የመርስዔ ኀዘን ትዝታዬ መጽሐፍ ሲያልቅ ገና ጣልያን እራሱ አልገባም። እስካሁን ሳነባቸው የነበሩት ሰውዬ ድንገት እዛ ላይ ታሪካቸው ቆሞ ኤዲተሩ ልጃቸው ስለቀረው ሕይወታቸው እና ስለአሟሟታቸው የጻፈውን ሳነብ በቅርብ የማውቃቸው ሰው ድንገት የሞቱብኝ ያህል ነው ያስለቀሱኝ። ያረፉት ደርግ በገባ ባምስት ዓመቱ ነው። አስቡት ኢትዮጵያን በስንት ሞያቸው እና በየትልልቅ ድርጅቱ ሲያገለግሉ የነበሩ ሰዎች ሀገሪቷ እርስበርሷ ስትታመስ እያዩ ሲሞቱ። አሳዘኑኝ።
ሆነም ቀረም ልጃቸው የጻፈው ማሳረጊያ ምዕራፍ ዉስጥ ይሄን አይቼ ትንሽ አዝናንቶኝ ነው፡
በ1918 ዓ.ም. 14ቱ መጽሐፈ ቅዳሴ ታትሞ ኖሮ በ1942 የወጣውን ብላታ መርስዔ ኀዘን ናቸው አሻሽለው ያዘጋጁት (እነ ሊጦን፣ መስተብቍዕ እና ዘይነግሥ ተጨምረው) እና ከመጽሐፉ ሽያጭ የተገኘው ጥቅም ለማን ሄደ መሰላችሁ? «የኢጣልያ ጦር በ1929 ዓ.ም. ሕፅዋን (ጃንደረባ) ላደረጋቸው ድኾች ልጆች ለሚያድጉበት መንፈሳዊ ትምህርት ቤት እንዲሰጥ ተደርጎ ነበር» ይለናል መጽሐፉ። (ገጽ 225)
ጃንደረባ በግዕዙ ስልብ አገልጋይ ማለት ነው ፡) -- በየሚዲያው ለሚታየው አዲሱ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ትውልድ ሲባል ምን እያልን እንደሆንን ለማሳየትም ነው። (ያው አሁን ትርጉሙን ለውጠን ይሆናል ግን አመጣጡን ማወቃችን አይከፋም)
--
መርስዔ ኀዘን ያገለገሉባቸውን፣ የሠሩዋቸውን ሁሉ የሚጠቅሰውን ምዕራፍ ፎቶ አንስቼ ከሥር ልኬያለሁ።
አሰላም-አሌይኩም
ሆነም ቀረም ልጃቸው የጻፈው ማሳረጊያ ምዕራፍ ዉስጥ ይሄን አይቼ ትንሽ አዝናንቶኝ ነው፡
በ1918 ዓ.ም. 14ቱ መጽሐፈ ቅዳሴ ታትሞ ኖሮ በ1942 የወጣውን ብላታ መርስዔ ኀዘን ናቸው አሻሽለው ያዘጋጁት (እነ ሊጦን፣ መስተብቍዕ እና ዘይነግሥ ተጨምረው) እና ከመጽሐፉ ሽያጭ የተገኘው ጥቅም ለማን ሄደ መሰላችሁ? «የኢጣልያ ጦር በ1929 ዓ.ም. ሕፅዋን (ጃንደረባ) ላደረጋቸው ድኾች ልጆች ለሚያድጉበት መንፈሳዊ ትምህርት ቤት እንዲሰጥ ተደርጎ ነበር» ይለናል መጽሐፉ። (ገጽ 225)
ጃንደረባ በግዕዙ ስልብ አገልጋይ ማለት ነው ፡) -- በየሚዲያው ለሚታየው አዲሱ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ትውልድ ሲባል ምን እያልን እንደሆንን ለማሳየትም ነው። (ያው አሁን ትርጉሙን ለውጠን ይሆናል ግን አመጣጡን ማወቃችን አይከፋም)
--
መርስዔ ኀዘን ያገለገሉባቸውን፣ የሠሩዋቸውን ሁሉ የሚጠቅሰውን ምዕራፍ ፎቶ አንስቼ ከሥር ልኬያለሁ።
አሰላም-አሌይኩም