አለሕግAleHig ️


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter








የሕግ ምክር ያስከፍላል !!!


ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ጠበቃ በአሜሪካ የተከሰሰውን ቻይናዊ ነፃ አወጡ፡፡ የስልሳ አምስት አመቱ ቻይናዊ ሊታንግ ሊያንግ በአሜሪካ ፌዴራል ፍርድ ቤት የተከሰሱት የቻይና ሰላይ ናቸው በሚል ነበር፡፡

እ.ኤ.አ በ2023 የቀረበባቸው ይህ ክስ በቦስተን የሚገኙ የቻይና ኮሚኒቲ አባላትንና ቡድኖችን እንዲሁም የመንግስት ተቃዋሚዎችን የግል መረጃ ለቻይና ባለስልጣናት እየሰጡ መሆኑን የሚገልፅ ነው፡፡ በክሱ ላይ የቻይና መንግስት በውጭ አገር የሚገኙ ተቺዎቹን ድምፅ ዝም ለማስባል በሚያደርገው እንቅስቃሴ እኚህ ቻይናዊ በድብቅ ለአገራቸው መንግስት እየሰለሉ መሆናቸው ተገልፆ ነበር፡፡

በቻይና የተወለዱትና የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው እኚህ ቻይናዊ ክሱ እንደቀረበባቸው የተባለውን ድርጊት እንዳልፈፀሙ ገልፀው ታዋቂውን ኢትዮጵያዊ የህግ ባለሙያ አቶ ደረጀ ደምሴን ጠበቃቸው አድርገው ሲሟገቱ ቆይተዋል፡፡ ጉዳዩ ትላንት በጁሪ ከታየ በኋላ ተከሳሹ ነፃ መሆናቸው ተገልፆላቸዋል፡፡

ይህ ውሳኔ ከተሰማ በኋላ የአሜሪካ መንግስት አቃቤ ህግ በመሆን ሲሟገቱ የቆዩት ሊህ ፎሊ ‹‹የጁሪውን ውሳኔ እናከብራለን፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ክሳችንን አቋርጠናል›› ብለዋል፡፡ የተከሳሹ ጠበቃ አቶ ደረጄ ደምሴ እንደገለፁት ይህ ክስ የቀረበባቸው ቻይናዊ በቦስተን የሚገኘው የአሜሪካዊ ቻይናዊያን ኮሚኒቲ አስተባባሪና አክቲቪስት ናቸው፡፡

ብዙውን ጊዜ የቻይናን አንድነት ማለትም የታይዋንን መጠቃለል የተመለከቱ አስተያየቶችን እንደሚሰጡ የጠቀሱት አቶ ደረጄ ይህ ሀሳብ ከቻይና መንግስት አቋም ጋር ስለሚመሳል ብቻ የቻይና ሰላይ ተብለው መከሰሳቸውን አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም ይህ ክስ የሰዎችን የመናገር ነፃነትን የሚገድብና ሌሎች ሰዎችን ለማስፈራራት ሲባል የቀረበ መሆኑን በመግለፅም ተከራክረዋል፡፡

ክርክሩን የተመለከቱት የጁሪ አባላትም የአቶ ደምሴን ሙግት ተቀብለው ተከሳሹ ላይ የቀረበው ክስ ውቅድ መሆን እንዳለበት ውሳኔ ካሳለፉ በኋላ ቻይናዊው ተከሳሽ ‹‹ትክክለኛ ፍትህ ዛሬ አግኝቻለሁ›› በማለት መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
(ዘ-ሐበሻ ዜና)
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig


የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ግዴታ ሆኗል‼️

በአካል ኢትዮጵያ ውስጥ የማይገኙ ዜጎችና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንደ ዩናይት ዶት ኢቲ ያሉ አማራጮችን ተጠቅመው ፋይዳን ሳይዙ የባንክ አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉ ተገልጿል።

በቅርቡ በአዲስ አበባ የሚገኙ ሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንደ ቅደመ ሁኔታ ተግባራዊ እንዲያደርጉ ብሔራዊ ባንክ አቅጣጫ ማስቀመጡን ያስታወሰው መረጃው ይህው አሰራርም በውጭ የሚኖሩ ዜጎችን እንዲያካትት መደረጉን ነው የተናገረው።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን መያዝ በሀገር ውስጥ የሚገኙ የውጪ ሀገር ዜጎችንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን የሚያጠቃልል መሆኑ ጭምር የተገለፀ ሲሆን መመሪያው በብሔራዊ ባንክ መውጣቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ መሥሪያ ቤት በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
#ኢትዮ-መረጃ


