በኮሚሽኑ የሚያዙ ዕቅዶች ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ ጋር የተቀናጁ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ፦ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ
#####################
(ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም )
የጉምሩክ ኮሚሽን ዋናው መስሪያ ቤት ከፍተኛ አመራሮች ፣ አማካሪዎች ፣ ዳይሬክተሮች ፣ የቡድን አስተባባሪዎች እና በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችበ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ ክንውን ላይ ውይይት አድርገዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ፣ በ2017 በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በገቢ አሰባሰብ ፣ ኮንትሮባንድ እና ህገ ወጥ ንግድን በመከላከል እና በመቆጣጠር ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል::
በኮሚሽኑ የሚያዙ ዕቅዶችም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ ጋር የተቀናጁ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ኮሚሽነር ደበሌ አስረድተዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ አንዱ ምሰሶ ገቢን ማሳደግ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ ባለፉት ሶስት ወራትም 87 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 88 ነጥብ 2 ቢሊዮን ገቢ መሰብሰቡን አብራርተዋል።
ከኮንትሮባንድ መከላከል እና ከህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ስራዎችም 50 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ከህገወጦች ማዳን ተችሏል ብለዋል።
በቀጣይ ወራትም የኮሚሽኑን ተልዕኮ ማሳካት የሚችል በዕውቀቱ የዳበረ ፣ በስነምግባሩ የተመሰገነ ፣ በአመራር ብቃቱ የተመሰከረለት አመራር እና ባለሙያ ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ እና የስትራቴጂክ ፕላን እና ፕሮጀክት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አብዲሳ ዱፌራ የ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ ክንውን ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የኮሚሽኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች በበኩላቸው በ2017 በጀት ዓመት በ ኮሚሽኑ የተያዘውን 390 ቢሊዮን ብር የገቢ እቅድ ለማሳካት የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsCommission
#####################
(ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም )
የጉምሩክ ኮሚሽን ዋናው መስሪያ ቤት ከፍተኛ አመራሮች ፣ አማካሪዎች ፣ ዳይሬክተሮች ፣ የቡድን አስተባባሪዎች እና በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችበ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ ክንውን ላይ ውይይት አድርገዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ፣ በ2017 በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በገቢ አሰባሰብ ፣ ኮንትሮባንድ እና ህገ ወጥ ንግድን በመከላከል እና በመቆጣጠር ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል::
በኮሚሽኑ የሚያዙ ዕቅዶችም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ ጋር የተቀናጁ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ኮሚሽነር ደበሌ አስረድተዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ አንዱ ምሰሶ ገቢን ማሳደግ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ ባለፉት ሶስት ወራትም 87 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 88 ነጥብ 2 ቢሊዮን ገቢ መሰብሰቡን አብራርተዋል።
ከኮንትሮባንድ መከላከል እና ከህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ስራዎችም 50 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ከህገወጦች ማዳን ተችሏል ብለዋል።
በቀጣይ ወራትም የኮሚሽኑን ተልዕኮ ማሳካት የሚችል በዕውቀቱ የዳበረ ፣ በስነምግባሩ የተመሰገነ ፣ በአመራር ብቃቱ የተመሰከረለት አመራር እና ባለሙያ ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ እና የስትራቴጂክ ፕላን እና ፕሮጀክት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አብዲሳ ዱፌራ የ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ ክንውን ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የኮሚሽኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች በበኩላቸው በ2017 በጀት ዓመት በ ኮሚሽኑ የተያዘውን 390 ቢሊዮን ብር የገቢ እቅድ ለማሳካት የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsCommission