⛪️መንፈሳዊ መጻሕፍትን እናንብብ እንወቅ⛪️


Channel's geo and language: Ethiopia, English
Category: Books


በዚህ ቻናል የሚቀርቡ
፩.ተከታታይ የቤተክርስቲያን ትምህርቶች ፣
፪. መንፈሳዊ መጻሕፍት ጥቆማ፤
፫. የተለያዩ አጫጭር የቤተክርስቲያን መጣጥፎች ፣ ወጎች ፣ ታሪኮች ፤
፬. ለተለያዩ ጥያቄዎች መልስ እና ወቅታዊ ትምህርቶችን እንማማራለን ፣
፭. ዘወትር #ቃለ_ወንጌል የእለቱ(በግፃዌ) ይቀርባሉ።
ተከታታይ ትምህርቶች ለማግኘት 👇👇
@EOTC_teketatay
ለጥያቄ👉 @Temechache

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Category
Books
Statistics
Posts filter


⚙️ ጠላትህን የምታስወግድበት መንገድ እርሱን ባልንጀራ አድርገህ በመቀየር ነው።

⚙️ መከራን በመከራነቱ ሳይሆን በመካሪነቱ ውደደው

⚙️ ችግር መከራ የሌለበት ህይወት አትመኝ ምንም አታተርፍምና

⚙️ ከምቀኝነት ከክፋት የሚከፋ የለምና በፍፁም ሰው በሰዎች አትቅና


ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


#ቃለ_ወንጌል

18/12/2018
 
         ማቴዎስ 15:6-21


   ‘አባቱን ወይም እናቱን አያከብርም፡’ ትላላችሁ፤ ስለ ወጋችሁም የእግዚአብሔርን ቃል ሻራችሁ። “እናንተ ግብዞች፥ ኢሳይያስ ስለ እናንተ፦ ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤ የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል፣’ ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።” ሕዝቡንም ጠርቶ፦ “ስሙ አስተውሉም፤ ሰውን የሚያረክሰው ወደ አፍ የሚገባ አይደለም፥ ከአፍ የሚወጣው ግን ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው፡” አላቸው።

በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ቀርበው፦ “ፈሪሳውያን ይህን ቃል ሰምተው እንደ ተሰናከሉ አወቅህን?” አሉት። እርሱ ግን መልሶ፦ “የሰማዩ አባቴ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል። ተዉአቸው፤ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው፤ ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ፡” አለ። ጴጥሮስም መልሶ፦ “ምሳሌውን ተርጕምልን፡” አለው።

ኢየሱስም እንዲህ አለ፦ “እናንተ ደግሞ እስካሁን የማታስተውሉ ናችሁን? ወደ አፍ የሚገባ ሁሉ ወደ ሆድ አልፎ ወደ እዳሪ እንዲጣል አትመለከቱምን? ከአፍ የሚወጣ ግን ከልብ ይወጣል፥ ሰውንም የሚያረክሰው ያ ነው።ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና። ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው እንጂ፥ ባልታጠበ እጅ መብላትስ ሰውን አያረክሰውም


#መልእክታት
ፊልጵስዩስ 3:1-6
1 ዮሐንስ 2:1-20
ሐዋ.ሥራ 20:28-31

ምስባክ

            መዝሙር 2:12-13

አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር

ወኢትትኀጐሉ እምፍኖተ ጽድቅ

ሶበ ነደት ፍጡነ መዓቱ

ትርጉም

ተግሣጹን ተቀበሉ ጌታ እንዳይቈጣ፡

እናንተም በመንገድ እንዳትጠፉ፥

ቍጣው ፈጥና ትነድዳለችና።

ዓዲ ምስባክ
መዝሙር 108፥17-18

ዘአበያ ለበረከት ወትርኀቅ እምኔሁ

ወለብሳ ለመርገም ከመ ልብስ

ወቦአ ከመ ማይ ውስተ አማዑቱ

ትርጉም

በረከትንም አልመረጠም ከእርሱም ራቀች።

መርገምን እንደ ልብስ ለበሳት፥

እንደ ውኃም ወደ አንጀቱ፥ ገባች


Forward from: Henok Haile
ከፀሐይ አጠገብ የነበረው ኮከብ

የአምላክ ሰው መሆንና ተወልዶ የማደጉ ዜና ሲነገር ሁልጊዜም የሚዘነጋ ክብሩ ግን ከብዙ ቅዱሳን ክብር የሚበልጥ አንድ ታላቅ ሰው ዛሬ በልቡናዬ ውል አለ፡፡ መቼም ከፀሐይ አጠገብ ያለ ኮከብ በፀሐይ ብርሃን ምክንያት መሸፈኑ አይቀርምና በተወለደው የጽድቅ ፀሐይ ፣ የሰላም ንጉሥ በልደቱ ደስታ ተውጠን ፣ በገብርኤል ብሥራት ፣ በድንግል ምስጋና ፣ በመላእክት ዝማሬ ተስበን የዘነጋነውን ፣ ድምቀት ሳያንሰው የተሸፈነውን ኮከብ የቅዱስ ዮሴፍን ነገር ባሰብኩኝ ጊዜ ክብሩን ለመናገር ልቡናዬ ተጨነቀ፡፡

በቅድስናው እያመንን ፣ ውለታውንም እያወቅን የምንዘነጋውን ምናልባትም አንዳንድ ሰዎች የድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለማቃለል ስሙን በክፉ ማስረጃነት ሲያነሱብን ከእነርሱ ሸሸን ብለን ሳናውቅ ከበረከቱ የሸሸነውን ጻድቅ ዛሬ ልዘክረው ብል ልቤ በጥፋተኝነት ስሜት ተጨነቀብኝ፡፡

ስለ እርሱ ብዙ ያልዘመርንበትን ፣ ብዙ ያልተቀኘንበትን ዘመን ሳስብ ‘ላዕከ ማርያም ቅዱስ ዮሴፍ ሆይ ስለረሳንህ ቀኛችን ትርሳን ፣ ስላላሰብንህም ምላሳችን ከትናጋችን ይጣበቅ’ ብዬ ይቅርታውን ለመለመን ተመኘሁ፡፡

ቅዱስ ዮሴፍን ማን ብለን እንጥራው? እርሱ እንደሆን እንደ አብርሃም ዘመዶቹን የተወ አማኝ ፣ እንደ ይስሐቅ የታዘዘውን ብቻ ያደረገ ትሑት ፣ እንደ ያዕቆብ በእምነት ግብጽ የወረደ ስደተኛ ነውና እርሱን ለመግለፅ እንደምን ያለ ቋንቋ እንጠቀም ይሆን?

እስቲ ንገሩኝ? ‘መልካሙን እረኛ’ ክርስቶስን የጠበቀውን እረኛ ቅዱስ ዮሴፍን ከቶ በምን ቃል እንገልጸዋለን? የአብን ልጅ ያሳደገውን (ሐፃኔ ወልደ አብ) ቅዱስ ዮሴፍን በምን ቅኔ እናወድሰው?

ሕዝቅኤል ያያትን የእስራኤል አምላክ ገብቶባት ለዘላለም የተዘጋችውን ደጅ የጠበቀውን ታማኝ ዘብ ፤ ‘ከበሩ ደጀ ሰላም መንገድ በዚያ ይገባል በዚያም ይወጣል’ ተብሎ የተነገረለትን የተዘጋችው በር ደጀ ጠኚ ፣ ከታላቅዋ ተራራ ከድንግል ማርያም ያለ ሰው እጅ ድንጋይ ተፈንቅሎ ሲወርድ ቆሞ የተመለከተውን የሐዲስ ኪዳኑን ዳንኤል ከቶ እንዴት ባለ ቃል እንገልጸዋለን?

በቤተ ልሔም ግርግም ውስጥ በላምና አህያ መካከል የተኛውን ሕፃን የተመለከተውንና እንደ ነቢዩ ዕንባቆም
‘በማዕከለ ክልዔ እንስሳ ርኢኩከ’ /በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ/ ሊል የሚቻለውን የቅዱስ ዮሴፍን ክብር በምን አቅማችን እንግለጸው?

ወደ ግብጽ ወርዶ ለወገኖቹና ለዓለም ሁሉ ምግብን እንዳቆየው የብሉይ ኪዳኑ ዮሴፍ ወደ ግብጽ በመከራ ተሰድዶ የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን ለሁላችን ላቆየልን ጻድቅ እንዴት ያለ የምስጋና ቃል እናዋጣ?

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ


በክንፎቻቸው ተሸፋፍነው በፊቱ የሚቆሙለት ቅዱሳን መላእክት፣ ፈጣሪያቸው "እኔ በምድር ወዳጅ አለኝ። እርሱም አብርሃም ነው" ብሎ በነገራቸው ጊዜ እጅግ በመደነቅ ወደ አብርሃም ሄደው "አብርሃም አርከ እግዚአብሔር"/"አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ"/ እያሉ ዘምረውለት ነበር። በእውነት እግዚአብሔር "ወዳጅ አለኝ" ስላላቸው እንዲህ የተደነቁ መላእክት፣ "እኔ በምድር እናት አለኝ" ሲላቸው ምን ያህል ተገርመው ይሆን? እመቤታችንንስ በምን ዓይነት ቃል አመስግነዋት ይሆን?

በዛሬው እለት የአምላክን እናት ልዩ በሆነ ምስጋና እና እልልታ ያሳረጓት መላእክት፣ በምድር ሳለች "እይዋት የአምላክን እናት በምድር ትመላለሳለች" እያሉ በስስት የሚያይዋትና መምጣቷን የሚጠባበቁ እመቤታቸው ነበረች። ለዚህም ነው አባቶቻችን በሌሊት ማኅሌት "ተበሃሉ በሰማያት እለ ኪያኪ አፍለሱ፣ ማርያምሰ እንተ በምድር ታንሶሱ" እያሉ ሲወርቡ ያደሩት።

እኛም ንግሥታችንን ወደ ልጇ እልፍኝ ለሸኘንበት፣ መላእክትም እርሷን በደስታ ለተቀበሉባት ለበዓለ ዕርገቷ እንኳን በሰላም አደረሰን!!!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ነሐሴ 16፣ 2014 ዓ.ም.
ኢየሩሳሌም፣ እስራኤል


Forward from: Henok Haile
+++ አበው ስለ እመቤታችን እንዲህ አሉ +++

"አምላክ ከንጉሥ ሔሮድስ ሴት ልጅ ቢወለድ ኖሮ አልጋ ወራሽ በሆነና ባልተሰደደ ነበር። እርሱ ግን የድሆች ልጅ የሆነችውን ድንግል መረጠ" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

"ታላቁ ተራራ ሆይ ታናሽዋ ብላቴና የተሸከመችህ ራስህን በሚቻላት መጠን አድርገህላት ነው ፣ ታላቁ እሳት ሆይ ታናሽዋ ብላቴና ተሸክማህ ያልተቃጠለችው ኃይልን ትችል ዘንድ አጽንተሃት ነው "  ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

"ይህ ዓለም የእግዚአብሔርን ልጅ በቀጥታ ከእግዚአብሔር አብ እጅ ለመቀበል የተገባ ሆኖ ስላልተገኘ ፣ ዓለም ከእርስዋ ይቀበል ዘንድ አንድያ ልጁን ለድንግል ማርያም እናት ትሆነው ዘንድ ሠጣት" ቅዱስ አውግስጢኖስ

"ሔሮድስ የማይያዘውን ይይዝ ዘንድ ተነሣ ፣ ዓውሎ ነፋስንም በቤቱ አስገብቶ ሊዘጋ ታገለ" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

"ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን??"  ቅዱስ ኤፍሬም

     ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!

ይህ በየቀኑ የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች የሚለቀቅበት ቻናል ነው ይቀላቀሉ 👇👇👇

@dnhenok_haile
@dnhenok_haile


​​​​እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ጾመ ፍልሰታ ፍቺ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ! በየትም ዓለም የምትኖሩ የክርስትና እምነት ተከታዮች ሰላምታችን ይድረሳችሁ፡፡

የእመቤታችን ትንሣኤና ዕርገት

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር የኖረችው ስልሳ አራት ዓመት ነው፡፡ እነዚህ ዓመታት ሲተነተኑ ሦስት ዓመት በወላጆቿ ሐናና ኢያቄም ቤት፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ፣ ሠላሣ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አሥራ አምስት ዓመት ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር ነው፡፡

ያረፈችውም ጥር 21 ቀን በ50 ዓ.ም ነው፡፡ ባረፈችበት ወቅት ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሔዱ አይሁድ "ቀድሞ ልጇ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፤ በአርባኛውም ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ተመልሶም ይህን ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል እያሉ በማስተማር ሕዝባችንን ወስደውብናል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷም እንደ ልጇ ተነሳች እያሉ በማስተማር ሊያውኩን አይደለምን? ኑ! ተሰብስበን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ክፉ ምክር ተማከሩ፡፡

ከመካከላቸውም ብርቱ ሰው የሆነው #ታውፋንያ የተባለ ቅድስት ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ለማስቀረት ክቡር ሥጋዋ ያለበትን የአልጋ ሸንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጣ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥላ ቀረች፤ ከዚህ የጥፋቱ ሥራው ተምሮ እመቤታችንን በመለመኑ እመቤታችን የተቆረጠች እጁን መልሳለታለች፡፡

ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የተቀደሰ ሥጋዋን ጌታችን ይወደው የነበረ ተብሎ የተነገረለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ይዞ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሆነውን ሁሉ ለወንድሞቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ነገራቸው፡፡ እነሱም የእመቤታችን ሥጋ በክብር ለማሳረፍ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ ሱባኤ ገቡ፡፡

ከሁለተኛ ሱባኤ ቆይታቸው በኋላ በአሥራ አራተኛ ቀናቸው ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ ሰጣቸው፡፡ ሐዋርያትም በዝማሬና በታላቅ ምስጋና በጌቴ ሴማኔ ቀበሯት፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት› › ተብሎ ትንቢት የተናገረውን ሲተረጉሙት ‹‹ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታሳርፈው የመቅደስህ ታቦት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ›› ብለው ያመሰጥሩታል፡፡ /መዝ. 131፥8/፡፡

የእመቤታችንን ቅድስት ሥጋዋን ሐዋርያት ሲቀብሯት በሀገረ ስብከቱ ሕንድ የነበረው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ ሲመለስ እመቤታችን ስታርግ ያገኛታል ለምልክት እንዲሆነው ሰበኗን (የመግነዟን ጨርቅ) ተቀብሏት ይለያያሉ፡፡ ለወንድሞቹ ሐዋርያት ያየውን ይነግራቸዋል፡፡

ለበረከት የሰጠችውንም ሰበን ያካፍላቸዋል፤ ሐዋርያት ‹ ‹ዕርገቷን እንዴት እሱ ብቻ ተመልክቶ ለምን እኛ ይቀርብናል› › ብለው በዓመቱ ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ፡፡ ነሐሴ 16 ቀን የልባቸው መሻት ተፈጸመላቸው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቀ (ረዳት) ቄስ፣ ቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ (ዋና ዲያቆን) አድርጎ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡

በትኅትና የያዙት ሱባኤም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገቷን ለማየት አበቃቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን መሠረት አድርጋ ከነሐሴ 1-16 ጾመ ፍልሰታ በማለት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ አድርገን እንድንጠቀምበት ሥርዐት ሠራችልን፡፡

በነቢያና በሐዋርያት መሠረት ላይ የታነጽን ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች በየዓመቱ ይህን ጾም በሱባኤ በማሳለፍ ከእመቤታችን ጸጋና በረከት ተሳታፊዎች እንሆናለን፤ ሆነናልም፡፡ የዓመት ሰዎች ይበለን፡፡

ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ተቋዳሾች ያድርገን፡፡
                     አሜን!

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
💚@Eotc_spritual_books💚
💛@Eotc_spritual_books💛
❤️@Eotc_spritual_books


#ቃለ_ወንጌል


16/12/2017
                         ማቴዎስ 26:26-31

   ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ “እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡” አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ “ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።

ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር ከዚህ ከወይን ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣውም። መዝሙርም ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ።

መልእክታት

ሮሜ 8:31-ፍጻሜ
ዮሐንስ 2:1-7
ሐዋ.ሥራ 1:12-15
                                 
ምስባክ
                           መዝ· ፵፭: ፬ – ፭

ቀደሰ ማኅደሮ ልዑል

እግዚአብሔር ውስተ ማዕከላ ኢትትሀወክ

ወይረድኣ እግዚአብሔር ፍጽመ

አዲ ምስባክ
                     መዝሙር  121:6-7

ወተዜያነዉ ዳኅናሃ ለኢየሩሳሌም

ወፍሥሓሆሙ ለእለ ያፈቅሩ ስመከ

ይኩን ሰላም በኃይልከ


Forward from: ያሬዳውያን
🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁
ሥርዓተ ማኅሌት ዘነሐሴ ፲፮ በዓለ ኪዳነምህረት
💎💎💎💎💎💎💎💎💎💎💎💎💎💎
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክአ ሥላሴ፦
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣሕል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
ወታስተሥርዩ ኃጥያተ ህዝብኪ ተበውሐ ለኪ፤ እም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ ከመ ትኲኒ ተንከተመ ለውሉደ ሰብእ፤ ለሕይወት ዘለዓለም፤ ለኪ ይደሉ ከመ ትኵኒ መድኀኒቶሙ ለመሐይምናን ሕዝብኪ፤ ኦ መድኃኒተ ኩሉ ዓለም ወልድኪ ሣህሎ ይክፍለነ ሰዓሊ ለነ ቅድስት
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ነግስ፦
እምጌቴሴማኒ ፈለሰት ኀበ ዘሉዓሌ መካን፤ውስተ ቤተ መቅደስ ረባቢ ዘመሳከዊሁ ብርሃን፤ አንቀጸ አድኅኖ ማርያም ጽላተ ኪዳን፤ኵሉ ይብልዋ በአኅብሮ ዘበዕብራይስጢ ልሳን፤ ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን ቅድስተ ቅዱሳን፤ እመቅድሐ ከርሣ ተቀድሐ አስራባተ ወይን ወውስቴታ ተሠርዓ ቁርባን።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን መዝገቡ ለቃል፤ ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን አንቀጸ ብርሃን፤ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን ጽጌ ደንጉላት፤ ሐረገ ወይን ዘእምነገደ ይሁዳ፤ እንተ ሠረፀት ለሕይወት።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዓ ኪዳነምህረት፦
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ኀበ ሕንጻ ሕይወት ዘተሐደሰ፤ እምቅድመ ዝኒ ኀቤሁ ሥጋ ወልድኪ ፈለሰ፤ ቤዛዊተ ዓለም ማርያም አስተበቁዓኪ አንሰ፤ ትቤዝዊ በኪዳንኪ ዘዚዓየ ነፍሰ፤ እስመ በሥራያ ይዕቲ ቀብዓተኒ ፈውሰ።
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
ደብተራ ፍጽምት ዘጳዉሊ፤ወማኅደሩ በጽድቅ ዘገብራ ከሃሊ፤ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ፤በመሰንቆሁ እንዘ የኃሊ፤ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ።
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ደብተራ ፍጽምት ዘጳዉሊ ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ/፪/
በመሰንቆሁ እንዘ የኃሊ ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክአ ማርያም
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፣እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፣ማርያም ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትዕዛዝ፣ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፣ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።
@EOTCmahlet
ዚቅ
ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ፤ወልድኪ ይጼዉዓኪ፤ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር።
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ ማኅደረ መለኮት/፪/
"ወልድኪ"/፪/ይጼዉዓኪ ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዓ ማርያም፦
ሰላም ለእስትፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት፤ከመ መዓዛ ዕፀ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፤ ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ ፤መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል፤ ወኵሉ ነገራ በሰላም
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ/፪/
መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል/፬/
@EOTCmahlet
መልክዓ ፍልሰታ
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ዘኢይቀብል ሞገሱ፤ ወዘኢይነጸፍ ባሕርየ ተውዳሱ፤ ማርያም ታዕካ ለእግዚአብሔር ጽርሐ መቅደሱ፤ተበሃሉ በሰማያት እለ ኪያኪ አፍለሱ፤ ማርያምሰ እንተ በምድር ታንሶሱ።
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
ማርያም ጽርሕ ንጽሕት፤ማሕደረ መለኮት፤እኅቶሙ ለመላእክት ሰመያ፤ ሰማያዊት እንተ በምድር ታንሶሱ
@EOTCmahlet
አመላለስ፦
ማርያም ጽርሕ ንጽሕት/፪/
ጽርሕ ንጽሕት ማሕደረ መለኮት/፪/
@EOTCmahlet
ምልጣን፦
ትርሢተ ወልድ መለኮት ወፍቅር፤ኀደረ ላዕሌሃ፤ይቤላ ርግብየ ወይቤላ ሠናይትየ፤ፀቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍሪሃ
@EOTCmahlet
አመላለስ፦
ፀቃውዕ ይውኅዝ/፪/
ይውኅዝ እምከናፍሪሃ/፬/
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ትርሢተ ወልድ መለኮት ወፍቅር ኀደረ ላዕሌሃ/፪/
ይቤላ ርግብየ ወይቤላ ወይቤላ ሠናይትየ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ቅንዋት
ክብሮሙ ለቅዱሳን ሞገሶሙ ለጻድቃን፤መርሖሙ ለዕውራን ዝንቱ ውእቱ መስቀል፤እንስሳ ገዳምኒ አዕዋፈ ሰማይኒ ያንቀዓድዉ ኀቤከ፤አምላክ መስተመይጥ፤ያፀግብ ነፍሰ ነዳያን ያከርም በበዓመት፤ለዘበእንቲአነ ውስተ ማኅፀና ለማርያም ተሠወርከ፤ወበደመናትኒ
ሰማየ ዘከለልከ፤ወኵሉ ቀሊል በኀቤከ።
@EOTCmahlet
ሰላም፦
ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ ፤መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል፤ ወኵሉ ነገራ በሰላም

👇👇👇👇👇🇪🇹
👉@EOTCmahlet👈
👉@EOTCmahlet👈
👉@EOTCmahlet👈
🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹

@EOTCmahlet
#ይቀላቀሉ & #ለወዳጅዎ_ሼር_ያርጉ


‛‛ለሌሎች ይቅርታን ስትሰጥ፣ ለራስህ ሰላምን ትሰጣለህ።’’

አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ


#ቃለ_ወንጌል

15/12/2017
                        ማቴዎስ 10:1-15

     አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ፥ እንዲያወጡአቸው በርኩሳን መናፍስት ላይ ደዌንና ሕማምንም ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው። የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም ይህ ነው፤ መጀመሪያው ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን ወንድሙ እንድርያስም፥ የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብም ወንድሙ ዮሐንስም፥ ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥ ቶማስም ቀራጩ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥ ቀነናዊውም ስምዖን ደግሞም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ።

እነዚህን አሥራ ሁለቱን ኢየሱስ ላካቸው፥ አዘዛቸውም፥ እንዲህም አለ፦ “በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ፥ ወደ ሳምራውያንም ከተማ አትግቡ፤ ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑ ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ። ሄዳችሁም፦ ‘መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች፡’ ብላችሁ ስበኩ። ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ። ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ፥ ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ፤ ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና።

“በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ። ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ፤ ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት፤ ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ። ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ። እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል

መልእክታት

1 ቆሮንጦስ 12:18-ፍጻሜ
ይሁዳ 1:17-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 1:12-15

                                
ምስባክ

                  መዝሙር 18:3

አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ

ውስተ ኩሉ ምድ ወጽአ ነገሮሙ

ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ
              
ትርጉም

ነገር የለም መናገርም የለም ድምፃቸውም አይሰማም

ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ

ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ


አንድ አረጋዊ "ጠባቧና ቀጥተኛዋን መንገድ ምንድን ናት? " ተብሎ ተጠየቀ። እርሱም "ቀጥተኛዋና ጠባቧ መንገድ ይህች ናት:- ለራስ ሃሳብ አለመታዘዝና የራስን ፍላጎት ማሸየፍ። 'እነሆ ሁሉን ትተን ተከተልንህ' ማለት ይህ ነው" ማር 10÷28።


#ቃለ_ወንጌል
14/12/2018
           ማቴዎስ 17:14-24


     ወደ ሕዝቡም ሲደርሱ አንድ ሰው ወደ እርሱ ቀረበና ተንበርክኮ፦ “ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤ ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና። ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው፡” አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ “የማታምን ጠማማ ትውልድ ሆይ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ ወደ እኔ አምጡት፡” አለ።

ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ። ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና፦ “እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው?” አሉት። ኢየሱስም፦ “ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ‘ከዚህ ወደዚያ እለፍ’ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም። ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም፡” አላቸው። በገሊላም ሲመላለሱ ኢየሱስ፦ “የሰው ልጅ በሰዎች እጅ አልፎ ይሰጥ ዘንድ አለው፥ ይገድሉትማል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል፥” አላቸው። እጅግም አዘኑ


#መልእክታት
1 ቆሮንጦስ 1:10-19
ያዕቆብ 1:12-22
ሐዋ.ሥራ 10:30-54
                
ምስባክ

           መዝሙር 43:4-5

ዘአዘዝከ መድኃኒቶ ለያዕቆብ

ብከ ንወግዖሙ ለኵሎሙ ፀርነ

ወበስምከ ናኃሥሮሙ ለእለ ቆሙ ላዕሌነ

ትርጉም

ለያዕቆብ መድኀኒትን አዘዝህ

ባንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን

በስምኽም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን




Forward from: Henok Haile
+++ "የምወደው ልጄ ይህ ነው" +++

ጌታችን ከሐዋርያቱ መካከል "የምሥጢር ሐዋርያ” የተባሉትን ያዕቆብና ጴጥሮስ፣ ዮሐንስንም ወደ ቅዱሱ የታቦር ተራራ ብቻቸውን ይዟቸው ወጣ። ከተራራውም ጫፍ ሲደርሱ ሦስቱ ደቀ መዛሙርት የመምህራቸው ፊት እንደ ፀሐይ ሲያበራ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሲሆን ተመለከቱ። እነሆም ከቀደሙት ጻድቃን ታላላቆቹ ሙሴና ኤልያስ በታቦር ተገኝተው ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።

እነዚህ የብሉይ ኪዳን ነቢያት የትንቢታቸው ፍጻሜ ከሆነው ክርስቶስ ጋር ምን ተነጋገሩ? መቼም በጊዜው ከጌታ ጋር ውለው ያድሩ እንደ ነበሩት ተማሪዎቹ ሐዋርያት  "አትሙትብን" አይሉትም። በሺህ ለሚቆጠሩ ዓመታት ሱባኤ የያዙለትና ደጅ የጠኑት የድኅነት ተስፋ እናዳይፈጸም "ይቅር አትሙት" እንዴት ይላሉ? ስለዚህ ከብሔረ ሕያዋን የመጣው ኤልያስና ከብሔረ ሙታን የመጣው ሙሴ በአንድ ላይ "በኢየሩሳሌም ሊፈጸም ስላለው ስለ መውጣቱ (ስለ መከራው፣ ሞቱ)" ያነጋግሩት ነበር።(ሉቃ 9፥31)

በታቦር ተራራ ላይ የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን መልእክተኞች ተገናኙ። በባሕር ላይ በእግሩ የተራመደው ጴጥሮስ፣ የኤርትራን ባሕር እጁን ዘርግቶ የከፈለው ሙሴን አየው።(ማቴ 14፥29፣ ዘጸአ 14፥21) የሰማርያ ሰዎች በተቃወሙ ጊዜ "እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው" ያሉ ያዕቆብና ዮሐንስ፣ ከሰማይ እሳት አዝንሞ ሃምሳ አንዱን ወታደሮች ያስበላ ኤልያስን ተመለከቱት።(ሉቃ 9፥54፣ 2ኛ ነገ 1፥10)

ሁለቱ ምስክሮች እንደ ተሰወሩም ወዲያው ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ ሦስት ዳሶች እንሥራ ብሎ ጌታውን ጠየቀ። ሐዋርያው በዚህ ተራራ ላይ መቅረት የፈለገው ያለ ምክንያት አይደለም። መድኃኒታችን አስቀድሞ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄድ ዘንድ ከሽማግሎችና ከካህናት አለቆች ከጻፎችም ዘንድ ብዙ መከራ ይቀበልና ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲነግራቸው ቅዱስ ጴጥሮስ "አይሁንብህ፤ አይድረስብህ" ሲል ሊከላከለው ሞክሮ ነበር። ለዚህም በጊዜ "ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል" ተብሎ ተገስጾበታል።(ማር 9፥31-33) ይሁን እንጂ አሁንም ቅዱስ ጴጥሮስ ያለውን ሁሉ እድል ተጠቅሞ ጌታን ወደ ኢየሩሳሌም ከመሄድና በካህናት አለቆች እጅ ተላልፎ ከመሰጠት ማስቀረት ስለሚፈልግ "ጌታ ሆይ፦ በዚህ(በታቦር ተራራ) መሆን ለእኛ መልካም ነው" ብሎ ተናገረ።

እርሱም ይህን ገና ሲናገር ሳለ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው። ከደመናው "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት" የሚል ድምፅ መጣ። ሐዋርያቱ ይህን ድምጽ የሰሙት ሙሴ እና ኤልያስ ከክርስቶስ ተለይተው ከሄዱ፣ እነርሱም ወድቀው ከነበሩበት ከተነሡ በኋላ ነው። ይህም ከደመናው ውስጥ ሲወጣ ስለ ሰሙት ቃል "ለማን የተነገረ ይሆን?" ብለው እንዳይጠይቁና ምስክርነቱ ለክርስቶስ ብቻ የተሰጠ መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ እንዲረዱ ነው። በዚሁም ላይ ደመናው ወርዶ የጋረደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ ሳይሆን ሐዋርያቱንም ጭምር ነበር። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚነግረን ደመናው ጌታን ብቻ ጋርዶት ቢሆን ኖሮ፣ ሐዋርያቱ "እርሱን ስሙት" የሚለውን ቃል ራሱ ክርስቶስ ለራሱ የተናገረው ሊመስላቸው በቻለ ነበር። 

ቅዱስ ጴጥሮስ "አትሙት" ያለው መምህሩን በፍጹም ልቡ ስለሚወደው መሆኑ አያጠራጥርም። ነገር ግን ጴጥሮስ ጌታን የቱንም ያህል ቢወደው፣ ፍቅሩ ግን ከወለደው ከባሕርይ አባቱ ከአብ አይደለም ሊበልጥ ሊነጻጸርም አይችልም። ታዲያ አብ በእርሱ ደስ የሚለው፣ የሚወደው፣ አንድያ ልጁ እንዲሞት ፈቃዱ ከሆነ፣ የአብን ያህል ሊወደው የማችለው አረጋዊው ጴጥሮስ ለምን "አትሙት" እያለ ይቃወማል?!

አብ ምትክ የሌለው ልጁ ወልድ ሰው ሆኖ በክፉዎች እጅ ሲንገላታ እና እስከ መስቀል ሞት ሲደርስ እያየ ዝም ያለው ስለማይወደው አይደለም። ዓለም ያለ ልጁ መከራና ሞት ስለማትድን ነው እንጂ። ከዚህ ምን እንማራለን?  ዛሬም ወደ መከራ የምንገባ የጸጋ ልጆቹ የምንሆን እኛ ክርስቲያኖች "እግዚአብሔር እንዲህ ስሆን ዝም ያለኝ  ስለማይወደኝ ነው" አንበል። ባገኘን ጥቂት የሥጋ መከራና ሕመም የሚበልጠውን የነፍስ ጤና የምንሸምት ከሆነ እግዚአብሔር ዝም ይላል። ዝም የሚለው መከራችንን ስለማያይ ሳይሆን ከመከራው ጀርባ ያለው ዓላማ ታላቅና የተቀደሰ እንደ ሆነ ስለሚያውቅ ነው።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን


Forward from: Henok Haile
+ ከታቦር ተራራ አትቅር +

"አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ። "
ማር 9: 3
/ሽራፊ ሃሳቦች ከደብረ ታቦር ንባብ/

የወንጌላውያን ትሕትና ይደንቃል ፣ ማቴዎስ ማርቆስ ሉቃስ ስለ ደብረ ታቦር ሲጽፉ ዮሐንስ አልጻፈም። ዮሐንስ ተመርጦ የተገኘበትን ታሪክ "ተመርጬ" ብሎ አልጻፈም። የቀሩት ወንጌላውያን ደግሞ "እኛ የሌለንበትን ነገር አንጽፍም" አላሉም። አንድ ወንጌል እየሰበኩ የሚፎካከሩ ፣ የአንድ ቤት ጣሪያ እየሠሩ ቆርቆሮ የሚሻሙ የእኛ ዘመን አገልጋዮች አልነበሩምና እነርሱ ያልተመረጡበትን ታሪክ ለመናገር ተሯሯጡ። እኛን የማያካትት ክብር ፣ እኛን የማይጨምር ድግስ ጉዳይ ሲነሣ ለማይጥመን ፣ እኛ የሌለንበትን ፎቶ እንኳን ለማየት የማንፈልግ ፣ በእኛ በኩል ያለፈን ነገር ብቻ የምናራግብ ፣ የሌለንበትን ነገር ጥሩም ቢሆን እንኳን ለምናጣጥል "በእኔ በቀር ባዮች" ትምህርቱ ድንቅ ነው።

ሌላ ማሳያም አለ ማቴዎስ ወንጌላዊው ስለ ራሱ ታሪክ ሲጽፍ "ማቴዎስ የተባለ ቀራጭ በመቅረጫው ተቀምጦ" ብሎ በኃጢአት ከተዘፈቀበት ሥራ ላይ ወደ ክርስትና እንደተጠራ በግልጽ ሲጽፍ ሌሎቹ ወንጌላውያን ግን በሐዋርያት ዝርዝር ላይ ማቴዎስ ያሉትን ሰው ስለ ቀድሞ የቀራጭነት ሥራው ሲጽፉ ግን ሌዊ የሚል ተለዋጭ ስሙን ተጠቅመዋል። ትሑቱ ማቴዎስ ግን በሌሎች ወንጌላውያን የተሸሸገ የቀድሞ የኃጢአት አኗኗሩን ለእግዚአብሔር ይቅር ባይነት ማሳያ እንዲሆን ስለፈለገ ጭራሽ በሐዋርያት የስም ዝርዝር ላይ "ቀራጩ ማቴዎስ" ብሎ ራሱን ጠርቷል።

የሚገርመው ከቀራጭነት ከተጠራ በኋላ በቤቱ ታላቅ ድግስ ደግሶ ጌታችንን ከኃጢአተኞች ጓደኞቹ ጋር የተቀበለ መሆኑን በሌሎች ወንጌላውያን ሲጽፉ ማቴዎስ ግን ቀራጭነቱን አጉልቶ እንዳልጻፈ ሁሉ የግብዣው ነገር ደጋሹ እርሱ መሆኑን አድበስብሶ በመጻፍ አልፎታል።

★ ★ ★

ቅዱስ ጴጥሮስ "ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው" አለ። "ለእኛ" መልካም ነው የሚለው ቃል ድንቅ ነው። በእግዚአብሔር ቤት መኖራችን መልካምነቱና ጥቅሙ ለእኛ ነው እንጂ ለእግዚአብሔር አይደለም። የማንጠቅም ባሪያዎቹ ስሙን በአሕዛብ ዘንድ ከማሰደብ በቀር ለእርሱ ምን እንጠቅመዋለን። ለዚህም ነው ቅዱስ ባስልዮስ "ጌታ ሆይ የአንተ አምላክነት ለእኔ ያስፈልገኛል እንጂ የእኔ ፍጡርነት ለአንተ አያስፈልግህም" ያለው።
ስለዚህ ጴጥሮስ "ለእኛ መልካም ነው" አለ።

"ብትወድስ ሦስት ዳስ እንሥራ" አለ ፣ ጌታ ካልወደደ እንኳን ሦስት አንድ ዳስ መሥራት አይቻልም ፣ እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ" ስለዚህ "ብትወድስ" አለ።

የዋሁ ጴጥሮስ ለእኔ ልሥራ አላለም ፣ የሐዲስ ኪዳን ሐዋርያ ነኝ ብሎ የብሉይ ኪዳን ነቢያትን ከማክበር ወደ ኋላ አላለም። "አንተ ዓለት ነህ በዚህች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ" በተባለ ማግስት ለነቢያቱ ድንኳን ሊቀልስ የጠየቀ ከጴጥሮስ በቀር ማን አለ?

