📍ተፈጥሮ በአጠቃላይ እጅግ በጣም የተወሳሰበ ሂደት ነው ፣ እናም በውስጡ ጥሩም ይሁን መጥፎ ነገር እንደያዘ ለመናገር ከባድ ነው። ምክንያቱም የመጥፎ ነገር ውጤት ምን እንደሚሆን በጭራሽ አይታውቅም ፣ ወይም ደግሞ መልካም ዕድል ምን ይዞ እንደሚመጣ በጭራሽ አይታውቅም።
🔆በአንድ ወቅት አንድ የቻይና ገበሬ ፈረሱ ሸሽቶ ተሰወረበት ፡፡ የዚያን ዕለት ምሽት ሁሉም ጎረቤቶቹ ተሰብስበው ሊያፅናኑት መጡ ፡፡ እነሱም “ፈረስህ በመጥፋቱ በጣም አዝነናል ፡፡ ይህ በጣም መጥፎ ነገር ነው አሉት ፡፡
”ገበሬውም“ ምናልባት ”አላቸው ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ፈረሱ ሰባት የዱር ፈረሶችን ይዞ ወደ ቤቱ ተመለሰ
ምሽት ላይ ሁሉም ጎረቤቶቹ ወደ ቤቱ በመምጣት“ ዕድለኛ ነህ በጣም ፡፡ እንዴት ያለ ታላቅ ክስተት!! አሁን እኮ ስምንት ፈረሶች አሉህ! ” አሉት።
ገበሬው እንደገና“ ምናልባት ”አላቸው ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ልጁ ከፈረሶቹ አንዱን ለመጋለብ ሲሞክር ወድቆ እግሩን ተሰበረ ፡፡ ጎረቤቶቹም “ ይሄ ደግሞ በጣም መጥፎ አጋጣሚ ነው” አሉት።
ገበሬውም በድጋሚ “ምናልባት” ብሎ መለሰላቸው ፡፡
🔆በሚቀጥለው ቀን የግዳጅ መኮንኖች ሰዎችን ወደ ጦርርነት ለማሰማራት በመጡበት ጊዜ የገበሬው ልጅ የተሰበረ እግር ስለነበረውው ልጁን አይመጥንም ብለው ጥለውት ሄዱ ፡፡ እንደገና ጎረቤቶቹ ሁሉ መጡ እና “ይሄ እንዴት ደስ ይላል ልጅህ እኮ ጦርነት ከመግባት ተረፈ!” አሉት ፡፡
አሱ ግን እንደገና “ምናልባት” አላቸው፡፡
🔑ገበሬው ስለ ትርፍ ወይም ኪሳራ ፣ ጥቅምና ጉዳት ከመሳሰሉ ነገሮች ከማሰብ በጥብቅ ተቆጥቧል፣ ምክንያቱም የህይወት ክስተቶች በጭራሽ ይዘው የሚመጡትን ነገር ማናችንም አናውቅም። ብዙዏቻችን በህይወት ባህር ውስጥ የምንሰምጠው፤ እንደገበሬው ከኑሮ ጋር በቀላሉ መንሳፈፍን ስላለመድን ነው። በህይወታችን ወስጥ በእኛ ቁጥጥር ስር የሆኑ ነገሮች አሉ፤ ሌሎች ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ደግሞ እጅግ ብዙ ነገሮች ይኖራሉ።
💡በኑሮ ባህር ውስጥ መስመጥ የሚከሰተው ታዲያ፤ ከእኛ ቁጥጥር ወጪ የሆኑ ነገሮች ላይ ግትርነታችንን ለማሳየት ስንሞክር ነው። መለወጥ የማንችለውን ነገር በጉልበት ለመለወጥ ስንሞክር፤ የመዋኘት ጥበቡ ጠፍቶናል ማለት ነው። ህይወት ወደድንም ጠላንም ባልታሰቡ ፈተናዎች እና ስጦታዎች የተሞላች ነች። እንደ ገበሬው ረጋ ብለን ካልተንሳፈፍን በፍጹም ከለውጥ ጋር ተግባብተን ለመኖር አይቻለንም።
📍እናም ወዳጄ ዓለም እና የሰው ልጅ ተፈጥሮ በብዙ ስንክሳር የተሞሉ ናቸው። ባሳለፍከው ህይወት ብዙ ክስተቶች ታይተዋል። የሚያሳዝንም የሚያስደስቱም ሁኔታዎች የህይወት ገጾች ናቸው። ሁሉ ይመጣል፣ ሁሉም ይሄዳል። ያለፈውና የሚሄደውን በሰላም ሸኘው። አሁን ካለው ጋር በሰላም ተከባብረህና ተሳስበህ ኑር። ዘልዓለማዊ ክስተት የለም፣ ለውጥ እንጂ ። ከሁኔታዎች በላይ መሆንን እወቅበት። መረጋጋት መልካም ነው።
