በሰሜን ጎንደር ዞን የፅንፈኛው አመራሮች እና ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ በመምረጥ እጃቸውን ሰጡ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ጎንደር እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዳባት ፣ወገራ ወረዳና አካባቢው ራሳቸውን በብርጌድ አደረጃጀት ሰይመው ሲንቀሳቁሱ የነበሩ የፅንፈኛው ቡድን አመራሮች እና አባላቱ ለሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮር የሠራዊት አባላት እጃቸውን ሰጥተዋል።
አበበ ገዳሙ እና አዲሰ አዘዘው የተባሉ አመራሮች ከነ አባላቶቻቸው በሰላም እጃቸውን ለሠራዊቱ የሰጡት በማዕከላዊ ጎንደር በአካባቢው ኮማንድ ፓሰት ከህግ ማስከበር ተልዕኮው ጎን ለጎን ሰላምን ለሚፈልጉ ሃይሎች ምህረቱ የሰጠውን የሰላም ጥሪ በጊዜው እንዲጠቀሙ በፈጠረው ምቹ የሰላም መንገድ መሆኑን ገልፀዋል ።
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ተሰማርቶ የሚገኘው ክፍለጦር በአካባቢው የሚገኘውን ፅንፈኛ ሀይል እየደመሰሰ የአካባቢውን ሰላም እያረጋገጠ ይገኛል ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ክፍለጦር አዛዥ ኮሎኔል ስንታየሁ ሰይድ ተናግረዋል።
ክፍለ ጦሩ በተሰጡት የግዳጅ ቀጠናዋች ሁሉ ህዝባዊ ፍቅሩን ሳያላላ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ተናቦ በመሰራት ፅንፈኛ ሀይሉን የገባበት ገብቶ በመምታት እና እጅ የሰጡትን በሰላም በመቀበል ግዳጅን በብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ ዋና አዛዡ አሰረድተዋል።
ህዝቡ በቡድኑ በየጊዜው የሚደርስበትን የመብት ጥሰት እየተረዳን ሲመጣ እና ህዝቡ ከእኛ እየራቀ ድጋፍ አልባ መሆናችን ሲገባን የሰላም ጥሪውን ተቀብለን ከህብረተሰባችን ጋር በይቅርታ ተቀላቅለን ለመሰራት በሰላማዊ መንገድ እጃችንን ሰጥተናል ነው ያሉት።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ጎንደር እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዳባት ፣ወገራ ወረዳና አካባቢው ራሳቸውን በብርጌድ አደረጃጀት ሰይመው ሲንቀሳቁሱ የነበሩ የፅንፈኛው ቡድን አመራሮች እና አባላቱ ለሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮር የሠራዊት አባላት እጃቸውን ሰጥተዋል።
አበበ ገዳሙ እና አዲሰ አዘዘው የተባሉ አመራሮች ከነ አባላቶቻቸው በሰላም እጃቸውን ለሠራዊቱ የሰጡት በማዕከላዊ ጎንደር በአካባቢው ኮማንድ ፓሰት ከህግ ማስከበር ተልዕኮው ጎን ለጎን ሰላምን ለሚፈልጉ ሃይሎች ምህረቱ የሰጠውን የሰላም ጥሪ በጊዜው እንዲጠቀሙ በፈጠረው ምቹ የሰላም መንገድ መሆኑን ገልፀዋል ።
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ተሰማርቶ የሚገኘው ክፍለጦር በአካባቢው የሚገኘውን ፅንፈኛ ሀይል እየደመሰሰ የአካባቢውን ሰላም እያረጋገጠ ይገኛል ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ክፍለጦር አዛዥ ኮሎኔል ስንታየሁ ሰይድ ተናግረዋል።
ክፍለ ጦሩ በተሰጡት የግዳጅ ቀጠናዋች ሁሉ ህዝባዊ ፍቅሩን ሳያላላ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ተናቦ በመሰራት ፅንፈኛ ሀይሉን የገባበት ገብቶ በመምታት እና እጅ የሰጡትን በሰላም በመቀበል ግዳጅን በብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ ዋና አዛዡ አሰረድተዋል።
ህዝቡ በቡድኑ በየጊዜው የሚደርስበትን የመብት ጥሰት እየተረዳን ሲመጣ እና ህዝቡ ከእኛ እየራቀ ድጋፍ አልባ መሆናችን ሲገባን የሰላም ጥሪውን ተቀብለን ከህብረተሰባችን ጋር በይቅርታ ተቀላቅለን ለመሰራት በሰላማዊ መንገድ እጃችንን ሰጥተናል ነው ያሉት።