ከእግዚአብሔር አብ ግን "አትሙት" እስከማለት ለደረሰው ለነጴጥሮስ ንግግር "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" የሚል ትእዛዝ መጣ። ሃሳቡ ድንቅ ቢሆንም ቃሉን ሳይሰሙ ዳስ መሥራት መጀመር አይቻልም።

በዚያ ላይ ጌታ የመጣው በደብረ ታቦር ድንኳን አስጥሎ ሊኖር ሳይሆን በቀራንዮ በተሰቀለበት በመስቀሉ ካስማ በደሙ ድንኳን ተክሎ ሊያስጠልለን ነው። ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ "ጴጥሮስ ሆይ ለአንተ የፊቱን ብርሃን እያየህ በዚህ መኖር መልካም ነው ፣ እኛ ግን የምንድነው በተራራው ሲኖር ሳይሆን ወርዶ ፊቱን በጥፊ ሲመታ ነው" ብሎታል።

ጴጥሮስ የዋሁ "በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ" ላለው ለክርስቶስ ድንኳን ሊቀልስ ጠየቀ። በሰማይ "በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ድንኳን" ላለችው ሊቀ ካህናት ድንኳን ሊሠራ ለመነ። እዚህ አለ ሲሉት እዚያ ለሚገኘው ፣ በመንፈስ እየተነጠቀ አድራሻውን ለመወሰን ያስቸግር ለነበረው ኤልያስ እንዲቀመጥ ተስፋ አድርጎ ድንኳን ልሥራ አለ። እጅግ የተዋበችና በወርቅ በሐር ያጌጠችን የኦሪት ድንኳን ለሠራው ሙሴ ዓሣ አጥማጁ ጴጥሮስ ድንኳን ልሥራለት አለ። ሐዋርያት ነቢያቱን ሊያስተናግዱ የለመኑባት ደብረ ታቦር ፣ ሐዋርያት ነቢያቱን ለጌታ ቀኝ አዝማች ግራዝማች አድርገው በድንኳን አስቀምጠው እነርሱ እንደ ሎሌ ከደጅ ሊኖሩ የጠየቁ እነ ጴጥሮስ እንደምን ይደንቃሉ? ጴጥሮስ ሆይ አሁን በሰማይ ድንኳኖች ውስጥ እያገለገልህ ይሆንን? ደብረ ታቦርን አይተህ በደስታ "እንኑር" ያልከው ጴጥሮስ ሆይ የገነት ደስታ ስታይ ምን ተሰምቶህ ይሆን?

በእሳት ድንኳን ለመኖር ተስፋ የምናደርግ "በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል" የተባልን እኛስ ምንኛ የታደልን ነን?

★ ★ ★

በታቦር ተራራ ላይ የጌታችን ልብስ እንደ ፀሐይ አበራ ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ከፀሐይም በላይ ነው ፣ ፀሐይ አይቶ የወደቀ የለም የጌታችንን ልብስ ሲያዩ ግን የወደቁት ያበራው ከዚያ በላይ ስለሆነ ነው" ይላል።

ከጌታችን በዚያ ተራራ ከሙሴና ኤልያስ ጋር ነበረ። ሙሴ እንደምናውቀው ጽላቱን ተቀብሎ ሲወርድ ሕዝቡ "እባክህን ተሸፈንልን" ብለውት ፊቱን በመጎናጸፊያው ሸፍኖ ነበር። የሙሴ አምላክ ክርስቶስ ግን ደቀ መዛሙርቱ ሲወድቁ አይቶ በልብሱ እንዳይሸፈን ያበራው ፊቱ ብቻ ሳይሆን ልብሱም ነበር።

" አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ" ማር 9: 3
የሚለው ቃል ምንኛ የሚደንቅ ነው። በምድር ላይ ያለ አጣቢ ቢፈትግ ቢታገል የዚያን ያህል ሊያነጻው የማይችለው ነጭ እንዴት ያለ ነው? መቼም ሁላችን የምናውቀው ነጭ ነገር ሁሉ በምድር ላይ ባለ አጣቢ የታጠበ ስለሆነ እንዲህ ነው ማለት አንችልም። ብቻ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በምድር ያሉ አጣቢዎች ከሚያነጡት በላይ ልብስን ማንጣት ይችላል።

ይህ ቃል በኃጢአት እድፍ ልብሳችን ላደፈ ሁሉ መጽናኛችን ነው።

መቼም የምድር አጣቢዎች አቅማቸው ውስን ነው።
ቆሽሸን ያዩን ሰዎች ብንታጠብም አያምኑንም ፣ ቢያጥቡልንም በኅሊናቸው የሚያስቀሩብን ቆሻሻ አለ።
በሰው ዓይን አንዴ ቆሽሸህ አትገኝ እንጂ ከተገኘህ መቼም ነጭ አትሆንም። አንተ ግን የደብረ ታቦሩ ብርሃን መድኃኔ ዓለምን ብቻ "እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ" በለው "ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። " ብሎ በገባው ቃል መሠረት ነጭ ያደርግሃል።

እርሱ ወዳለባት የቅድስት ቤተክርስቲያን ተራራ በንስሓ ከደረስክና በታቦር ያበራውን ብርሃኑን ካበራልህ ነጭ ትሆናለህ። ከዚያ "አጣቢ የማያነጻውን ያህል ትነጻለህ" ከአብ የባሕርይ ልጅ ከብርሃኑ ፀዳል ስትቀርብ አንተም በጥምቀት ያገኘኸው የጸጋ ልጅነትህ ያንጸባርቃል። ነጭ በሆንህ ጊዜ የሚያዩህ ሁሉ "በበጉ ደም ልብስህ መታጠቡን"ና ነጭ መሆኑን አይተው ይደነግጣሉ ፣ ሊሰሙህ ያልወደዱ ሁሉ ለባሕርይ ልጁ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" ብሎ እንዳዘዘለት ለአንተም ጆሮ እንዲሠጡህ ያደርግልሃል።

አንተ ብቻ ከደብረ ታቦር አትቅር ፣ ካልሞትህ እንደ ኤልያስ ፈጥነህ ና ፣ በበደል ከሞትክም እንደሙሴ ተነሥተህ ና። ብቻ ወደ ደብረ ታቦር ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት ተስፋ አትቁረጥ ፣ እንደ ሙሴ ትሞታለህ እንጂ ምድረ ርስትን አታይም ብትባል ፣ እንደ ኤልያስ ትኖራለህ እንጂ ሞትን አታይም ብትባል ብቻ አንተ ከደብረ ታቦር አትቅር።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ደብረ ታቦር
ለንደን ፣ ብሪታንያ


#ቃለ_ወንጌል

13/12/2016
       
ሉቃ ፱÷፳፪-፴፰


  ከዚህም ቃል በኋላ ስምንት ቀን ያህል ቈይቶ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ያዕቆብንም ይዞ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ። ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሁለት ሰዎች እነርሱም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር፤ በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር።

ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ። ከእርሱም ሲለዩ ጴጥሮስ ኢየሱስን፦ “አቤቱ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነውና አንድ ለአንተ አንድም ለሙሴ አንድም ለኤልያስ ሦስት ዳሶች እንሥራ፡” አለው፤ የሚለውንም አያውቅም ነበር። ይህንም ሲናገር ደመና መጣና ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ።

ከደመናውም፦ “የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት፡” የሚል ድምፅ መጣ። ድምፁም ከመጣ በኋላ ኢየሱስ ብቻውን ሆኖ ተገኘ። እነርሱም ዝም አሉ ካዩትም ነገር በዚያ ወራት ምንም ለማንም አላወሩም። በነገውም ከተራራ ሲወርዱ ብዙ ሕዝብ ተገናኙት።

መልእክታት

ዕብ 11÷23-30
1ኛ ጴጥ 1÷15-ፍጻ
ሐዋ   6÷44-51
ምስባክ

    መዝ 88÷ 12-13

ታቦረር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌስኁ፤

ወይሴብሑ ለስምከ፤

መዝራዕትከ ምስለ ኃይል።


Forward from: ያሬዳውያን
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
ስርአተ ማህሌት ዘበዓለ ደብረ ታቦር
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ሥርዓተ ነግሥ
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
@EOTCmahlet
መልክአ ሥላሴ፦
ሥላሴክሙ ሥላሴ ይረስየኒ መካነ፤ድኅረ ተዋሓድኩሰ ዘሥላሴሁ ብርሃነ፤ዮርዳኖስክሙ ዝየ እስመ ኵለንታየ ኮነ፤ኢየኀሥሥ እምዮርዳኖስ ሰማዕተክሙ ምእመነ፤ወኢይትሜነዮ ለታቦር እስመ ታቦር አነ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
ሰላም ለከ ኦ ደብረ ታቦር፤ዘአስተርአየ ላዕሌከ ትእምርተ መንግስት ህየ ንሰግድ ኩልነ፤ኀበ ተሰብሐ እግዚእነ
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ሰላም ለከ ኦ ደብረ ታቦር ዘአስተርአየ ላዕሌከ ትእምርተ መንግስት/2/
ህየ ንሰግድ ኩልነ ኀበ ተሰብሐ እግዚእነ/2/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ነግሥ
ዳዊት ነቢይ እምነ አድባራት አልዓላ ፤አምሳለ ኪሩብ አስተማሠላ ፤አመ ወአለ ባቲ ክርስቶስ ርእሰ መሐላ ፤በደብረታቦር ካልዕተ ጸናፊ ጌልጌላ ፤ናሁ ተመነየ በማዕከላ ጴጥሮስ ከመ ይሣርር ሠቀላ ።
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
ደብር ዘበእንቲአሁ ጸርሐ፤ዳዊት ነቢይ እንዘ ይብል፤ወሰምዐኒ እምደብረ መቅደሱ
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክአ ፍልሰታ፦
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ስቡሐ ዘተሰብሐ፤እምነ ፀሐይ ወወርህ ስነ ስብሐትኪ አብርሃ ፤ እንበሌኪ ድንግል ወእንበለ ወልድኪ በኩረ ፍስሐ ፤ አልቦ ለሞት ማዕሰሪሁ ዘፈትሐ፤ ወሙታነ በሲኦል አንቅሐ።
@EOTCmahlet
ዚቅ፦
እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤ እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ኢየሱስ፦
ሰላም ለዝክረ ስምከ ስመ መሓላ ዘኢይሔሱ፡ ዘአንበረ ቅድመ እግዚአብሔር በአትሮንሱ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዳዊት ባሕርየ ከርሡ፡ አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቄጸል በርእሱ፡ አህጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌስሁ ወይሴብሑ ለስምከ ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌስሑ ወይሴብሑ ለስምከ ዮም ታቦር
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌስሑ በስመ ዚአከ/፪/
ወይሴብሑ ለስምከ ይሴብሑ ለስም/፪/
@EOTCmahlet
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለልሳንከ በደብረ ታቦር ዘአልኆሰሰ፡ለብርሃን ዐቢይ እስከ ጽላሎቱ ተሐውሰ፡ ነበልባለ እሳት ክርስቶስ ዘተዋሐድከ ጳጦሰ፡በዋዕየ ፍቅርከ ከመ ሥርወ አእዋም የብሰ፤ውሣጤ ሕሊናየ ነደ ወልብየ ጤሰ።
@EOTCmahlet
ዚቅ
ወሪዶሙ እምደብር እም ደብረ ታቦር አዘዞሙ ኢይንግሩ ዘርእዩ በደብር እስከ አመ ይትፈጸም በዕድሜሁ
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ወሪዶሙ እምደብር እምደብር እምደብረ ታቦር  ኢይንግሩ ዘርእዩ በደብር /፪/
እስከ አመ ይትፈጸም በዕድሜሁ ይትፈጸም/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለሰኰናከ እንተ ይስተጋብእ ኩሎ፡ ኃበ ኅደገ ወቀጽዐ ውስተ ሠሌዳ ኰኩሕ ሥዕሎ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመልአከ ዓለም ዘትትቤቀሎ፡ ስብሐቲከ እርአይ እግዚኦ እምቅድመ ዓለማት ዘሀሎ፤መንጦላዕተ ዓይንየ ቅላዕ ወአብርህ ጸዳሎ።
@EOTCmahlet
ዚቅ
ስብሐቲሁ ዘእምሃቤሁ ወውዳሴሁ እምዚአሁ አኃዜ አለም ለሊሁ ሰይፈ በቀል ውስተ እዴሁ ፍትሐ ግፉዓን ይወጽእ እምጽሩሕ
@EOTCmahlet
ወረብ
አሐዜ አለም ዘእምሃቤሁ ስብሐቲሁ ወውዳሴሁ እምዚአ/፪/
ሰይፈ በቀል ውስተ እዴሁ ፍትሐ ግፉአን እምጽሩይ ህይወት/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክአ ኢየሱስ
እምኩሉ ይኄይስ በሥላሴከ ተአምኖ፡ ወበወላዲትከ ተማኅፅኖ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ እምቤተ መንግሥት ወተክህኖ፡ ተሰብኦተከ እመቦ ዘያስተሐቅር መኒኖ፡ ያንኰ ርኩር ታሕተ ደይን ግዱፈ ከዊኖ
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ነአምን ዘንተ ሥላሴ አሐዱ ውእቱ አምላክ ፍጹም ዘእምኔሁ ለአብ ወወልድ ተወልደ በአምሳለ ዚአሁ ኅቡር ህላዌሁ ነአምን ንሕነ ነአምን።
@EOTCmahlet
ወረብ
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ/፪/
አሐዱ ውእቱ አምላክ ፍፁም አሐዱ ውእቱ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ምልጣን:-
ደብር ርጉዕ ወደብር ጥሉል ለምንት ይትነሥዑ አድባር ርጉዓን ደብር ዘሠምሮ የኀድር ውስቴቱ እግዚአብሔር አማን ተሰብሐ በደብረ ታቦር።
@EOTCmahlet
አመላለስ፦
አማን በአማን አማን በአማን ተሰብሐ አማን በአማአማን በአማ/፪/
ተሰብሐ በደብረ ታቦር/፪/
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ደብር ርጉዕ ወደብር ጥሉል ደብር ርጉዕ ወደብር ጥሉል ለምንት ይትነሥዑ አድባር ርጉዐን/፪/
ደብር ዘሠምሮ እግዚአብሔር የሐድር ውስቴቱ እግዚአብሔር/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
እስመ ለዓለም
ወተወለጠ ራዕዮ በቅድሜሆሙ ወአልባሲሁኒ ኮነ ጸአዳ ከመ በረድ ይቤሎ ጴጥሮስ ለኢየሱስ ሊቅ ንንበር ዝየ ወንግበር ሠለስተ ማህደረ፤ማ-አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ፤ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማህደረ።
@EOTCmahlet           
አመላለስ፦
አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ/፪/
ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማህደረ/፬/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ፦
ወተወለጠ ራዕዮ በቅድሜሆሙ ራዕዮ በቅድሜሆሙ/፪/
ወአልባሲሁኒ ኮነ ጸአዳ ከመ በረድ/፪/

👇👇👇👇👇🇪🇹
👉@EOTCmahlet👈                 
👉@EOTCmahlet👈
👉@EOTCmahlet👈
🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹

      @EOTCmahlet
  #ይቀላቀሉ & #ለወዳጅዎ_ሼር_ያርጉ




በተጨማሪም ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ሹመት፣ ሽልማትና ክብር ፈላጊዎች ነበሩ፡፡ ከዚህ ምድራዊ ሐሳብ እንዲታደሱ ለይቶ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለድኅነተ ዓለም የመጣው በሞቱ ድኅነት የሚሆነን አምላክ “ልሰቀል ነው” ባለ ጊዜ “አይሁንብህ” ብሎት ስለነበር እንዲህ ያለው ሐሳብ የጠላት እንጂ የሰው ልጆች ሊሆን አይችልም ከሞቱ በቀር ድኅነት ሊያስገኝልን የሚችል የለምና፡፡ ደቀ መዝሙሩ ግን መምኅሬ ከሞተ ክብሬ ምንድን ነው? የሚለውን በማሰብ “አይሁንብህ” አለ፡፡ በሌላም ጊዜ እንደዚሁ “ሁሉን ትተን ተከተልንህ እንግዲያስ ምን እናገኝ ይሆን?” በማለት በጠየቁት ጊዜ ጌታችን ግን ዋጋችሁ ሰማያዊ ክብራችሁ ዘላለማዊ ነው ሲል እስከ ፍጹማን መዓርግ /ነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ/ አድርሶ ብርሃነ መለኮትን ገልጦ ተስፋውን ነግሯቸዋል፡፡

ሁለቱ ወንድማማች ደቀ መዛሙርትም እናታቸውን ማርያም ባውፍልያን ልከው ሹመት ሽልማት መዓርግ እንዲሰጠቸው ለምነዋል፡፡ ስለዚህም ጌታችን በደብረ ታቦር “በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ነገር” ስለሞቱ እንዲነጋገሩ አደረገ፡፡ ይህ ምድራዊ ሐሳብ ከልባቸው እንዲጠፋ እነርሱን ወደ ቅዱስ ተራራ ይዟቸው ወጥቷል፡፡

ሁለቱን ከነቢያት ሦስቱን ከሐዋርያት ለምን ወሰዳቸው?