የብድር ውል ይፍረስልኝ በሚል ከሚቀርብ ክስ ጋር በተያያዘ የተወሰነ አስተማሪ ጠቃሚ የሰበር ውሳኔ
በጋብቻ መካከል አንደኛው ተጋቢ የውል ግደታ ሲገባ በስምምነት ተሳታፊ ያልሆነ ተጋቢ ውል ይፍረስልኝ ክስ ሊያቀርብ በሚያስችል ልክ ስለውሉ መኖር የተሟላ እዉቀት ሊኖረው ስለሚገባ በአንደኘው ተጋቢ የተደረገ የብድር ውል መኖሩን ሌላኛው ተጋቢ አወቀ ሊባል የሚችለው ቢያንስ የገንዘብ ብድር ዉሉ ከማን ጋር እንደተደረገ፣ የምን ያህል ገንዘብ ብድር ውል እንደሆነ፣ መቼ የተደረገ ውል እንደሆነ ማወቅ ሲችል ነው፡፡በሌላ በኩል በፌደራል የቤተሰብ ህግ አንቀጽ 68/መ እና 69/1 መሰረት የገንዘብ ብድር ውል ሲደረግ ያልተሳተፈ ተጋቢ እንድፈርስ በመጠየቅ ምክንያት ሊያደርግ የሚገባው እና ውሉ እንዲፈርስ ከመወሰኑ በፊት በፍሬ ነገር ደረጃ ሊረጋገጥ የሚገባው በገንዘብ ብድር ውል ግደታው በተዋናይነት አለመሳተፉ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ የብድር ውል ይፍረስልኝ በሚል ከሚቀርብ ክስ ጋር በተያያዘ በብድር ተገኘ የተባለው ገንዘብ ለትዳር ጥቅም ውሏል ወይስ አልዋለም በሚል ጭብጥ ላይ በማከራከርነወ ውሳኔ መስጠት አይቻልም፡፡ ይህ አይነት ክርክር ሊቀርብ የሚገባው የጋብቻ ፍች ተከትሎ በሚደረግ የባል እና ሚስት ንብረት ክፍፍል ጊዜ ነው፡፡ ስለሆነም ፍረድ ቤቶች የብድር ውል ይፍረስልኝ ተብሎ በቀረበ ክስ ክርክር ላይ ለክርክሩ መነሻ የሆነው በብድር የተገኘው ገንዘብ ለትዳር ጥቅም ውሏል ወይስ አልዋለም የሚለውን ጭብጥ ላይ አከራክረው መወሰናቸው ሊታረም የሚገባው የክርክር አመራር ጉድለት ነው ፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅጽ 26 በመ/ቁ 208197
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alehig.com @Alehig


230493 (2).pdf
881.9Kb
የተከራየ መኪና ተከራይ እጅ እያለ በሌላ ሰዉ ንብረት ላይ ጉዳት ካዳረሰ ለደረሰዉ ጉዳት ተጠያቂዉ ተከራይ ብቻ ነዉ።
ስ/መ/ቁ 230493


ከሳሽ ስለሚያሲይዘው የወጪና ኪሳራ ዋስትና ሰ/መ/ቁ. 218235
በፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ከሳሽ በክሱ ተረቺ ቢሆን ለተከሳሽ ወጪና ኪሳራ ለመክፈል ፈቃደኛ ላይሆን ይችላል በሚል ዋስትና እንዲያስይዝ ሊጠየቅ አይገባም። 
የፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 200(1) ለመክፈል አቅም ማጣትን አስመልክቶ የተደነገገ በመሆኑ ለመክፈል አቅሙ ካለ ፍ/ቤቱ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ፍርዱን የሚያስፈፅም በመሆኑ ለመክፈል ፈቃደኛ አለመሆን ከመነሻውም በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 200(1) ዋስትና ለማስጠራት በቂ ምክንያት ተደርጎ የሚወሰድ አይሆንም።
#daniel fikadu


#የውርስ_ንብረት በሆነ ጊዜ ክርክር መኖሩን ቢያውቁም በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ቁ አንቀጽ #358 መሰረት የማቅረብ መብት ያላቸው ስለመሆኑ የተሰጠ የሕግ ትርጉም


ማጠቃለያ💎
በአጠቃላይ ከፍ ሲል አጠር ባለ መልኩ ለማቅረብ ከተሞከረው ጽሁፍ መረዳት እንደሚቻለው የማስታወቂያ ስራዎች ሊከተሏቸው የሚገቡ የሕግ ሁኔታዎች እንዳሉ መረዳት ይቻላል፡፡ ስለሆነም አሁን ላይ እየተስፋፋ ከመጣው የቴክኖሎጂ ተደራሽነት አንፃር ዜጎች በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በማስታወቂያ ስራዎች ውስጥ የሚሳተፉበት ሁኔታ እየሰፋ በመምጣቱ በዚሁ የስራ መስክ የሚሰማሩ ሰዎች ቢያንስ መሰረታዊ የሚባሉ የማስታወቂያ ስራ ሕጎች ላይ በንባብም ሆነ በሌላ መልኩ እራሳቸውን በማብቃት ስራውን ተከትሎ ሊመጡ ከሚችሉ የሕግ ተጠያቂነቶች ራሳቸውን ሊጠብቁ ይገባል፡፡
ፍትህ ሚኒስቴር
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig


ውድድር ማስታወቂያ እንዲሁም የፖለቲካ ድርጅቱ የሚያሰራጨውን የአድራሻ ለውጥ፣ የስብሰባ ጥሪ እና መሰል ማስታወቂያዎችን የሚከለክል አይደለም።)እና ሌሎች በሕግ የተከለከሉ ማስታወቂያዎች፡፡

💎 ገደብ የተደረገባቸው ማስታወቂያዎች
- የአልኮል መጠኑ ከ12 በመቶ በላይ የሆነ ማንኛውንም መጠጥ የሚመለከት ማስታወቂያ ከውጭ ማስታወቂያ እና እለታዊና ሳምንታዊ ካልሆነ ጋዜጣ እና መጽሔት በስተቀር በሌሎች የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገዶች (ማለትም በብሮድካስት አገልግሎት፣ በስልክ አገልግሎት ወይም በፖስታ አገልግሎት የማስራጫ መንገዶች) አማካኝነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ማሰራጨት የተከለከለ ነው፡፡ ሌላው እዚህ ጋር ልብ ሊባል የሚገባው የአልኮል መጠኑ ከ12 በመቶ በላይ የሆነን መጠጥ በውጭ ማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ ለምሳሌ፡- በሕንጻ ወይም በማናቸውም ስትራክቸር ወይም በትራንስፖርት ተሽከርካሪ ላይ በሚፃፍ ወይም በሚለጠፍ፣ በተንጠልጣይ ነገር፣ በፖስተር፣ በስቲከር፣ በብሮሸር፣ ሊፍሌት ወይም በራሪ ወረቀት በመጠቀም ማሰራጨት ቢቻልም በሌላ በኩል ደግሞ እንደ የኤሌክትሮኒክ ስክሪን፣ በድምፅ ማጉያ፣ የድምፅ ካሴት ወይም በሌላ በምስልና በድምፅ በሚሰራጭ የውጭ ማስታወቂያ መንገዶች ማሰራጨት አይቻልም፡፡ ሌላው ማንኛውም የአልኮል መጠጥ ማስታወቂያ የአልኮል መጠጡን መውሰድ ለጤና ተስማሚ እንደሆነ፣ ግላዊ ወይም ማኅበራዊ ስኬትን እንደሚያስከትል፣ የተሻለ ሥነ ልቦናዊ ወይም አካላዊ ብቃት እንደሚያስገኝ ወይም ፈዋሽ እንደሆነ የሚገልጽ ወይም በተደጋጋሚ ወይም ከልክ በላይ እንዲጠጣ የሚገፋፋ፤ ከአልኮል ሱስ መጠበቅን የሚያጣጥል ወይም የሚቃወም፣ አካለ መጠን ያልደረሰ ልጅ ላይ ትኩረት የሚያደርግ ወይም አካለ መጠን ያልደረሰ ልጅን የማስታወቂያው ተዋናይ አድርጎ የሚጠቀም፤ ወይም ሌላ መሰል መልእክት የሚያስተላልፍ መሆን የለበትም፡፡ በተጨማሪም የአልኮል መጠጥ የውጭ ማስታወቂያ ከልጆች መዋያ ማዕከል፣ ከትምህርት ቤት፣ ከህክምና ወይም ታሪካዊ ተቋም፣ ከሲኒማ ቤት፣ ከቲያትር ቤት ወይም ከስታዲየም በመቶ ሜትር ራዲየስ ውስጥ እንዲቀመጥ መደረግ የለበትም፡፡

የሕግ ተጠያቂነት💎💎
የማስታወቂያ ስራ ሊከተለው የሚገባ ህግና ስርዓት ያለው እንደመሆኑ ህግና ስርዓቱን ባልጠበቀ መልኩ የማስታወቂያ ስራ ላይ መሰማራትም ሆነ ማሰራጨት አስተዳደራዊ፣ ፍትሀ ብሔራዊና የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ሲሆን በዚህ ፅሁፍ ከወንጀል አንፃር ሊኖር የሚችለውን የህግ ተጠያቂነት ሁኔታ እንደሚከተለው ተዳሷል፡-
- በአዋጅ ቁጥር 759/2004 አንቀፅ 34/1/ሀ/ መሰረት አንድ ሰው በአዋጁ አንቀፅ 5/1/ እና/2/ መሰረት በማስታወቂያ ስራ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችለውን ፍቃድ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ሳያገኝ በማስታወቂያ ስራ ላይ የተሰማራ እንደሆነ በንግድ ምዝገባና ፍቃድ አዋጅ አንቀፅ 49/2/ መሰረት ለስራው የሚጠቀምበት መሳሪያ መወረስን ጨምሮ ከብር 150ሺ እስከ 300ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እና ከ7ዓመት እስከ 15ዓመት በሚደርስ የፅኑ እስራት ሊቀጣ ይችላል፡፡
- ከይዘትና ስርጭት አንፃር በመገናኛ ብዙሀን የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች ከሌሎች ፕሮግራሞች የተለየ መሆኑ በግልፅ በሚታወቅ መልኩ እና በዜና መልክ ባልተዘጋጀ መልኩ መቅረብ ያለበት መሆኑን፣ የማስታወቂያ ወኪል የአንድን ሰው ምርት፣ አገልግሎት ወይም ሌላ መልእክት የሚያስተዋውቅ የንግድ ማስታወቂያ አዘጋጅቶ ባሰራጨ በሦስት ወራት ውስጥ የሌላ ሰውን ተመሳሳይ ምርት፣ አገልግሎት ወይም ሌላ መልእክት በተመሳሳይ የማስታወቂያ ተዋናይ ምስል ወይም ድምፅ አዘጋጅቶ ማሰራጨት የለበትም በማለት በአዋጁ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ (2)(3) እና(4) የተደነገጉትን መተላለፍ፣ በአዋጁ አንቀፅ 26(3) ስር 12 በመቶ በላይ የአልኮል መጠን ያላቸውን መጠጦች የማስታወቂያ ስርጭት በተመለከተ የተቀመጡ ገደቦችን መተላለፍ ደግሞ በአዋጁ አንቀፅ 34/1/ለ/ መሰረት ከብር 10ሺ በማያንስና ከብር 100ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ተደንግገዋል፡፡
- በአዋጁ አንቀፅ 6/1/ ስር የተዘረዘሩት የማስታወቂያ ይዘት የተመለከቱ ክልከላዎችን መተላለፍ፣ ህግን ወይም መልካም ስነምግባርን የሚፃረሩ እንዲሁም አሳሳች ወይም ተገቢ ያልሆኑ ማስታወቂያዎች ተብለው በህጉ የተደነገጉትን ማስታወቂያዎች ሰርቶ ማሰራጨት፣ በአዋጁ አንቀፅ 26(1)፣(2) እና (4) የተጠቀሱትን ክልከላዎች በመተላለፍ የአልኮል ይዘታቸው ከ12 በመቶ በላይ የሆኑ መጠጦችን ከተፈቀደው የማስታወቂያ መንገድና ቦታ ውጭ ማስተዋወቅ ከ20ሺ ብር በማያንስና ከብር 150ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡
- በአዋጁ አንቀፅ 25/1/ ስር የተመለከቱትን በህግ ክልከላ የተደረገባቸውን ማስታወቂያዎች ማሰራጨት ደግሞ ከ30ሺ ብር በማያንስና ከብር 250ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡
- በአዋጁ አንቀፅ 34/2/ መሰረት ከፍ ሲል ከተመለከተው የገንዘብ መቀጮ በተጨማሪ ጥፋተኛ የሆነው ሰው ከሕገ ወጥ ማስታወቂያ ሥራው ያገኘው ገቢ ይወረሳል፡፡
ከቅጣት ጋር በተያያዘ ሌላው ከግንዛቤ ልናስገባው የሚገባው ጉዳይ በአዋጁ ላይ በዝርዝር የተጠቀሱት ሌሎች ሁኔታዎች ማለትም የተለየ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ስለሚያስፈልገው ማስታወቂያ፣ አካለመጠን ያልደረሰ ልጅን ስለሚመለከት ማስታወቂያ፣ ስለፀረ አረም ወይም ፀረ ተባይ በተመለከተ የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች ወዘተ በተመለከተ የተጠቀሱ ዝርዝር ሁኔታዎችን አለማሟላት በአዋጁ አንቀፅ 34 መሰረት የሚያስቀጡ መሆናቸውን መገንዘብ የሚገባ ሲሆን፡፡ በተጨማሪም ከፍ ሲል ያየናቸው በአዋጁ ላይ ተጠቅሰው የሚገኙት ቅጣቶች ተፈፃሚ የሚሆኑት ድርጎቶቹ በሌላ ህግ የበለጠ የማያስቀጡ እንደሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት ድርጊቱ በሌላ ህግ በአዋጁ ከተገለፀው የቅጣት መጠን በላይ የሚያስቀጣ በሆነ ጊዜ ለጉዳዩ የምንጠቀመው የበለጠ የሚያስቀጣውን ህግ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ በአዋጅ ቁጥር 759/2004 አንቀፅ 8(12) መሰረት በትክክለኛ ዋጋው እየተሸጠ ያለን ምርት ወይም አገልግሎት በነጻ እየተሰጠ ወይም በቅናሽ እየተሸጠ እንደሆነ አድርጎ የሚያቀርብ ማስታወቂያ አሳሳች ወይም ተገቢ ያልሆነ ይዘት ወይም አቀራረብ እንዳለው ማስታወቂያ ይቆጠራል፡፡

በአዋጁ አንቀፅ 34(1)(ሐ) መሰረት ደግሞ መሰል አሳሳች ይዘት ያለው ማስታወቂያ ማሰራጨት ከ20ሺ ብር በማያንስና ከብር 150ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡ በሌላ በኩል በዚሁ ተመሳሳይ ጉዳይ ላይ የንግድ ስራ እና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 አንቀፅ 22(4)(5) መሰረት የንግድ እቃዎችንና አገልግሎቶችን በማስታወቂያ እንደተነገረላቸው አለመሸጥ፣ ስለዋጋ ቅናሽ አሰተኛ ወይም አሳሳች መረጃ መስተላለፍ በአዋጁ አንቀፅ43/3/ ተጠቃሎ ሲታይ ስለ ዋጋ ቅናሽ አሰተኛ ወይም የተሳሳተ መረጃ ማስተላለፍ(ማስተዋወቅ) የአመታዊ ሽያጭ ገቢውን ከ5 እስከ 10 በመቶ የገንዘብ ቅጣት እና ከ1 ዓመት እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንደሚያስቀጣ ይደነግጋል፡፡ ይሄም ከፍ ሲል በአዋጅ ቁጥር 759/2004 አንቀፅ 34/1/ሐ/ ከተጠቀሰው የቅጣት መጠን ከፍ የሚል በመሆኑ መሰል የዋጋ ቅናሽን በተመለከተ የሚቀርቡ ሀሰተኛ ማስታወቂያዎች ሲሰሩ ክስ ሊቀርብ የሚገባው በንግድ ስራና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ መሰረት ሊሆን እንደሚገባ መረዳት ያስችላል፡፡


የማስታወቂያ ሕግ⚠️🔽
በዓለም እንዲሁም በሀገራችን እየተስፋፋ የመጣው የዲጂታል ኮሚውንኬሽን ቴክኖሎጂ ሰዎች የሚሰሩትን ምርትም ሆነ አገልግሎት ለሌሎች ሰዎች ተደራሽ ለማድረግና ለማስተዋወቅ እጅግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል፡፡ አሁን አሁን መደበኛ በሚባሉት የሚዲያ ማስራጫዎችና ከዚህ ቀደም ከተለመዱት የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገዶች በተጨማሪ የኢንተርኔት ድረ ገፅ (ቲክቶክና ፌስቡክ በመሳሰሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች) ዋነኛ የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ መሆን ጀምረዋል፡፡
⚠️
የማስታወቂያ ሕግን አለማወቅ እና በሂደቱም የሚፈፀሙ የሕግ ጥሰቶች ተጠያቂነት እንደሚያስከትሉ ተገንዝቦ ዘርፉ የሚፈልገውን ተገቢውን እውቀት እና የሚገዛበትን የሕግ ማዕቀፍ ጠንቅቆ ማወቁ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ከሚመጣብን ተጠያቂነት ሊታደገን ስለሚችል ተገቢውን ትኩረት መስጠት ይገባናል፡፡

🔽🕯📈⁉️
የማስታወቂያ ስራዎች የሚመሩበት ዋነኛው የሕግ ክፍል የሚገኘው በአዋጅ ቁጥር 759/2004 በተደነገገው አግባብ ነው፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ የማስታወቂያ ምንነት እና ዓላማ፣ በማስታወቂያ ስራ ለመሰማራት ሊሟሉ የሚገባቸው ቅድመ-ሁኔታዎች፣ የማስታወቂያዎች ይዘትና አቀራረብ፣ ክልከላና ገደብ የተደረገባቸው የማስታወቂያ ዓይነቶች እና የሕግ ተጠያቂነት የሚሉትን ጉዳዮች በአጭሩ ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

የማስታወቂያ ምንነት እና ዓላማ
ማስታወቂያ ማለት አንድን ምርት፣ አገልግሎት፣ ክስተት ወይም ሀሳብ ለህዝብ ለማስተዋወቅ እና ፍላጎት ለመፍጠር የሚደረግ ማንኛውም ጥረት ነው። ይህም በተለያዩ መንገዶች ሊከናወን ይችላል:: ለምሳሌ፡- በህትመት ሚዲያ (ጋዜጦች፣ መጽሔቶች፣ እና ብሮሸሮች)፤ በኤሌክትሮኒክ ሚዲያ (ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ እና ኢንተርኔት)፤ በማህበራዊ ሚዲያ (📱ፌስቡክ፣ ትዊተር📱፣ ኢንስታግራም📱፣ ቲክቶክ📱 እና ሌሎችም)፤ በውጭ ማስታወቂያዎች (ቢልቦርዶች፣ ፖስተሮች እና ሌሎችም) እና በቀጥታ ግንኙነት (ስልክ፣ ኢሜይል፣ እና ፊት ለፊት ውይይት) መንገዶች የማስታወቂያ ስራ ሊሰራ ይችላል፡፡

በአዋጅ ቁጥር 759/2004 አንቀጽ 2/1/ ድንጋጌ መሠረት ማስታወቂያ ማለት የምርት ወይም የአገልግሎት ሽያጭ እንዲስፋፋ ወይም ስም፣ አርማ፣ የንግድ ምልክት ወይም ዓላማ እንዲተዋወቅ በማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ አማካኝነት የሚሰራጭ የንግድ ማስታወቂያ ሲሆን የሕዝብ አገልግሎት ማስታወቂያንና የግል ማስታወቂያን ይጨምራል፡፡ በሕጉ መሰረት የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገዶች የሚባሉት ደግሞ፡- መገናኛ ብዙሃንን፣ የውጭ ማስታወቂያን፣ የቴሌኮምን፣ የፖስታ፣ የኢንተርኔት ድረ ገፅ እና የፋክስ አገልግሎቶችን፣ ሲኒማን፣ ፊልምን፣ ቪዲዮን እና መሰል የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድን እንደሚጨምር ተደንግጎ ይገኛል፡፡
የማስታወቂያ ዓላማ ሰዎችን ስለ አንድ ነገር ማሳወቅ፣ ፍላጎት መፍጠር፣ እና ሽያጭ ማሳደግ ነው። ውጤታማ ማስታወቂያ ግልጽ፣ አጭር፣ እና ትኩረት የሚስብ መሆን አለበት።

በማስታወቂያ ስራ ለመሰማራት ሊሟሉ የሚገባቸው ቅድመ-ሁኔታዎች
በማስታወቂያ ስራ ላይ ሊሰማሩ የሚችሉ ሰዎችን በተመለከተ ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት የሚገባቸው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የመጀመርያው ቅድመ-ሁኔታ ዜግነት ነው፡፡ የማስታወቂያ አዋጁ በአንቀጽ 4(1) እና (2) ስር በግልጽ እንዳስቀመጠው በማስታወቂያ ስራ ላይ ለመሰማራት ፈቃድ ጠያቂው ግለሰብ ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ መሆን ያለበት ሲሆን ፍቃድ ጠያቂው ሕጋዊ ሰውነት ያለው አካል በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ በኢትዮጵያ ሕግ መሰረት የተቋቋመና በካፒታሉ ውስጥ የውጭ አገር ዜጋ ድርሻ የሌለበት የንግድ ማኅበር መሆን ይጠበቅበታል፡፡ በሌላ ሀገር ዜግነት የተሰጣቸው በትውልድ ኢትዮጵያዊ የሆኑ የውጪ አገር ዜጋ በማስታወቂያ ስራ ላይ የመሰማራት መብት ያላቸው መሆኑን ከአዋጁ መገንዘብ ይቻላል፡፡
ይሁንና ኢትዮጵያዊ መሆን ብቻውን የማስታወቂያ ወኪል ወይም አስነጋሪ ለመሆን ያስችላል ማለት ግን አይደለም፡፡ ይልቁንም በማስታወቂያ ስራ ላይ ለመሰማራት አግባብ ካለው የመንግስት አካል ሕጋዊ ፈቃድ ማግኘት እንደሚገባ በአዋጁ አንቀፅ 5 ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ማንኛውም ማስታወቂያ አሰራጭ ማስታወቂያ በማዘጋጀት ሥራ ላይ ለመሰማራት አግባብ ካለው የመንግስት አካል የማስታወቂያ ሥራ ፈቃድ ማውጣት አለበት፡፡ ይሄም ማለት አሁን አሁን በስፋት እየተለመደ የመጣው በኢንተርኔት ድረ ገፅ እና እንደ ቲክቶክና ፌስቡክ ባሉ መሰል የማስራጫ መንገዶች ላይ ማስታወቂያዎችን በክፍያ እንደሚሰሩ በመግለፅ ብዙ ተከታይ ባላቸው የማህበራዊ ድህረ ገፆቻቸው ላይ አድራሻ በማስቀመጥና የቪዲዮ፣ የፊልም ወይም የሲኒማን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ከሚመለከተው አካል ምንም ዓይነት የማስታወቂያ ስራ ፍቃድ ሳይወስዱ የማስታወቂያ ስራዎችን መስራት የሕግ ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል የሚያስገነዝብ ነው፡፡ የማስታወቂያ ፍቃድን በተመለከተ ሌላው ልብ ሊባል የሚገባው ነጥብ ምርቱ፣ አገልግሎቱ ወይም ሌላ መልዕክት እንዲተዋወቅለት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው የማስታወቂያ ሥራ ፈቃድ ማውጣት ሳያስፈልገው የራሱን ማስታወቂያ አዘጋጅቶ ማሰራጨት ወይም ማስታወቂያውን አዘጋጅቶ በማስታወቂያ አሰራጭ አማካኝነት እንዲሰራጭለት ማድረግ ይችላል፡፡

የማስታወቂያዎች ይዘትና አቀራረብ
በአዋጁ አንቀፅ 6 መሰረት የማስታወቂያዎች ይዘትና አቀራረብ ተከታዮቹን ነጥቦች ከግምት ያስገባ መሆን ይኖርበታል፡፡ እነሱም፡-

