ኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀትን በተመለከተ
አንድ ወንድም ከቲክታክ ውይይት ሰማሁት ብሎ የጠየቅኝ ጆሮጅዬን ጭው ነው ያደረገኝ። አንዳንድ ተወያዮች እድገት ያመጡ እና ከፍ ያለ ዕውቀት ላይ የደረሱ እየመሰላቸው ነው መሰል በአብና በወልድ መካከል ገብተው ሁሉ አስተያየት እየሰጡ መሆኑን (የጠየቀኝ ሰው ያለኝን ቃለ በቃል መድገም አልፈለግሁም) ከጥያቄው ተረድቻለሁ። ኪሩቤል ቀና ብለው ወደማያዩት ዙፋን፣ ሱራፌል በሁለት ክንፎቻቸው እግራቸውን በሁለት ክንፎቻቸው ፊታቸውን ሸፍነው ሁለት ክንፎቻቸውን ደግሞ ዘርግተው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ከማመስገን ውጭ ወደ ማይደፍሯት ዙፋን ወይም ገናንነት መግባት የሚፈልግ ሕሊና በፍጥነት በንስሐ መመለስ አለበት ብዬ አምናለሁ።
አንድ ወንድም አንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ነገር ገጥሞት ነበር። ከጓደኛው ጋር ወደ ጎንደር በሔዱበት ወቅት ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራን ሰላም ለማለት በገቡበት ጥያቄ አነሣ። ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች በአንድ አካል ሁለት ባሕርይ የሚሉት ባሕርየ ትስብእት ከባሕርየ መለኮት ጋር ከተዋሐደ ፣ ወልድ ደጎሞ በባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ ስለሆነ እንዴት ሊይድርገው ነው ይላሉ ብሎ ይጠይቃል፤ እንደማስታውሰው ነው። ሊቀ ሊቃውንትም እርሱ ከበደኝ አላለ እናንተን ምን አስጨነቃችሁ ብለው መለሱለት ብሎ የነገረኝን ባስታወስኩ ቁጥር እደነቃለሁ። (በአጻጻፍ የሳትኩት ካለ ሓላፊነቱ የእኔ ነው)። መልሱ ሁልጊዜ ያስደስተኛል። ምክንያቱም በሥላሴ አንድነት ውስጥ ገብታ ቦታ ለማካፈል የምትደፍር ኅሊና እንዴት ያለች ደፋር እና አላዋቂ ናት በእውነት ። ሙሴ እንኳ ወደ ዕፀ ጳጦስ ለመጠጋት ጫማውን እንዲያውልቅ ታዝዞ ነበር። የቀረበውም በረዓድ እና በመንቀጥቀጥ ነበር። ምሳሌው ለተመረጠው ለሙሴ እንኳ እንዲያ የሚያስፈራ ከሆነ አማናዊው የተዋሕዶ ምሥጢርም ይልቁን ምን ያህል ትሕትና እና ጥንቃቄ ይፈልግ ይሆን?
የተገለጠና እና በትክክል የምናውቀው እንኳ ቢሆን እንዲህ ያለው ይዘት በፍጹም ለማኅበራዊ ሚዲያ የሚሆን አይደለም። እውነቱን ለመናገር “የተቀደሰውን ለውሾች አት ስጡን” ለምን አንጠብቀውም የሚለውን እጠይቅና የተቀደሰውን ስለማናውቀው ይሆናል በሚል መልስ እንደገና እቆማለሁ። በርግጥም የምናውቀው አይመስለኝም። ይህ ሁሉ እንግዲህ ኦርቶዶክሳዊውን ነገረ ዕውቀት በመጠቆም ለማሳሰብ እንደ መግቢያ ያነሣሁት ነው።
ሴባስቲያን ብሮክ የሚባለው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የኦሬንታል በተለይም የሶርያ ኦርቶዶክስ አባቶችን ጽሑፎች በተመለከተ ብዙ ካጠና በኋላ ሀሳቦቹን ካጋራባቸው መጻሕፍት አንዱ ሰሞኑን በሕሊና በለጠ ብርህት ዓይን ተብሎ የተተረጎመውን The luminous Eye የተባለ መጸሐፍ ጽፏል። ብሮክ በዚህ መጽሐፉ ካነሳቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የምሥራቃውያን (ኦሬንታል) አባቶች ትምህርታቸውን እንደ ምዕራቡ በነገረ ጉዳይ የተደራጀ (Systematic) ለምን አላዳረጉትም የሚለው ይገኝበታል። (ይህን ስጽፍ መጽሐፉን እያየሁ ስላልሆነ በትክክል ባልገልጸውም አሁን) እርሱ የሚለው የኦሬንታል ሊቃውንት የምዕራብ ሊቃውንት ያደረጉትን ማድረግ ስለማይችሉ ወይም አቅም ስለሌላቸው ሳይሆን ስለኦርቶዶክስ ነገረ ዕውቀት ባላቸው መረዳት ምክንያት ነው። ለምሳሌ የምዕራብ ሊቃውንት አንድን ጉዳይ ብያኔ (definition) ሰጥተው ይጽፋሉ። ለምሥራቃውያን ደግሞ ብያኔ ችግር ያመጣል።
ምክንያቱም መበየን ማለት ለነገሮች ድንበር መሥራት፣ መከለል፣ መለየት፣ መወሰን ማለት ነው። ነገረ ሃይማኖት ደግሞ ለሰው ልጅ አእምሮ በሚመጥን ከእግዚአብሔር የተገለጠ መለኮታዊ ሀሳብ ነው። ያን መልኮታዊ ሀሳብ ደግሞ ጥልቀቱን መወሰን እና ለዚያም ድንበር ማበጀት አይቻልም። የሰው ቋንቋም ለሰው ማስረዳት ቢችልም ነገረ አምላክን ወስኖ መያዝ ግን አይችልም። ስለዚህ እግዚአብሔር በገለጠልን መጠን እናብራራዋለን (እንተረጉመዋለን) እንጂ ልንወስነው ወይም በብያኔ ልንዘጋው አንችልም የሚል እምነት ወይም አረዳድ ስላላቸው ብያኔ እና ብያኔያዊ አካሔድ አይጠቀሙም የሚል ማብራሪያ ይሰጣል። ይህን ሀሳብ በየንታ እሸቱ ርጢን መጽሐፍ መቅድም ላይ ለመጠቆም ሙከራ አድርጊያለሁና ያንንም ማየት ይቻላል።ይህን እውነታ ከእኛም ሆነ ከሌሎች የኦሬንታል አብያተ ክርስቲያን ትውፊት መረዳት ይቻላል።
ኦሬንታሎቹን ብቻ ሳይሆን እኔ እስካየሁት ድረስ ምሥራቅ ኦርቶዶክሶችን ከምዕራቡ (ከካቶሊክም ከሮቴስታንትም) ከሚለዩን መሠረታዊ ነገሮች አንዱ ይህን የሚመለከት ነው።
ሌላውና መሠረታዊው የኦርቶቶዶክስ ነገረ ዕውቀት የሚያጠነጥነው ደግሞ መገለጥ ላይ ነው። መገለጥ በሁሉም ክርስቲያኖች ዘንድ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በሮማ ካቶሊክ በተለይም ደግሞ ከቶማስ አኲናስ መምጣት በኋላ (በእምነት መግለጫዋ ላይም እንዳለው) የሰው አእምሮ ወይም የመረዳት ችሎታ (reason) ብቻውን እግዚአብሔርን በርግጠኝነት ለማወቅ በአጠቃላይ ሃይማኖትን ለማወቅ በቂ ነው ብለው ያምናሉ። (ይህን ሀሳብ Thinking Orthodox እና የመሳሰሉትን መጻሕፍት አንብቦ የበለጠ መረዳት ይቻላል።)
በሁለቱም ኦርቶዶክሶች ግን ይህ ሀሳብ ተቀባይነት የለውም። እንደዚህ ከሆነ ሃይማኖት ከሳይንስ የሚለይበት መሠረታዊ ነገር ይጠፋል ወይም ያንሣል። ይህን ጉዳይ አሁንም በስፋት መግባት ባልፈልግም ኦርቶዶክሳዊው ነገረ ዕውቀት ከዚህ በጅጉ የራቀ እና የተለየ መንገድ ያለው ነው። ምንም እንኳ ሲስተማቲክ ቲዖሎጂ በእኛም ተቋማት እየተሰጠ እና በዚሁ መንገድ መጻሕፍት እየተጻፉና እየተዘጋጁ ቢሆንም መሠርታዊ ጥንቃቄ እና ኦርቶዶክሳዊውን ድነበር መጠበቅ ግን በብዙ የምሥራቅ ሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ብቻ ሳይሆን የተለመደም ጭምር ነው።
በኦርቶዶክሳዊያን ዘንድ ደግሞ በሰው አእምሮ አድሮ የሚናገረው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ይህም በጥልቅ መግቦቱ ለሰው ልጆች በመግለጥ የሚያሳየው ነው። ሰዎች በቅጥነተ ኅሊና ማለትም አእምሮአቸውን በማራቀቅ ብቻ ሊደርሱበት የሚቻላቸውም አይደለም። ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን “እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም። ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤” /1ኛ ቆሮ 3 ፤ 1 – 2/ የሚላቸው በክርስትና ለመንፈሳዊ ሕይወት ሕጻናት ስለሆኑ እንጂ ለእውቀት ለፍልስፍና እና ለአመክንዮ ሕጻናት ሆነው አልነበረም ባዮች ናቸው። ስለዚህ በመንፈሳዊ ሕይወት በተጋድሎ ውስጥ በምትገኝ የማትቋረጥ መገለጥ የሚሰጥ እንጂ የሰው አእምሮ የማሰብ ችሎታ ብቻውን ይደርስበት ዘንድ አይቻልም ብለው ያምናሉ። በተለይም ደግሞ መጀመሪያ ቅዱስ ወግሪስ እንደተናገረው የሚታመነው “እውነተኛ የነገረ ሃይማኖት ዐዋቂ የሚጸልይ ሰው ነው” የሚለው አባባል የሰው የሃይማኖት ዕውቀት የመረዳት ችሎታ ላይ እንዳያርፍ መጠበቂያ አጥራቸው ነው።
የኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት ሦስተኛው መሠረታዊ መለያ ደግሞ ሃይማኖታዊ ዕውቀት በመሠርቱ ለሰዎች ድኅነት ቅድሚያ የሰጠ (Pastoral) መሆኑ ነው። ይህም ማለት ጉዳዮች የሚብራሩት የሚተረጎሙት የሚሰበኩት የሰውን ድኅነት ቅድሚያ ሰጥተው እንጂ ለዕውቀት እና ለርቃቄ ተብለው አይደለም። ከዚህ የተነሣ ለድኅነት ከሚጠቅመው ውጭ እንኳን እንዳሁኑ ማንም ሊያየው በሚችል ሚዲያ ይቅርና ለኦርቶዶክሳዊያን ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን የጉባኤ ቀለም ለመናገር እና ለማራቀቅ የሚደክም የለም፣ ሲያጋጥምም አይመሰገንም። ምክንያቱም ለድኅነታቸው
አንድ ወንድም ከቲክታክ ውይይት ሰማሁት ብሎ የጠየቅኝ ጆሮጅዬን ጭው ነው ያደረገኝ። አንዳንድ ተወያዮች እድገት ያመጡ እና ከፍ ያለ ዕውቀት ላይ የደረሱ እየመሰላቸው ነው መሰል በአብና በወልድ መካከል ገብተው ሁሉ አስተያየት እየሰጡ መሆኑን (የጠየቀኝ ሰው ያለኝን ቃለ በቃል መድገም አልፈለግሁም) ከጥያቄው ተረድቻለሁ። ኪሩቤል ቀና ብለው ወደማያዩት ዙፋን፣ ሱራፌል በሁለት ክንፎቻቸው እግራቸውን በሁለት ክንፎቻቸው ፊታቸውን ሸፍነው ሁለት ክንፎቻቸውን ደግሞ ዘርግተው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ከማመስገን ውጭ ወደ ማይደፍሯት ዙፋን ወይም ገናንነት መግባት የሚፈልግ ሕሊና በፍጥነት በንስሐ መመለስ አለበት ብዬ አምናለሁ።
አንድ ወንድም አንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ነገር ገጥሞት ነበር። ከጓደኛው ጋር ወደ ጎንደር በሔዱበት ወቅት ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራን ሰላም ለማለት በገቡበት ጥያቄ አነሣ። ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች በአንድ አካል ሁለት ባሕርይ የሚሉት ባሕርየ ትስብእት ከባሕርየ መለኮት ጋር ከተዋሐደ ፣ ወልድ ደጎሞ በባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ ስለሆነ እንዴት ሊይድርገው ነው ይላሉ ብሎ ይጠይቃል፤ እንደማስታውሰው ነው። ሊቀ ሊቃውንትም እርሱ ከበደኝ አላለ እናንተን ምን አስጨነቃችሁ ብለው መለሱለት ብሎ የነገረኝን ባስታወስኩ ቁጥር እደነቃለሁ። (በአጻጻፍ የሳትኩት ካለ ሓላፊነቱ የእኔ ነው)። መልሱ ሁልጊዜ ያስደስተኛል። ምክንያቱም በሥላሴ አንድነት ውስጥ ገብታ ቦታ ለማካፈል የምትደፍር ኅሊና እንዴት ያለች ደፋር እና አላዋቂ ናት በእውነት ። ሙሴ እንኳ ወደ ዕፀ ጳጦስ ለመጠጋት ጫማውን እንዲያውልቅ ታዝዞ ነበር። የቀረበውም በረዓድ እና በመንቀጥቀጥ ነበር። ምሳሌው ለተመረጠው ለሙሴ እንኳ እንዲያ የሚያስፈራ ከሆነ አማናዊው የተዋሕዶ ምሥጢርም ይልቁን ምን ያህል ትሕትና እና ጥንቃቄ ይፈልግ ይሆን?
የተገለጠና እና በትክክል የምናውቀው እንኳ ቢሆን እንዲህ ያለው ይዘት በፍጹም ለማኅበራዊ ሚዲያ የሚሆን አይደለም። እውነቱን ለመናገር “የተቀደሰውን ለውሾች አት ስጡን” ለምን አንጠብቀውም የሚለውን እጠይቅና የተቀደሰውን ስለማናውቀው ይሆናል በሚል መልስ እንደገና እቆማለሁ። በርግጥም የምናውቀው አይመስለኝም። ይህ ሁሉ እንግዲህ ኦርቶዶክሳዊውን ነገረ ዕውቀት በመጠቆም ለማሳሰብ እንደ መግቢያ ያነሣሁት ነው።
ሴባስቲያን ብሮክ የሚባለው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የኦሬንታል በተለይም የሶርያ ኦርቶዶክስ አባቶችን ጽሑፎች በተመለከተ ብዙ ካጠና በኋላ ሀሳቦቹን ካጋራባቸው መጻሕፍት አንዱ ሰሞኑን በሕሊና በለጠ ብርህት ዓይን ተብሎ የተተረጎመውን The luminous Eye የተባለ መጸሐፍ ጽፏል። ብሮክ በዚህ መጽሐፉ ካነሳቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የምሥራቃውያን (ኦሬንታል) አባቶች ትምህርታቸውን እንደ ምዕራቡ በነገረ ጉዳይ የተደራጀ (Systematic) ለምን አላዳረጉትም የሚለው ይገኝበታል። (ይህን ስጽፍ መጽሐፉን እያየሁ ስላልሆነ በትክክል ባልገልጸውም አሁን) እርሱ የሚለው የኦሬንታል ሊቃውንት የምዕራብ ሊቃውንት ያደረጉትን ማድረግ ስለማይችሉ ወይም አቅም ስለሌላቸው ሳይሆን ስለኦርቶዶክስ ነገረ ዕውቀት ባላቸው መረዳት ምክንያት ነው። ለምሳሌ የምዕራብ ሊቃውንት አንድን ጉዳይ ብያኔ (definition) ሰጥተው ይጽፋሉ። ለምሥራቃውያን ደግሞ ብያኔ ችግር ያመጣል።
ምክንያቱም መበየን ማለት ለነገሮች ድንበር መሥራት፣ መከለል፣ መለየት፣ መወሰን ማለት ነው። ነገረ ሃይማኖት ደግሞ ለሰው ልጅ አእምሮ በሚመጥን ከእግዚአብሔር የተገለጠ መለኮታዊ ሀሳብ ነው። ያን መልኮታዊ ሀሳብ ደግሞ ጥልቀቱን መወሰን እና ለዚያም ድንበር ማበጀት አይቻልም። የሰው ቋንቋም ለሰው ማስረዳት ቢችልም ነገረ አምላክን ወስኖ መያዝ ግን አይችልም። ስለዚህ እግዚአብሔር በገለጠልን መጠን እናብራራዋለን (እንተረጉመዋለን) እንጂ ልንወስነው ወይም በብያኔ ልንዘጋው አንችልም የሚል እምነት ወይም አረዳድ ስላላቸው ብያኔ እና ብያኔያዊ አካሔድ አይጠቀሙም የሚል ማብራሪያ ይሰጣል። ይህን ሀሳብ በየንታ እሸቱ ርጢን መጽሐፍ መቅድም ላይ ለመጠቆም ሙከራ አድርጊያለሁና ያንንም ማየት ይቻላል።ይህን እውነታ ከእኛም ሆነ ከሌሎች የኦሬንታል አብያተ ክርስቲያን ትውፊት መረዳት ይቻላል።
ኦሬንታሎቹን ብቻ ሳይሆን እኔ እስካየሁት ድረስ ምሥራቅ ኦርቶዶክሶችን ከምዕራቡ (ከካቶሊክም ከሮቴስታንትም) ከሚለዩን መሠረታዊ ነገሮች አንዱ ይህን የሚመለከት ነው።
ሌላውና መሠረታዊው የኦርቶቶዶክስ ነገረ ዕውቀት የሚያጠነጥነው ደግሞ መገለጥ ላይ ነው። መገለጥ በሁሉም ክርስቲያኖች ዘንድ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በሮማ ካቶሊክ በተለይም ደግሞ ከቶማስ አኲናስ መምጣት በኋላ (በእምነት መግለጫዋ ላይም እንዳለው) የሰው አእምሮ ወይም የመረዳት ችሎታ (reason) ብቻውን እግዚአብሔርን በርግጠኝነት ለማወቅ በአጠቃላይ ሃይማኖትን ለማወቅ በቂ ነው ብለው ያምናሉ። (ይህን ሀሳብ Thinking Orthodox እና የመሳሰሉትን መጻሕፍት አንብቦ የበለጠ መረዳት ይቻላል።)
በሁለቱም ኦርቶዶክሶች ግን ይህ ሀሳብ ተቀባይነት የለውም። እንደዚህ ከሆነ ሃይማኖት ከሳይንስ የሚለይበት መሠረታዊ ነገር ይጠፋል ወይም ያንሣል። ይህን ጉዳይ አሁንም በስፋት መግባት ባልፈልግም ኦርቶዶክሳዊው ነገረ ዕውቀት ከዚህ በጅጉ የራቀ እና የተለየ መንገድ ያለው ነው። ምንም እንኳ ሲስተማቲክ ቲዖሎጂ በእኛም ተቋማት እየተሰጠ እና በዚሁ መንገድ መጻሕፍት እየተጻፉና እየተዘጋጁ ቢሆንም መሠርታዊ ጥንቃቄ እና ኦርቶዶክሳዊውን ድነበር መጠበቅ ግን በብዙ የምሥራቅ ሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ብቻ ሳይሆን የተለመደም ጭምር ነው።
በኦርቶዶክሳዊያን ዘንድ ደግሞ በሰው አእምሮ አድሮ የሚናገረው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ይህም በጥልቅ መግቦቱ ለሰው ልጆች በመግለጥ የሚያሳየው ነው። ሰዎች በቅጥነተ ኅሊና ማለትም አእምሮአቸውን በማራቀቅ ብቻ ሊደርሱበት የሚቻላቸውም አይደለም። ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን “እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም። ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤” /1ኛ ቆሮ 3 ፤ 1 – 2/ የሚላቸው በክርስትና ለመንፈሳዊ ሕይወት ሕጻናት ስለሆኑ እንጂ ለእውቀት ለፍልስፍና እና ለአመክንዮ ሕጻናት ሆነው አልነበረም ባዮች ናቸው። ስለዚህ በመንፈሳዊ ሕይወት በተጋድሎ ውስጥ በምትገኝ የማትቋረጥ መገለጥ የሚሰጥ እንጂ የሰው አእምሮ የማሰብ ችሎታ ብቻውን ይደርስበት ዘንድ አይቻልም ብለው ያምናሉ። በተለይም ደግሞ መጀመሪያ ቅዱስ ወግሪስ እንደተናገረው የሚታመነው “እውነተኛ የነገረ ሃይማኖት ዐዋቂ የሚጸልይ ሰው ነው” የሚለው አባባል የሰው የሃይማኖት ዕውቀት የመረዳት ችሎታ ላይ እንዳያርፍ መጠበቂያ አጥራቸው ነው።
የኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት ሦስተኛው መሠረታዊ መለያ ደግሞ ሃይማኖታዊ ዕውቀት በመሠርቱ ለሰዎች ድኅነት ቅድሚያ የሰጠ (Pastoral) መሆኑ ነው። ይህም ማለት ጉዳዮች የሚብራሩት የሚተረጎሙት የሚሰበኩት የሰውን ድኅነት ቅድሚያ ሰጥተው እንጂ ለዕውቀት እና ለርቃቄ ተብለው አይደለም። ከዚህ የተነሣ ለድኅነት ከሚጠቅመው ውጭ እንኳን እንዳሁኑ ማንም ሊያየው በሚችል ሚዲያ ይቅርና ለኦርቶዶክሳዊያን ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን የጉባኤ ቀለም ለመናገር እና ለማራቀቅ የሚደክም የለም፣ ሲያጋጥምም አይመሰገንም። ምክንያቱም ለድኅነታቸው