በቤተክርስቲያን ነቢያት ያስተማሩት ብሉይ ኪዳንና ሐዋርያት የሰበኩት ሐዲስ ኪዳን ይነገራሉና ነው፡፡ በደብረ ታቦር ነቢያትም፣ ሐዋርያትም እንደ ተገኙ ሁሉ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ብሉይና ሐዲስ ኪዳን ይሰበካል፡፡ ሥርዓተ ቅዳሴ የሚፈጽሙ ልዑካን አምስት መሆናቸውም በደብረ ታቦር የተገኙትን ሙሴን፣ ኤልያስን፣ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ያስታውሱናል፡፡ ዘወትር በቤተ መቅደሱ የሚፈተተው ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ደግሞ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን የገለጠው የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው፡፡ ደብረ ታቦር የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው፡፡ በሕግ በሥርዓት ያገቡ ሰዎችም፣ በንጽሕና በድንግልና በምንኩስና የአምላካቸውን ፈቃድ የሚፈጽሙ  መናንያን፣ ባሕታውያን፣ መነኮሳት አንድ ሆነው መንግሥተ ሰማያትን እንደሚወርሷት ለማስተማር ከሕጋውያን ሙሴን ከደናግል ደግሞ ኤልያስን ወደ ደብረ ታቦር ወስዷቸዋል፡፡ ሙሴን ከመቃብር አንሥቶ ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ በደብረ ታቦር ተራራ አብረውት እንዲገኙ ያደረገው ሰዎች ሙሴ ነው ወይም ኤልያስ ነው በሚል ሲጠራጠሩ እንዳይኖሩ መለኮታዊ ምሥጢርን በተግባር ለማስተማር ነው፡፡

የደብረ ታቦር ምሳሌነት

"ደብረ ታቦር" የወንጌል ምሳሌ ነው፡፡ ተራራ ሲወጡ በጣም ያስቸግራል፤ ከብዙ ድካምና ውጣ ውረድ በኋላ ተራራውን ጨርሰው ከተራራ ላይ ሲወጡ ግን ሜዳና ገደሉን ሁሉ ያሳያል፡፡ ወንጌልንም በሚገባ ከተማሯት ጽድቅን ከኃጢአት ለይተን እንድናውቅ ታደርገናለች፡፡ "ደብረ ታቦር" የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነው፡፡ በደብረ ታቦር ምሥጢረ ሥላሴ እንደተገለጠ ሁሉ በቤተ ክርስቲያንም የቅድስት ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት ይነገርባታል፡፡ ተራራ መሠረቱ ከመሬት የላይኛው ጫፍ ከሰማይ እንደሆነ ሁሉ፤ ቤተ ክርስቲያንም መሠረቷ በምድር ሲሆን ራሷ በላይ በሰማይ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮቿ የተጠሩት ከምድር (ከዓለም) ሲሆን ክብራቸው ግን በሰማይ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እኛስ ሀገራችን በሰማይ ነውና›› እንዲል፡፡(ፊልጵ.፫፥፳)፡፡ 

ቅዱስ ጴጥሮስም "ለእኛ በዚህ መኖር መልካም ነው" ብሏል፤ ይህን ያለው ክርስቲያኖች የቤተ ክርስቲያናችንን ሕግና ሥርዓት አክብረን፣ በምግባር በትሩፋት አድገንና አፍርተን፣ በፍቅረ እግዚአብሔር በፍቅረ ሰብእ መኖር በሥጋዊ ዓይን መከራና ድካም መስሎ ቢታየንም ፍጻሜውን ግን ዘለዓለማዊ ሕይወት መሆኑን አምነን እስከ ሕይወታችን ፍጻሜ በመንፈሳዊ ጥበብ እንዲንመራ ያስገነዝበናል፡፡

ጅራፍ፡-በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምሥጢር በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምሥጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ እና ጅራፍ ማጮኽ ሁለት ዓይነት ምሥጢር ይዞ የሚከወን ትውፊታዊ ተግባር ነው፡፡ የመጀመሪያው ግርፋቱንና ሞቱን እናስብበታለን፡፡ እንዲሁም ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምስክርነት ቃል፣ እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡ የጅራፍ ትውፊታዊነት ውርስ መጽሐፋዊ ትምህርትና ምሥጢር ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ጨዋታውን በተራራማ አካባቢ፣ ከመኖሪያ ቤት ርቆና፣ በሜዳ ማድረጉ ጠቃሚ ነው፡፡ ጅራፍን በርችት መቀየር የሚያመጣውን የምሥጢር ተፋልሶ ያለው በመሆኑ ልናስወግደውና ምሥጢራዊ ትውፊቱን የስቀጠል ሥራ መስራት አለብን፡፡

ችቦ፡- ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት በመሆኑ ችቦ ለኩሰን በዓሉን እናከብራለን፡፡ ይህ ትውፊታዊ ሠርዓት የመጣው በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ስለቀሩ ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ስለሄዱ ያንን ታሪክ እያዘከርን በዓሉን እናከብራለን፡፡ የችቦው መንደድም ሌለኛው ትርጉም ደግሞ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን፣ መከራ እየተቀበለም አርአያ ምሳሌ ብርሃን መሆኑን ያሳያል፡፡ በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆናል፡፡

ሙልሙል፡-በችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን፣ ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን “ቡሄ” በሉ እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም ዘምረው እንዳበቁ “ሙልሙል” ዳቦ ይሠጣል፡፡ ሕፃናቱም መጥተው ሲዘምሩ ዳቦ የመስጠት ልማዳዊ ብቻ አልነበርም፤ ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ መሆናቸውንም ያመልክታል፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት “የምሥራች” ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሄዱም፣ ልጆችም ዘምረው፣ አመስግነው፣ “ውለዱ ክበዱ፣ ሀብት አግኙ፣ የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች ያድርጋችሁ….” ይላሉ፡፡

ጠቅልል ባለ መልኩ ሲታይ በዓለ ደብረ ታቦር ከእነዚህ ምስክር ካላቸው ትምህርቶቹ፣ ምሥጢር ከሚራቀቅባቸው ትርጓሜያቱና ከትውልድ ትውልድ በቅብብል በተላለፈው ቅዱስ ትውፊት ጋር ሃይማኖታዊ ባህል ሆኖ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡ ይህ ደግሞ በቅብብሎሽ ለአዲሱ ትውልድ የሚቀጥለው ወጣቱ ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ይዘው እንዲያድጉ የማድረግ የመጀመሪያዎቹ ባለድርሻዎች ወላጆች ናቸው፡፡ ሕፃናቱም ዝማሬውን ሲጀምሩ “ከሰጡን እንነሣ ከነሱን እናርዳ” ማለትም ከሰጡን እንመርቃለን ካልሰጡን እንራገማለን በማለት ትኩረት ሊደረግብት የሚገባው ነገር ደግሞ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ወደ ገንዘብ ማግኛነት የቀየሩት ሰዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየበዛ መሄዳቸው ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የምሥጢር ግምጃ ቤት በመሆኗ የምታከናውነውን ሁሉ አውቀን ተረድተን ለቀሪው ትውልድ ማስተላለፋ እንችል ዘንድ ከክፉ ጠላት ከሰይጣን ፈተና፣ በሽታ ከመሳሰሉት ችግሮች ለመዳን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ተጠግተን ከክፉ ነገሮች ሁሉ ተጠብቀን ዕድሜ ለንስሓ ዘመን ለፍሥሓ ተሰጥቶን፣ በማስተዋልና ሁሉን በማየት የሚጠቅመንን በመምረጥ በሥነ-ምግባር ታንጸን አገርንና ወገንን የምንጠቅም እንዲንሆን የአምላክ የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን፤ ቸርነቱም ይርዳን፡፡

ምንጭ፡- 1. መጽሐፈ ታሪክ ወግስ፣ መምህር አፈወርቅ ተክሌ፤ ፳፻፭ ዓ.ም፣ ገጽ ፫፻፲፭-፫፻፲፯፡፡

        2. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ፤፳፻፯ ዓ.ም፣ ገጽ ፻፲፩፡፡


በዓለ ደብረ ታቦር


ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን የምናከብረው የደብረ ታቦር በዓል ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን፣ ክብረ መንግሥቱን የገለጠበት በመሆኑ በየዓመቱ  በድምቀት ይከበራል፡፡ (ማቴ .፲፯፡፩፣ ማር.፱፡፩፣ሉቃ.፱፡፳፰)፡፡

ደብረ ታቦር፡- ‹‹ደብረ ታቦር›› ደብር እና ታቦር ከሚባሉ ከሁለት ቃላት የተገኘ ሲሆን ‹‹ደብር›› ማለት ተራራ ማለት ነው፤ ‹‹ታቦር›› ደግሞ በናዝሬት አካባቢ በሰማርያ አውራጃ በገሊላ የሚገኝ የረጅም ተራራ ስም ነው፡፡ የደብረ ታቦር ተራራ ከገሊላ ባሕር በምዕራባዊ በኩል ፲ ኪሎ ሜትር ርቀት የሚገኝ  ሲሆን፤ ከፍታው ከባሕር ጠለል በላይ ፭፻፸፪ ሜትር ነው፡፡ በዚህ ተራራ ላይ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን እንደሚገልጽ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ “ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል” በማለት አስቀድሞ ተናግሮ ነበር፡፡ (መዝ. ፹፰፥፲፪) ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ተራራ ላይ ብርሃነ መለኮቱን በመግለጡ የነቢያት ትንቢት ተፈጽሟል፡፡ በዘመነ መሳፍንት ባርቅ ሲሳራን ከነሠራዊቱ ድል ያደረገው በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ነበር፡፡ (መሳ. ፬፥፮)፡፡ የዚህም ታሪክ ምሳሌነቱ ባርቅ የጌታችን ሲሳራ ደግሞ የአጋንንት ነው፡፡ ጌታችን በደብረ ታቦር ክብሩን በመግለጥ በአይሁድ እያደረ አምላክነቱን እንዲጠራጠሩ ያደረጋቸውን አጋንንት ድል የማድረጉ ምሳሌ ነው፡፡ በዚህ ተራራ ነቢዩ ሳሙኤል ትንቢት ተናግሮበታል፡፡ ንጉሥ ሳኦልም ከሦስት ሰዎች ጋር ተገኝቶበታል (፩ኛ ሳሙ.፲፡፫)፡፡ ርእሰ አበው አብርሃምና ኖኅ በዚህ ተራራ ላይ ቀስተ ደመና ተተክሎ ያዩ ሲሆን አባታችን ኖኅ ይህንን ተራራ ‹‹መካነ ብርሃን፤ የብርሃን ቦታ›› ብሎ ጠርቶታል፡፡

የሐዲስ ኪዳን ወንጌል ጸሓፊያን ግን ‹‹ረጅም ተራራ፣ ቅዱስ ተራራ›› በማለት ጠርተውታል፡፡ ሆኖም ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ተራራ ላይ ክብሩን እንደገለጠና የዚህም ተራራ ስም ታቦር መሆኑን ሐዋርያት በሲኖዶሳቸው ገልጠዋል፣ በትውፊትም ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድም ይህንን ረጅም ተራራ ደብረ ታቦር እያለ በድጓው አስፍሮታል፡፡

በዚህ በዓል አምላክነት፣ ጌትነት፣ ንግሥና የባሕርይ ገንዘቡ መሆኑን፣ የድኅነታችን መሠረቱም የጌታችን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው መሆን (የተዋሕዶ ምሥጢርን)  የገለጸበት በዓል ነው፡፡ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ “እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኃኒተ በማእከለ ምድር/ እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፣ በምድርም መካከል መድኀኒትን አደረገ” (መዝ.፸፪፡፲፪) በማለት ትንቢት የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ማእከለ ምድር በተባለች በቀራንዮ ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ቤዛነት ዓለሙን ሁሉ አድኗልና፡፡ ሆኖም ግን የጌታችን ነገረ ተዋሕዶ ምሥጢር በሥጋዊ ዕይታ ውስጥ ለሆኑት ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖባቸዋል፡፡

ብርሃነ መለኮቱ የተገለጠበት  ምሥጢር፡-

ሦስቱ ሐዋርያት በተራራው ሳሉ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልኩ በፊታቸው ተለወጠ፡፡ ይህ የብርሃነ መለኮቱ የመገለጥ የተዋሕዶ ምሥጢር እንጂ ውላጤ/መለወጥ/ አይደለም፡፡ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” እንዲል፡፡(ሚል ፫፥፮)፡፡ ሦስት ክንድ ከስንዝር አካል ምሉዕ ብርሃን ሆኗል፡፡ ፊቱም እንደ ፀሐይ ብሩህ ሆነ፡፡ ልብሱም እንደ በረድ ጸዓዳ ሆነ፡፡ ይህ ሁሉ ነገረ ተዋሕዶን እንዲረዱ የተደረገ የተዋሕዶ ምሥጢር ነው፡፡ ሰውነቱን ባይክዱም አምላክነቱን ግን ተጠራጥረው ስለነበር እነር በሚያውቁት በባሕርየ ትስብዕቱ አምላክነቱን ከሰውነቱ አዋሕዶ ምሥጠረ ተዋሕዶን ገለጠላቸው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በ፴፪ ዓመት ከ፮ ወር ከ፲፫ ቀን፣ በዘመነ ማቴዎስ፣ በወርኃ ነሐሴ በዕለተ እሑድ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን ገልጧል፡፡

ሙሴንና ኤልያስን በደብረ ታቦር ለምን አመጣቸው?

ሙሴን ከመቃብር ጠርቶ ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን ወደ ደብረ ታቦር እንዲመጡ ያደረገበት ምክንያት ጌታችን አምለካችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ መሆኑን እንዲመሰክሩ ነው፡፡ ሙሴ ከመቃብር ተነሥቶ ስለጌታችን የሰጠው ምስክርነት፡- “እኔ ባሕር ብከፍልም፣ውኃ ከዓለት ላይ ባፈልቅም፣ በዓመደ ደመና ዕብራውያንን እየመራሁ ጠላትን ድል ባደርግም፣ ደመና ብጋርድም፣መና ከደመና ባወርድም በአንተ መልካም ፈቃድ ነው፤ ብዙ ተአምራንት እንዳደርግ የረዳኝን የእኔን ፈጣሪ እንዴት ሙሴ ነው ይሉሃል? የሙሴ አምላክ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” ሲል ኤልያስም ደግሞ “እኔ ሰማይ ዝናብ እንዳይሰጥ ብለጉም፣ እሳት ባዘንብም፣ እስራኤልን ከክፋታቸው ማዳን የማይቻለን ነኝ እንዴት የእኔን ፈጣሪ ኤልያስ ነህ ይሉሃል? የኤልያስ ፈጣሪ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” በማለት የባሕርይ አምላክነቱን በደብረ ታቦር ላይ መስክረዋል፡፡ ሙሴና ኤልያስ የተጠሩበት ሌላው ምሥጢር ሙሴ “ጀርባዬን ታያለህ፤ ፊቴን ግን አይታይም” ተብሎ ስለነበር (ዘፀ.፴፫፡፳፫) ከሞትም ከብዙ ዘመናት በኋላ ተነሥቶ ጌታን በአካል የማየትና ምስክርንት የመስጠት የቃል ኪዳን ተስፋ መፈጸሙን፣ ኤልያስም “በኋለኛው ዘመን ምስክሬ ትሆናለህ” ስለተባለ ያንን ለመፈጸም ሲሆን ካገቡት ሙሴን ከደናግል ኤልያስን ያመጣቸው መንግሥተ ሰማያት በሕግ የተጋቡ ሕጋውያንና ሥርዐት ጠብቀው የሚኖሩ ደናግላን እንደሚወርሷት ለማስተማር ሁለቱን ወደ ድበረ ታቦር አምጥቷቸዋል፡፡

መድኃኒታችን ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን “መነይብልዎ ሰብእ ለወልደ እጓለ እምሕያው፤ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል? ብሎ ጥየቋቸው ነበርመና ሲመልሱ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ›› ብለውት ነበርና (ማቴ.፲፮፡፲፬)፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ‹‹በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር›› ያለውም የነበራቸውን ክብር ታላቅነት ያስረዳል፡፡

በባሕርዬ አይተህ ደንግጠህ እንዳትሞት በብርሃን ሠረገላ ሆኜ እስካልፍ ድረስ ቀዳዳ ባለው ዋሻ እሠውርሃለሁ፡፡ በብርሃን ሠረገላ ሆኜ ካለፍሁ በኋላ እጄን አንሥቼልህ ከወደ ኋላዬ ታየኛለህ እንጂ በባሕርዬ ግን ፊቴን ማየት አይቻልህም›› የሚል ምላሽ ሰጥቶት ነበር (ዘፀ. ፴፫፡፲፫-፳፫)፡፡ ይህም በፊት የሚሄድ ሰው ኋላው እንጂ ፊቱ እንደማይታይ ጌታም በባሕርዩ አለመገለጡን ያስረዳል፡፡ ምሥጢሩም አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም አምላክ ሰው ሆኖ ሥጋን ተዋሕዶ በደብረ ታቦር በባሕርዩ እስኪገለጥለት ድረስ ሙሴ በመቃብር ተወስኖ እንደሚቆይ ያጠይቃል፡፡ በእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ከሙታን ተነሥቶ ከዘመናት በፊት የተመኘውን የአምላኩን ፊት ለማየት የታደለው ሊቀ ነቢያት ሙሴ የተወለደውም በዚህች ዕለት ነው፡፡ ነቢዩ ኤልያስም “በኋለኛው ዘመን ምስክሬ ትሆናለህ” የተባለው ትንቢትም በዚህች ዕለት ተፈጸመ፡፡


ሦስቱን ሐዋርያት ለምን ብቻቸውን ወሰዳቸው?

አዕማደ ሐዋርያት ተብለው የተጠሩት ጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ናቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጴጥሮስ፣ ዮሐንስና ያዕቆብን “አዕማድ ሐዋርያት” እያለ ጠርቷቸዋል፡፡(ገላ.፪፥፱) ስያሜውን ያገኙበት  ምክንያት ጌታችን በኢያኢሮስ ቤት ልጁን ሲፈውስ፣ በጌቴ ሴማኒ ሲጸልይና በደብረ ታቦር ምሥጢረ መለኮቱን ሲገልጥ ከእርሱ ስላልተለዩና ይዟቸው ስለሄደ ነው (ማር.፭፥፴፬-፵፫)

20 last posts shown.