ምርኩዜ🥺
ክፍል ፩
የሰው ልጅ እንደዚህ ሲንገዳገድ አይቼ አላውቅም አንድ ጊዜ ወደግራ ደግሞ ወደቀኝ ብቻ ምን አለፋችሁ ካሁን ካሁን ወደቀ እያለ ሰው ይመለከታል በሁለት ሊትር ሃይላንድ የተሞላ ድራፍት በቀኝ እጁ ይዟል በግራ እጁ ደግሞ ሲጋራውን ጨብጧል በብብቱ መሃል ደግሞ ጫቱን ይዞ እየተወላገደ ይራመዳል ያገኘውን ሰው ሁሉ እግዚአብሔርን አትከተሉት እንደኔ ያሰቃያችኋል እያለ ይመክራል መንገደኛው ሁሉ ወይ ጊዜ ሰው እንዴት በጠራራ ፀሃይ ይሰክራል እያለ ይመፃደቅበታል ድሮ የሚያውቁት ደግሞ አይ እንደዛ እንዳልተከበርክ በሀይላንድ ፀበሉን በፌስታል እምነቱን በክብሪት ጧፉን እንዳለኮስክ እንዲህ ተበላሽተህ ቀረህ እያሉ ከንፈራቸውን መምጠጥ ከጀመሩለት ሰነባብተዋል የሰፈሩ ህፃናት እንኳን ሳይቀሩ ባዶ እጁን ሲያዩት እንደ አበደ ሰው ነው የሚቆጥሩት ደግነቱ እሱ ባዶውን አይሄድም እንጂ ሁልጊዜ አቋራጭ መንገድ እያለ ወደ ቤቱ የሚገባው ዙሪያ ጥምጥም ሄዶ ነው እንድ ቀን አንድ ሰው ለምን በሚካኤል በኩል አድርገህ በአቋራጭ አትሄድም ሲለው እኔ ሚካኤል በተጠራበት በኩል ማለፍ ስለማልፈልግ ነው እንጂ ዙሪያ ጥምጥም መንገድ ፈልጌ አይደለም ግን እስከለተ ሞቴ በሚካኤል በር አላልፍም አለው ከዚያ ወዲህ ማንም ሰው ጠይቆት አያውቅም ለሰፈሩ አዲስ የሆኑ መጤ ሰዎች አይ ይሄ ሰው በቃ ሁልጊዜ መጠጣት መስከር ነው አይደል የሚያውቀው ሰውስ ቆይ ለምንድን ነው ብር የሚሰጠው አንዳንድ ሰዎች የጠቀሙት እየመሰላቸው በነፍሱ ይጫወቱበታል ወይ ዘመን እያሉ ይማረራሉ ሁልጊዜ ስለሱ መጥፎ ሲወራ የሚያቀጠቅጣቸው አንድ አባት እኔ ምላችሁ ልጆቼ ዛሬ ቅዱስን ያየው ሰው አለ እንዴ አለ አንዷ ቀልጠፍ ብላ ውይ ጋሼ ደግሞ አሁን ቅዱስ እዚህ ይኖራል ብለው ነው ያው እዛው መጠጥ ቤት እየተጋተ ይሆናል እንጂ…
ይቀጥላል
✍ ብርሃኑ ባውቄ
ክፍል ፩
የሰው ልጅ እንደዚህ ሲንገዳገድ አይቼ አላውቅም አንድ ጊዜ ወደግራ ደግሞ ወደቀኝ ብቻ ምን አለፋችሁ ካሁን ካሁን ወደቀ እያለ ሰው ይመለከታል በሁለት ሊትር ሃይላንድ የተሞላ ድራፍት በቀኝ እጁ ይዟል በግራ እጁ ደግሞ ሲጋራውን ጨብጧል በብብቱ መሃል ደግሞ ጫቱን ይዞ እየተወላገደ ይራመዳል ያገኘውን ሰው ሁሉ እግዚአብሔርን አትከተሉት እንደኔ ያሰቃያችኋል እያለ ይመክራል መንገደኛው ሁሉ ወይ ጊዜ ሰው እንዴት በጠራራ ፀሃይ ይሰክራል እያለ ይመፃደቅበታል ድሮ የሚያውቁት ደግሞ አይ እንደዛ እንዳልተከበርክ በሀይላንድ ፀበሉን በፌስታል እምነቱን በክብሪት ጧፉን እንዳለኮስክ እንዲህ ተበላሽተህ ቀረህ እያሉ ከንፈራቸውን መምጠጥ ከጀመሩለት ሰነባብተዋል የሰፈሩ ህፃናት እንኳን ሳይቀሩ ባዶ እጁን ሲያዩት እንደ አበደ ሰው ነው የሚቆጥሩት ደግነቱ እሱ ባዶውን አይሄድም እንጂ ሁልጊዜ አቋራጭ መንገድ እያለ ወደ ቤቱ የሚገባው ዙሪያ ጥምጥም ሄዶ ነው እንድ ቀን አንድ ሰው ለምን በሚካኤል በኩል አድርገህ በአቋራጭ አትሄድም ሲለው እኔ ሚካኤል በተጠራበት በኩል ማለፍ ስለማልፈልግ ነው እንጂ ዙሪያ ጥምጥም መንገድ ፈልጌ አይደለም ግን እስከለተ ሞቴ በሚካኤል በር አላልፍም አለው ከዚያ ወዲህ ማንም ሰው ጠይቆት አያውቅም ለሰፈሩ አዲስ የሆኑ መጤ ሰዎች አይ ይሄ ሰው በቃ ሁልጊዜ መጠጣት መስከር ነው አይደል የሚያውቀው ሰውስ ቆይ ለምንድን ነው ብር የሚሰጠው አንዳንድ ሰዎች የጠቀሙት እየመሰላቸው በነፍሱ ይጫወቱበታል ወይ ዘመን እያሉ ይማረራሉ ሁልጊዜ ስለሱ መጥፎ ሲወራ የሚያቀጠቅጣቸው አንድ አባት እኔ ምላችሁ ልጆቼ ዛሬ ቅዱስን ያየው ሰው አለ እንዴ አለ አንዷ ቀልጠፍ ብላ ውይ ጋሼ ደግሞ አሁን ቅዱስ እዚህ ይኖራል ብለው ነው ያው እዛው መጠጥ ቤት እየተጋተ ይሆናል እንጂ…
ይቀጥላል
✍ ብርሃኑ ባውቄ