ሰላምን ለማፅናት ከውስጥ እና ከውጭ ያጋጠሙ ጫናዎችን ከሕዝቡ ጋር ማሸነፍ ተችሏል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
********************
ሰላምን ለማፅናት ከውስጥ እና ከውጭ ያጋጠሙ ጫናዎችን ከሕዝቡ ጋር ማሸነፍ ተችሏል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናግረዋል።
ጨፌ ኦሮሚያ 4ኛ ዓመት 6ኛ የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአዳማ ጨፌ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል።
ርዕሰ መሥተዳድሩ የክልሉን የ6 ወራት የሥራ ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሪፖርት ለጨፌው አቅርበዋል።
ባቀረቡት ሪፖርትም ሰላምን ለማፅናት ከውስጥ እና ከውጭ ያጋጠሙ ጫናዎችን ከሕዝቡ ጋር ማሸነፍ መቻሉን ገልጸው፣ አስፈላጊውን መሥዕዋትነት ከፍለን ሕዝቡን ወደሚፈልገው ሰላም እናሸጋግራለን ብለዋል።
በክልሉ የተለያዩ አከባቢዎች መሳሪያ ታጥቀው ለሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በተደረገው የሰላም ጥሪም ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር አባላት እና አመራሮች ጋር የሰላም ስምምነት መፈረሙ በ6 ወራቱ የተገኘ ውጤት መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሕዝቡ ከዚህ በፊት ቅሬታ የሚያነሣበትን የአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፉን ለማሻሻል እና ጥራት ያለው እና የተደራጀ አገልግሎት ለመስጠት የሪፎርም ሥራ በመሥራት የቀበሌ አረጃጀቶች ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራበት መሆኑንም ነው አቶ ሽመልስ አብዲሳ የገለጹ።
በሐምራዊት ብርሀኑ
********************
ሰላምን ለማፅናት ከውስጥ እና ከውጭ ያጋጠሙ ጫናዎችን ከሕዝቡ ጋር ማሸነፍ ተችሏል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናግረዋል።
ጨፌ ኦሮሚያ 4ኛ ዓመት 6ኛ የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአዳማ ጨፌ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል።
ርዕሰ መሥተዳድሩ የክልሉን የ6 ወራት የሥራ ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሪፖርት ለጨፌው አቅርበዋል።
ባቀረቡት ሪፖርትም ሰላምን ለማፅናት ከውስጥ እና ከውጭ ያጋጠሙ ጫናዎችን ከሕዝቡ ጋር ማሸነፍ መቻሉን ገልጸው፣ አስፈላጊውን መሥዕዋትነት ከፍለን ሕዝቡን ወደሚፈልገው ሰላም እናሸጋግራለን ብለዋል።
በክልሉ የተለያዩ አከባቢዎች መሳሪያ ታጥቀው ለሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በተደረገው የሰላም ጥሪም ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር አባላት እና አመራሮች ጋር የሰላም ስምምነት መፈረሙ በ6 ወራቱ የተገኘ ውጤት መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሕዝቡ ከዚህ በፊት ቅሬታ የሚያነሣበትን የአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፉን ለማሻሻል እና ጥራት ያለው እና የተደራጀ አገልግሎት ለመስጠት የሪፎርም ሥራ በመሥራት የቀበሌ አረጃጀቶች ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራበት መሆኑንም ነው አቶ ሽመልስ አብዲሳ የገለጹ።
በሐምራዊት ብርሀኑ