ውብ ምሽት❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanitybot
🔆በአንድ ወቅት አንድ የቻይና ገበሬ ፈረሱ ሸሽቶ ተሰወረበት ፡፡ የዚያን ዕለት ምሽት ሁሉም ጎረቤቶቹ ተሰብስበው ሊያፅናኑት መጡ ፡፡ እነሱም “ፈረስህ በመጥፋቱ በጣም አዝነናል ፡፡ ይህ በጣም መጥፎ ነገር ነው አሉት ፡፡
”ገበሬውም“ ምናልባት ”አላቸው ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ፈረሱ ሰባት የዱር ፈረሶችን ይዞ ወደ ቤቱ ተመለሰ
ምሽት ላይ ሁሉም ጎረቤቶቹ ወደ ቤቱ በመምጣት“ ዕድለኛ ነህ በጣም ፡፡ እንዴት ያለ ታላቅ ክስተት!! አሁን እኮ ስምንት ፈረሶች አሉህ! ” አሉት።
ገበሬው እንደገና“ ምናልባት ”አላቸው ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ልጁ ከፈረሶቹ አንዱን ለመጋለብ ሲሞክር ወድቆ እግሩን ተሰበረ ፡፡ ጎረቤቶቹም “ ይሄ ደግሞ በጣም መጥፎ አጋጣሚ ነው” አሉት።
ገበሬውም በድጋሚ “ምናልባት” ብሎ መለሰላቸው ፡፡
🔆በሚቀጥለው ቀን የግዳጅ መኮንኖች ሰዎችን ወደ ጦርርነት ለማሰማራት በመጡበት ጊዜ የገበሬው ልጅ የተሰበረ እግር ስለነበረውው ልጁን አይመጥንም ብለው ጥለውት ሄዱ ፡፡ እንደገና ጎረቤቶቹ ሁሉ መጡ እና “ይሄ እንዴት ደስ ይላል ልጅህ እኮ ጦርነት ከመግባት ተረፈ!” አሉት ፡፡
አሱ ግን እንደገና “ምናልባት” አላቸው፡፡
🔑ገበሬው ስለ ትርፍ ወይም ኪሳራ ፣ ጥቅምና ጉዳት ከመሳሰሉ ነገሮች ከማሰብ በጥብቅ ተቆጥቧል፣ ምክንያቱም የህይወት ክስተቶች በጭራሽ ይዘው የሚመጡትን ነገር ማናችንም አናውቅም። ብዙዏቻችን በህይወት ባህር ውስጥ የምንሰምጠው፤ እንደገበሬው ከኑሮ ጋር በቀላሉ መንሳፈፍን ስላለመድን ነው። በህይወታችን ወስጥ በእኛ ቁጥጥር ስር የሆኑ ነገሮች አሉ፤ ሌሎች ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ደግሞ እጅግ ብዙ ነገሮች ይኖራሉ።
💡በኑሮ ባህር ውስጥ መስመጥ የሚከሰተው ታዲያ፤ ከእኛ ቁጥጥር ወጪ የሆኑ ነገሮች ላይ ግትርነታችንን ለማሳየት ስንሞክር ነው። መለወጥ የማንችለውን ነገር በጉልበት ለመለወጥ ስንሞክር፤ የመዋኘት ጥበቡ ጠፍቶናል ማለት ነው። ህይወት ወደድንም ጠላንም ባልታሰቡ ፈተናዎች እና ስጦታዎች የተሞላች ነች። እንደ ገበሬው ረጋ ብለን ካልተንሳፈፍን በፍጹም ከለውጥ ጋር ተግባብተን ለመኖር አይቻለንም።
📍እናም ወዳጄ ዓለም እና የሰው ልጅ ተፈጥሮ በብዙ ስንክሳር የተሞሉ ናቸው። ባሳለፍከው ህይወት ብዙ ክስተቶች ታይተዋል። የሚያሳዝንም የሚያስደስቱም ሁኔታዎች የህይወት ገጾች ናቸው። ሁሉ ይመጣል፣ ሁሉም ይሄዳል። ያለፈውና የሚሄደውን በሰላም ሸኘው። አሁን ካለው ጋር በሰላም ተከባብረህና ተሳስበህ ኑር። ዘልዓለማዊ ክስተት የለም፣ ለውጥ እንጂ ። ከሁኔታዎች በላይ መሆንን እወቅበት። መረጋጋት መልካም ነው።
ውብ ምሽት❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanitybot