ወይንኬ አልቦሙ
የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም
በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤
ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፡— የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም፡ አለችው።
ኢየሱስም፡— አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም፡ አላት።
እናቱም ለአገልጋዮቹ፡— የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ፡ አለቻቸው።
አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር።
ኢየሱስም፡— ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው፡ አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው፡ አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ፡—
ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል፡ አለው።
ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ። (ዮሐ 2፥1- 11)
የሰውን ችግር ተረድታ ለልጇ የምታሳስብ፣ ልመናን የምታቀርብ፣ መልስ የምታሰጥን እናት የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁንልን።
ልጆቿ እንድንሆን የረዳን፣ ፍቅሯንም በዕድሜ ዘመናችን ያበዛልን፣ ምስጢሩንም የገለጸልን መድኃኔአለም ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ለዘለዓለም የከበረ፣ የተመሰገነ ይሁንልን።
አማላጅነቷ፣ ጸሎቷ፣ ፍቅሯ፣ በረከቷ ከሁላችንም ጋር ጸንቶ ይኑር!
አሜን!
የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም
በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤
ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፡— የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም፡ አለችው።
ኢየሱስም፡— አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም፡ አላት።
እናቱም ለአገልጋዮቹ፡— የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ፡ አለቻቸው።
አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር።
ኢየሱስም፡— ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው፡ አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው፡ አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ፡—
ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል፡ አለው።
ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ። (ዮሐ 2፥1- 11)
የሰውን ችግር ተረድታ ለልጇ የምታሳስብ፣ ልመናን የምታቀርብ፣ መልስ የምታሰጥን እናት የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁንልን።
ልጆቿ እንድንሆን የረዳን፣ ፍቅሯንም በዕድሜ ዘመናችን ያበዛልን፣ ምስጢሩንም የገለጸልን መድኃኔአለም ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ለዘለዓለም የከበረ፣ የተመሰገነ ይሁንልን።
አማላጅነቷ፣ ጸሎቷ፣ ፍቅሯ፣ በረከቷ ከሁላችንም ጋር ጸንቶ ይኑር!
አሜን!