- ማንኛውንም ሕግ ወይም መልካም ሥነ-ምግባር የማይፃረር፣ አሳሳች ወይም ተገቢ ካልሆነ አገላለጽ ነፃ የሆነ፣ የሕብረተሰቡን ማህበራዊና ባህላዊ እሴት የሚያከብርና የሸማቹን ሕጋዊ ጥቅም የማይጎዳ፣ የሚተዋወቀውን ምርት ወይም አገልግሎት እውነተኛ ባህሪ፣ ጥቅም፣ ጥራትና ሌላ መሰል መረጃዎችን የሚገልጽ፣ የሌሎችን ሰዎች ምርት ወይም አገልግሎት የማያንቋሽሽ እና የአገርን ክብርና ጥቅም የሚጠብቅ እንዲሁም የሙያ ሥነ-ምግባርን የሚያከብር ይዘትና አቀራረብ ያለው መሆን አለበት፡፡

- በተጨማሪም ከይዘት አንፃር በመገናኛ ብዙኃን የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች ከሌሎች ፕሮግራሞች የተለየ መሆኑ በግልፅ በሚታወቅ መልኩ እና በዜና መልክ ባልተዘጋጀ መልኩ መቅረብ ያለበት ሲሆን፡፡ በተጨማሪም የማስታወቂያ ወኪል የአንድን ሰው ምርት፣ አገልግሎት ወይም ሌላ መልእክት የሚያስተዋውቅ የንግድ ማስታወቂያ አዘጋጅቶ ባሰራጨ በሦስት ወራት ውስጥ የሌላ ሰውን ተመሳሳይ ምርት፣ አገልግሎት ወይም ሌላ መልእክት በተመሳሳይ የማስታወቂያ ተዋናይ ምስል ወይም ድምፅ አዘጋጅቶ ማሰራጨት የለበትም::

🚫 ክልከላ የተደረገባቸው ማስታወቂያዎች
የሚከተሉትን ማስታወቂያዎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በማንኛውም የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገድ አማካኝነት ማሰራጨት የተከለከለ ነው፡-
- አግባብ ባለው የመንግስት አካል በአደንዛዥ እፅነት የተመደበን ማንኛውንም እፅ የሚመለከት ማስታወቂያ፤ ያለሐኪም ትእዛዝ የማይሰጥ ወይም በጥቅም ላይ የማይውል መድሀኒትን ወይም የሕክምና መገልገያን ተጠቃሚው በቀጥታ እንዲጠቀም የሚገፋፋ ማስታወቂያ፤ ናርኮቲክ መድሐኒትን ወይም ሳይኮቴራፒክ ንጥረ ነገርን የሚመለከት ማስታወቂያ፤ የጦር መሳሪያ ማስታወቂያ፤ የቁማር ማስታወቂያ፤የሕገ ወጥ ምርት ወይም አገልግሎት ማስታወቂያ፤ የአራጣ አበዳሪ ማስታወቂያ፤ የጥንቆላ ማስታወቂያ፤ የሲጋራ ወይም የሌሎች የትምባሆ ውጤቶች ማስታወቂያ፤ የፖለቲካ ግብ ያለው ማስታወቂያ(ነገር ግን አግባብ ባለው ሕግ መሠረት ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የምርጫ እጩ ተወዳዳሪ በምርጫ ወቅት የሚያሰራጨውን የምርጫ


አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ዜጋዋን አፍና ገደለች


ግለሰቡ የሁለት ልጆች እናት የሆነች ሴትን አስገድዶ ከደፈረ በኋላ ገድሏታል ተብሏል


የ14 ዓመት ታዳጊ በመድፈር ወንጀልም ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘው ይህ አሜሪካዊ በናይትሮጅን ጋዝ ታፍኖ እንዲሞት ተደርጓል


ተጨማሪ ያንብቡ https://am.al-ain.com/article/alabama-killed-a-rapist-by-nitrogen-gas




በሞት የተለዩ ተጠርጣሪዎችን ንብረት እንዲወረስ የሚያደርገው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ተግባራዊ ሊደረግ ነው‼️
ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ ተጠርጣሪው በሞት ቢለይ ወይም ከሀገር የሸሸ ቢሆንም ንብረቱ  እንዲታገድና ጉዳዩ ተጣርቶ ግለሰቡ በሌለበት እንዲወረስ እንደሚደረግ ተገለፀ፡፡

በአዲሱ የንብረት ማስመለስ አዋጅ  በጥፋተኝነት ላይ ያልተመሰረተ የንብረት ማስመለስ አዋጁ እንደሚያካትት ሲገለፅ  ይህም ተጠርጣሪው በሞት ቢለይ ወይም ከሀገር የሸሸ ቢሆን ንብረቱ እንዲሁ የሚቀር ሳይሆን እንዲታገድና ጉዳዩ ተጣርቶ ግለሰቡ በሌለበት እንዲወረስ ይደረጋል ሲል ፍትህ ሚኒስትር አስታውቋል።

