#ኖላዊ ወበግዕ#(እረኛም በግም)
#ትጉህ #እረኛችን #አማኑኤል ከድንግል #ማርያም ተወልዶ በበረት ተኛ።ቅዱስ ዳዊት “እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።”(መዝ 121፥4) ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ በበረት ውስጥ ተኛ።(ሉቃ 2:7)
#እረኛ ሲሆን በግ ፣ በግ ሲሆን እረኛ ነው።መልአኩም በጎቹን (ምዕመናንን) ተግቶ የሚጠብቅ የጌታን ልደት ያበሠረው መንጎቻቸውን ተግተው ይጠብቁ ለነበሩ እረኞች ነው።በእረኛነቱ ይጠብቀናል ፤ በበግነቱም በመስቀል ላይ ተሠውቶልናል (ዮሐ 1:29)።
#የጌታችን እረኛነት ግን ልዩ ነው።እረኛ በጎቹን አስብቶ ኋላ ይበላቸዋል ወይም ሽጧቸው ጥቅም ያገኛል።ይህ እረኛችን ግን ስለ ራሱ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
(ዮሐ 10፥11) ሲል ተናግሯል።
#እርሱ ከሚገኝባት የበጎች በረት (ከቤተክርስቲያን) ያልሆኑ ሌሎች በጎችን አስመልክቶ ሩኅሩኅ እረኛ #መድኃኔዓለም እንዲህ ይላል “ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።”(ዮሐ 10፥16)
#በዓሉን አከባበራችን ሁሉ የተዘክሮተ #እግዚአብሔር ሊሆን ይገባዋል።ስንበላ እውነተኛ መብላችን ክርስቶስ መወለዱን ፤ ስንጠጣም እውነተኛ መጠጣችን አምላካችን መወለዱን ፤ ስንለብስ ስናጌጥም እውነተኛ ልብሳችን ክርሰቶስ መወለዱን ልናስብ ይገባናል።ይህ ካልሆነ ግን ጌታ ለእኛ ያደረገውን ውለታ የዘነጋን ውለተ ቢሶች እንሆናለን።
በዓሉን በዓል የሚያደርገውም የጌታን የፈቃድ ተዋርዶውንና ውለታውን እያሰብን ካመሰገንን ብቻ ነው ፤ እንጂ የምግብና መጠጡ ጉዳይ አይደለም።ይህን #የጌታችን ውለታ ከሚያረሳሱ የቴሌቪዥን መርኃግብሮችን ሁሉ ልንጠነቀቅም ይገባናል!!!
#በዓለ #ልደቱን በተዘክሮ እግዚአብሔር እንድናከብር አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን!!!
#በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ
#ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ!!!
ልደተ #እግዚእ / 2017 ዓ.ም
#ትጉህ #እረኛችን #አማኑኤል ከድንግል #ማርያም ተወልዶ በበረት ተኛ።ቅዱስ ዳዊት “እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።”(መዝ 121፥4) ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ በበረት ውስጥ ተኛ።(ሉቃ 2:7)
#እረኛ ሲሆን በግ ፣ በግ ሲሆን እረኛ ነው።መልአኩም በጎቹን (ምዕመናንን) ተግቶ የሚጠብቅ የጌታን ልደት ያበሠረው መንጎቻቸውን ተግተው ይጠብቁ ለነበሩ እረኞች ነው።በእረኛነቱ ይጠብቀናል ፤ በበግነቱም በመስቀል ላይ ተሠውቶልናል (ዮሐ 1:29)።
#የጌታችን እረኛነት ግን ልዩ ነው።እረኛ በጎቹን አስብቶ ኋላ ይበላቸዋል ወይም ሽጧቸው ጥቅም ያገኛል።ይህ እረኛችን ግን ስለ ራሱ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
(ዮሐ 10፥11) ሲል ተናግሯል።
#እርሱ ከሚገኝባት የበጎች በረት (ከቤተክርስቲያን) ያልሆኑ ሌሎች በጎችን አስመልክቶ ሩኅሩኅ እረኛ #መድኃኔዓለም እንዲህ ይላል “ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።”(ዮሐ 10፥16)
#በዓሉን አከባበራችን ሁሉ የተዘክሮተ #እግዚአብሔር ሊሆን ይገባዋል።ስንበላ እውነተኛ መብላችን ክርስቶስ መወለዱን ፤ ስንጠጣም እውነተኛ መጠጣችን አምላካችን መወለዱን ፤ ስንለብስ ስናጌጥም እውነተኛ ልብሳችን ክርሰቶስ መወለዱን ልናስብ ይገባናል።ይህ ካልሆነ ግን ጌታ ለእኛ ያደረገውን ውለታ የዘነጋን ውለተ ቢሶች እንሆናለን።
በዓሉን በዓል የሚያደርገውም የጌታን የፈቃድ ተዋርዶውንና ውለታውን እያሰብን ካመሰገንን ብቻ ነው ፤ እንጂ የምግብና መጠጡ ጉዳይ አይደለም።ይህን #የጌታችን ውለታ ከሚያረሳሱ የቴሌቪዥን መርኃግብሮችን ሁሉ ልንጠነቀቅም ይገባናል!!!
#በዓለ #ልደቱን በተዘክሮ እግዚአብሔር እንድናከብር አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን!!!
#በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ
#ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ!!!
ልደተ #እግዚእ / 2017 ዓ.ም