የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ
***************************
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ከገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ ከብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ፣ ከፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) እና ከሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር የአድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የሥራ ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፖሊሲዎች፣ በኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና በግሉ ዘርፍ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድሎች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝታቸውም አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ልማት ለመደገፍ እና የፖሊሲ ምክክሮችን በማድረግ የማይበገር እና ዘላቂ ሀገራዊ ብልፅግናን ለማምጣት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ በትላንትናው ዕለት ብሔራዊ ቤተ መንግሥትን እና ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልንና ብርሃን የዓይነ ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤትን መጎብኘታቸው ይታወቃል፡፡
***************************
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ከገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ ከብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ፣ ከፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) እና ከሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር የአድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የሥራ ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፖሊሲዎች፣ በኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና በግሉ ዘርፍ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድሎች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝታቸውም አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ልማት ለመደገፍ እና የፖሊሲ ምክክሮችን በማድረግ የማይበገር እና ዘላቂ ሀገራዊ ብልፅግናን ለማምጣት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ በትላንትናው ዕለት ብሔራዊ ቤተ መንግሥትን እና ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልንና ብርሃን የዓይነ ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤትን መጎብኘታቸው ይታወቃል፡፡