰት ወንጀል ምርመራ እየተካሄደባቸው ስለመሆኑ ከትላንት በስቲያ ሰኞ አስታውቋል።
የትራምፕ አስተዳደር እስራኤል በጋዛ ላይ የምታደርገውን ጦርነት በመቃወም የሚካሄዱ ሰልፎችን በአይሁድ ተማሪዎች ላይ ያነጣጠረ “ፀረ-ሴማዊ ትንኮሳና መድልዎ” ሲል ፈርጇል።