በብርሸለቆ ጊዚያዊ መሰረታዊ ዉትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት 129ኛዉ የአድዋ ድል በአል በድምቀት ተከብሯል።
በስልጠና ላይ የሚገኙ የ33ኛ ዙር ምልምል ፖሊሶች 129ኛውን የአድዌ ድል መታሰቢያ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል።
ዕለቱን አስመልክቶ በተሰናዳው ዝግጅት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ምክትል ዋና ዳሬክተርና የ33ኛ ዙር የስልጠና አስተባባሪ ኮማንደር አብዩት ሽፈራዉ አባቶቻችን የጣሊያንን ወራሪ ያምበረከኩት በአንድነትና በነደደ ሀገራዊ ፍቅር በመሆኑ ለጥቁር ህዝቦች ኩራት የሆነውን ድል ያስመዘገቡበትን መንገድ ለመከተል አንድነታችንን በማጠናከር ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የዝግጅቱ ተሳታፊ ሰልጣኞች በበኩላቸው በክልላችን የተፈጠረውን የዘረፋና የዉብድና ሀገር አፍራሽ ቡድን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አከርካሪውን በመስበርና በማስወገድ ታፍራና ተከብራ የምትኖረዉን ታላቋን ሀያል ሀገር ኢትዮጵያን ለማፅናት የሚጠበቅብንን ታሪካዊ ኀላፊነት እንወጣለን ብለዋል።
በአዓሉ በተለያየ ትሪዒት ድራማና ስነ ፅሁፍ በድምቀት ተከብሯል።
ዘገባው ፦ የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ የህዝብ ግንኙነት ነው።
ከብርሸለቆ
በስልጠና ላይ የሚገኙ የ33ኛ ዙር ምልምል ፖሊሶች 129ኛውን የአድዌ ድል መታሰቢያ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል።
ዕለቱን አስመልክቶ በተሰናዳው ዝግጅት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ምክትል ዋና ዳሬክተርና የ33ኛ ዙር የስልጠና አስተባባሪ ኮማንደር አብዩት ሽፈራዉ አባቶቻችን የጣሊያንን ወራሪ ያምበረከኩት በአንድነትና በነደደ ሀገራዊ ፍቅር በመሆኑ ለጥቁር ህዝቦች ኩራት የሆነውን ድል ያስመዘገቡበትን መንገድ ለመከተል አንድነታችንን በማጠናከር ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የዝግጅቱ ተሳታፊ ሰልጣኞች በበኩላቸው በክልላችን የተፈጠረውን የዘረፋና የዉብድና ሀገር አፍራሽ ቡድን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አከርካሪውን በመስበርና በማስወገድ ታፍራና ተከብራ የምትኖረዉን ታላቋን ሀያል ሀገር ኢትዮጵያን ለማፅናት የሚጠበቅብንን ታሪካዊ ኀላፊነት እንወጣለን ብለዋል።
በአዓሉ በተለያየ ትሪዒት ድራማና ስነ ፅሁፍ በድምቀት ተከብሯል።
ዘገባው ፦ የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ የህዝብ ግንኙነት ነው።
ከብርሸለቆ