ስጋዋንም ያሳዩት ዘንድ ወደ መቃብሯ ባደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስላላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኋላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ሰጣቸው እነርሱም እስከ ነሐሴ አስራ ስድስት በተስፋ ኖሩ።
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት ዓመት ነው፤ በአባትና እናቷ ቤት ሶስት ዓመት ከሰባት ወር ፣ በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት ዓመት ፣ በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት ዓመት ከሶስት ወር ፣ ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት ዓመት ነው።
የእመቤታችን ፍቅሯ፤ በረከቷ ፤ አማላጅነቷ በእኛ በምናምን ክርስቲያኖች ላይ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርብን! የአስራት ሐገሯን ኢትዮጵያን ከፈተና ትጠብቅልን! አሜን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት ዓመት ነው፤ በአባትና እናቷ ቤት ሶስት ዓመት ከሰባት ወር ፣ በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት ዓመት ፣ በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት ዓመት ከሶስት ወር ፣ ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት ዓመት ነው።
የእመቤታችን ፍቅሯ፤ በረከቷ ፤ አማላጅነቷ በእኛ በምናምን ክርስቲያኖች ላይ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርብን! የአስራት ሐገሯን ኢትዮጵያን ከፈተና ትጠብቅልን! አሜን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox