ለምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢና ሁለት አባላት
እጩዎችን እንዲጠቁም ለህብረተሰቡ ጥሪ ቀረበ
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢና ሁለት አባላት እጩዎችን ከነገ ጀምሮ እንዲጠቁም የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስራ አመራር ቦርድ አባላት መልማይ ኮሚቴ ለህብረተሰቡ ጥሪ አቀረበ።
የእጩዎች ጥቆማ መስጫ ጊዜ ከነገ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይም ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ባለፈው ሳምንት መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም. ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ ስምንት አባላትን የያዘ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባላት ዕጩ መልማይ ኮሚቴ መሰየማቸው ይታወሳል፡፡
ኮሚቴው ከተቋቋመ አንስቶ የዕጩ ምልመላ ሥራውን ለመምራት የሚያስችሉ የውስጥ አሠራር መመሪያ ማጽደቅና የመመልመያ የጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀት የመሳሰሉ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን የኮሚቴው ሰብሳቢ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ተናግረዋል።
ቀሲስ ታጋይ እንደገለጹት፤ እነዚህን የምርጫ ቦርድ አመራሮች ለመተካት ሂደት የተጀመረው የሥራ ዘመናቸው የማጠናቀቂያ ጊዜ በመቃረቡ ነው። ዕጩ ጥቆማ የሚደረግባቸው የቦርድ አባላት፤ ምክትል ሰብሳቢው አቶ ውብሸት አየለ እንዲሁም ዶ/ር አበራ ደገፉና ብዙወርቅ ከተተ ናቸው።
እጩዎችን እንዲጠቁም ለህብረተሰቡ ጥሪ ቀረበ
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢና ሁለት አባላት እጩዎችን ከነገ ጀምሮ እንዲጠቁም የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስራ አመራር ቦርድ አባላት መልማይ ኮሚቴ ለህብረተሰቡ ጥሪ አቀረበ።
የእጩዎች ጥቆማ መስጫ ጊዜ ከነገ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይም ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ባለፈው ሳምንት መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም. ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ ስምንት አባላትን የያዘ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባላት ዕጩ መልማይ ኮሚቴ መሰየማቸው ይታወሳል፡፡
ኮሚቴው ከተቋቋመ አንስቶ የዕጩ ምልመላ ሥራውን ለመምራት የሚያስችሉ የውስጥ አሠራር መመሪያ ማጽደቅና የመመልመያ የጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀት የመሳሰሉ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን የኮሚቴው ሰብሳቢ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ተናግረዋል።
ቀሲስ ታጋይ እንደገለጹት፤ እነዚህን የምርጫ ቦርድ አመራሮች ለመተካት ሂደት የተጀመረው የሥራ ዘመናቸው የማጠናቀቂያ ጊዜ በመቃረቡ ነው። ዕጩ ጥቆማ የሚደረግባቸው የቦርድ አባላት፤ ምክትል ሰብሳቢው አቶ ውብሸት አየለ እንዲሁም ዶ/ር አበራ ደገፉና ብዙወርቅ ከተተ ናቸው።