ክለቦች የምዕተ ዓመት የዋንጫ ረሀባቸውን ያስታገሱበት (2024/25)
1. ክሪስታል ፓላስ - በ120 ዓመት የክለቡ ታሪክ ማንችስተር ሲቲን በማሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ያነሳበት።
ንስሮቹ ከአሁን በፊት ሁለት ጊዜ በኤፍ ኤ ዋንጫ ለፍጻሜ ቢደርሱም በማንችስተር ዩናይትድ ተሸንፈው ክብሩን ማጣታቸው ይታወሳል።
2. ጎ ኤሄድ ኤግልስ - በኤርዲቪዜው የሚሳተፈው ክለብ የደች ዋንጫን በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ሲያነሳ ዘንድሮ ከ 93 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ሆኗል።
3. ኒውካስል ዩናይትድ - ከተመሰረተ 133 ዓመት የሆነው ኒውካስትል የእንግሊዝ ሊግ ካፕን ለመጀመርያ ጊዜ ያነሳበት ዓመት ሆኗል።ክለቡ ከዋንጫ ጋር ሲገናኝ ደግሞ ከ70 ዓመት በኋላ ነው።
4. ቦሎኛ - በጣልያን ዋንጫ ፍጻሜ ኤሲ ሚላንን በማሸነፍ ከ51 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ነው።
በቀጣይ ሁለት ሳምንት ውስጥ መልስ ሊያገኙ የሚችሉ የረጅም ዓመታት የዋንጫ ጥያቄዎች
• ፒ ኤስ ጂ - በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የፈረንሳዩ ሀብታም ክለብ ኢንተር ሚላን ማሸነፍ ከቻለ ለመጀመርያ ጊዜ የአህጉሩን ትልቁን ክብር የሚያሳካበት ይሆናል።
• ሪያል ቤቲስ - በአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የስፔኑ ክለብ ቼልሲን ካሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የአውሮፓ መድረክ ውድድር ላይ የነገሰበት ይሆናል።
• ቶተንሀም ሆትስፐርስ - በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ ከማንችስተር ዩናይትድ የሚገናኝበትን ፈተና በድል የሚወጣ ከሆነ የ40 ዓመታት የዩሮፓ ሊግ የዋንጫ ድርቁን ያስታግሳል።
• ሀሪ ኬን - በግል ደግሞ የ31 ዓመቱ እንግሊዛዊው ሃሪ ኬን ለመጀመርያ ጊዜ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ዓመት ሆኖለታል።
በአንተነህ ሲሳይ
ኢቢሲ የስፖርት ገፅ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
1. ክሪስታል ፓላስ - በ120 ዓመት የክለቡ ታሪክ ማንችስተር ሲቲን በማሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ያነሳበት።
ንስሮቹ ከአሁን በፊት ሁለት ጊዜ በኤፍ ኤ ዋንጫ ለፍጻሜ ቢደርሱም በማንችስተር ዩናይትድ ተሸንፈው ክብሩን ማጣታቸው ይታወሳል።
2. ጎ ኤሄድ ኤግልስ - በኤርዲቪዜው የሚሳተፈው ክለብ የደች ዋንጫን በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ሲያነሳ ዘንድሮ ከ 93 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ሆኗል።
3. ኒውካስል ዩናይትድ - ከተመሰረተ 133 ዓመት የሆነው ኒውካስትል የእንግሊዝ ሊግ ካፕን ለመጀመርያ ጊዜ ያነሳበት ዓመት ሆኗል።ክለቡ ከዋንጫ ጋር ሲገናኝ ደግሞ ከ70 ዓመት በኋላ ነው።
4. ቦሎኛ - በጣልያን ዋንጫ ፍጻሜ ኤሲ ሚላንን በማሸነፍ ከ51 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ነው።
በቀጣይ ሁለት ሳምንት ውስጥ መልስ ሊያገኙ የሚችሉ የረጅም ዓመታት የዋንጫ ጥያቄዎች
• ፒ ኤስ ጂ - በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የፈረንሳዩ ሀብታም ክለብ ኢንተር ሚላን ማሸነፍ ከቻለ ለመጀመርያ ጊዜ የአህጉሩን ትልቁን ክብር የሚያሳካበት ይሆናል።
• ሪያል ቤቲስ - በአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የስፔኑ ክለብ ቼልሲን ካሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የአውሮፓ መድረክ ውድድር ላይ የነገሰበት ይሆናል።
• ቶተንሀም ሆትስፐርስ - በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ ከማንችስተር ዩናይትድ የሚገናኝበትን ፈተና በድል የሚወጣ ከሆነ የ40 ዓመታት የዩሮፓ ሊግ የዋንጫ ድርቁን ያስታግሳል።
• ሀሪ ኬን - በግል ደግሞ የ31 ዓመቱ እንግሊዛዊው ሃሪ ኬን ለመጀመርያ ጊዜ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ዓመት ሆኖለታል።
በአንተነህ ሲሳይ
ኢቢሲ የስፖርት ገፅ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