የጸደቀው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ተፈጻሚ ሲሆንም  ምክንያታዊ ያልሆኑ ክሶች እንዳይመጡ ተጠርጣሪው ግለሰብ ስለ ጉዳዩ ቀርቦ እንዲያስረዳ ዕድል የሚሰጥና በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብቻ ተፈጻሚ የሚሆን ነውም ብሏል።

አዋጁ በህገ-ወጥ መንገድ በወንጀል የተገኘ ንብረትን በአግባቡ በማስመለስ የሀገርንና የህዝብን ሀብት ከወንጀል ለመጠበቅ የሚሰራበት ነው ተብሏል።

የማይመለስ ጉዳት ማለትም ንብረቱ ከሃገር ሊሸሽና ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳት ደርሶ ከሆነ ጊዜያዊ እግድ በራሱ በፍትህ ሚኒስቴር ያለፍርድቤት ትዕዛዝ እንደሚሰጥም ተገልጿል።

አዋጁ አንድ ግለሰብ በቅን ልቦና ባለማወቅ ንብረቱ ህገ-ወጥ መሆኑን ሳያውቅ የገዛ ቢሆን ንብረቱ እንዳይወረስ ተገቢውን ጥበቃ የሚሰጥ ነው ተብሏል።

በአዋጁ ላይ በተደነገገው መሰረትም ህገ-ወጥ ንብረት በማፍራት የተጠረጠረ ሰው ያለደረሰኝ በሰውም ሆነ ሌሎች ያስረዱልኛል ባላቸው ማስረጃዎች ጥፋተኛ አለመሆኑን ማስረዳት የሚያስችል መመሪያ እንዳለውም ተነስቷል።

አዋጁን ለማስፈጸም ከተለያዩ ሀገራት ጋር በትብብር የሚሰራ ሲሆን  ንብረቱ ኢትዮጵያ ቢሆንም በውጭ ሀገራት በህገ-ወጥ መንገድ የተገኘ መሆኑ ከተረጋገጠ ለማስመለስ የሚሰራበት ነው ተብሏል።
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig


capital market amharic.pdf
268.2Kb
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን መግለጫ ለባለ አክስዮን ማህበሮች

ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig


#እንድታውቁት 📣❗️🆕

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን በሽያጭ የተሽከርካሪ ስም ዝውውር ለማድረግ ሊሟሉ እሚገባቸው ጉዳዮች ብሎ የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጧል።

በዚህም በሽያጭ የተሽከርካሪ ስም ዝውውር ለማድረግ፦

1. በተሽከርካሪው ላይ የተላለፈ ማንኛውም ዓይነት እዳ እና እገዳ እንዲሁም ቀረጥ ያለበት ከሆነ የስምምነት ደብዳቤ መኖሩን ማረጋገጥ፣

2. ኮድ 01 እና ኮድ 03 ከሆነ ከገቢዎች የግብር ክሊራንስ መቅረቡን

3. የዘመኑን ዓመታዊ የቴክኒክ ምርመራ/ቦሎ፤ ያደረገ መሆኑን፤

4. የጸደቀ የውልና ማስረጃ ሰነድና የስም ዝውውር 2% የከፈለበት ማስረጃ መኖሩን፣

5. የንግድ ተሽከርካሪ ከሆነ አንዱ የግምት ውጤት ለሀገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን ይላካል፤ ሁለተኛውን የግምት ውጤት ሁለቱ ተዋዋዮች ውል መፈፀም የሚችሉ ለመሆኑ በሸኚ ደብዳቤ ለሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት የተላከበት ሰነድ፤

6. የቤት ተሸከርካሪ ከሆነ የግምት ውጤቱን በቀጥታ ሰሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ የተላከበት ሰነድ፤

7 . የገዢ ሁለት ፎቶ ግራፍ

8. የስም ዝውውርና የአገልግሎት ለውጥ የሚያደርግ ከሆነ ተሸከርካሪው በድጋሚ ለቴክኒክ ምርመራ ብቃት ማረጋገጫ ሲቀርብ እገልግሎቱ ይሰጣል ሲል አስቀምጧል።

በተጨማሪም ቢሮው በዚሁ መረጃው ላይ በሰጠው ማሳሰቢያ፦

1. የሚገዙት ተሽከርካሪ የሻንሲና ምተር ቁጥር ትክክለኛነት የማረጋገጥ፣

2. የተሚገዙት ተሽከርካሪ ሊብሬና ተሽከርካሪ ስለያዙ እና ዉክልና ስለተሰጦት ብቻ ሀጋዊ ተሽከርካሪ ማለት ስላልሆነ የሚገዙት ተሽከርካሪ በተመዘገበበት ቅ/ጽ/ቤት ትክክለኛነቱ መረጋገጥ አለበት ሲል ገልጿል።
#tikvahethmagazine
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp📱 #+251920666595
Telegram📱 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ


ካርታ ማምከን ማለት የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ /ደብተር ወይም ካርታ/ በመሰረዝ ዋጋ የማሳጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ነው።
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp📱 #+251920666595
Telegram📱 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ

19 last posts shown.