#ነገ_በጸሎተ_ሐሙስ_በቅዱስ_ቁርባን_እንቀደስ!
የቆረባችሁም ያልቆረባችሁም የነገው እለት እንዳያመልጣችሁ!
በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
ሼር በማድረግ ለሁሉም አዳርሱ!
ተወዳጆች ሆይ ነገ ጸሎተ ሐሙስ ነው። ይህ ቀን ብዙ ስያሜ ቢኖረውም አንዱ ስያሜው የምስጢር ቀን ይባላል። ምክንያቱም በዚህ እለት ጌታችን የቅዱስ ቁርባንን ምስጢር ለቅዱሳን ሐዋርያት ያካፈለበት፣ ሥርዓተ ቅዱስ ቁርባንን የመሠረተበት ታላቅ ቀን ነው።
ስለዚህ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል የምትኖሩ ነገ በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባን ተቀበሉ። ንስሐ ገብታችሁ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ያሰባችሁም ከንስሐ አባታችሁ ጋር ተመካክራችሁ ነገ በጸሎተ ሐሙስ እለት ቅዱስ ቁርባን ተቀበሉ።
ቅዱስ ቁርባን ያልተቀበላችሁ ደግሞ፣ ጌታችን ሥርዓተ ቅዱስ ቁርባንን በመሠረተበት፣ ለቅዱሳን ሐዋርያት ምስጢርን ባካፈለበት በዚህ እለት ተገኝታችሁ አስቀድሳችሁ በቅዳሴው ተቀደሱ።
በጸሎተ ሐሙስ እለት ጌታች "እንኳችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፣ ይህ ደሜ ነው ጠጡ" ብሎ እራሱን ብሉኝ ጠጡኝ ብሎ ሰጠን።
የሚገርመው ጌታችን በማቴ 26፥27 ላይ "ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የሐዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው" በማለት ቅዱስ ሥጋውን እና ክቡር ደሙን ለሁላችን ሰጠን።
እንድ ሰው የሚወደውን ሰው በእንግድነት ቤቱ ቢጠራው የሚወደውን ምግብ እና መጠጥ ሊጋብዘው ይችላል። ጌታችን ግን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንድንመጣ ሲጋብዘን የሚሰጠን እራሱን ነው። የሚጋብዘን ቅዱስ ሥጋውንና ክብር ደሙን ነው።
ሰው ሰውን ቢጋብዝ የራሱን ነገር ነው የሚሰጠው። ጌታችን ግን እራሱን ነው የሰጠን። የሚደንቀው ደግሞ "ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ" አለ። ኃጥአን ፃድቃን ሳይል፣ የበቃ ያልበቃ ሳይል፣ ድንግል ዘማዊ ሳይል፣ ሕፃን ወጣት ጎልማሳ አዛውንት ሳይል፣ ግን ንስሐ የገባውን ሁሉ ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ አለ። አንዴት መታደል ነው!
ቅዱስ ቁርባንን በየትኛውም እለት ልትቀበሉ ትችላላችሁ ግን በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ከጌታ እጅ መቀበል ነው።
በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባንን በማስታወስ መቀበል የቅዱስ ቁርባንን በዓል አስቦ መቀበል ነው። ጸሎተ ሐሙስ ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታችን ቅዱስ ቁርባንን የሰጠን እለት ስለሆነ በዚህ እለት ቅዱስ ቁርባንን መቀበል የቅዱስ ቁርባንን የምሥረታ በዓል አስቦ መቀበል ነው።
በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባን መቀበል እኛ ቆራቢዎች እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ነን፤ ቀድሰው የሚያቆርቡን ክቡራን ካህናት ደግሞ እንደ ጌታችን ናቸው።
በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባን መቀበል፣ በምሥጢር እለት ምስጢር መሳተፍ ነው።
እስኪ አስቡት! በጸሎተ ሐሙስ እናንተ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት፣ ክቡራን ካህናት እንደ ጌታችን ሆነን በጸሎተ ሐሙስ በቅዳሴ ስንገኝ! ግሩም ነው!
ስለዚህ በቅዱስ ቁርባን ሕይወት ያላችሁም፣ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል በንስሐ የተዘጋጃችሁም፣ ይህቺ የምስጢር እለት አታምልጣችሁ! ደግሜ እናገራለሁ ለመቁረብ አንዳች ምክንያት እስካልከለከላችሁ ድረስ የቻላችሁ ቅዱስ ቁርባን ተቀበሉ።
እራሱ ጌታችን "ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ" ብሎ አዞናል። በነገራችን ላይ ቅዱስ ቁርባን መቀበል የጌታችን ትዕዛዝ ነው። በቃ አዞናል። በንስሐ ሆኖ ቅዱስ ቁርባን መቀበል ለጌታ መታዘዝ ነው። ቅዱስ ቁርባን አለመቀበል ለጌታ አለመታዘዝ ነው።
በእርግጥ እንደ ኃጢአታችን ላይቻለን ላይሆንልን ይችላል። በንስሐ ሆነን እንደ ቸርነቱ ይቻለናል። ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል እኔ አላዛቹ፣ መምህራን እና ካህናት አያዛቹ። እኛ ማስታወስ ብቻ ነው። ተቀበሉ ያላችሁ የቅዱስ ቁርባኑ ባለቤት ጌታችን ነው። ባለቤቱ ካዘዘ ደግሞ በንስሐ እና በትህትና ሆነን መቀበል ነው።
ቅዱስ ቁርባን የሚቀበል ሰው ዘላለማዊ ሕይወት፣ ጸጋ መለኮት፣ የእግዚአብሔር በረከት፣ የኃጢአት ሥርየት እና መንፈሳዊ ኃይል ወዘተ ይኖረዋል። ስለዚህ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል እነዚህን ጸጋዎች እንቀበል።
እንዲሁም ቅዱስ ቁርባን ያልተቀበላችሁም በምስጢር እለት ተገኝታችሁ ጌታችንን "ከዚህ ምስጢር እንድካፈል አብቃኝ" ብላችሁ በቅዳሴው ተማጸኑ።
በያላንብ የጌታችን ቸርነት የወለላይቱ እመቤት ጸሎት አይለየን!
ሚያዝያ 8-8-17 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የቆረባችሁም ያልቆረባችሁም የነገው እለት እንዳያመልጣችሁ!
በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
ሼር በማድረግ ለሁሉም አዳርሱ!
ተወዳጆች ሆይ ነገ ጸሎተ ሐሙስ ነው። ይህ ቀን ብዙ ስያሜ ቢኖረውም አንዱ ስያሜው የምስጢር ቀን ይባላል። ምክንያቱም በዚህ እለት ጌታችን የቅዱስ ቁርባንን ምስጢር ለቅዱሳን ሐዋርያት ያካፈለበት፣ ሥርዓተ ቅዱስ ቁርባንን የመሠረተበት ታላቅ ቀን ነው።
ስለዚህ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል የምትኖሩ ነገ በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባን ተቀበሉ። ንስሐ ገብታችሁ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ያሰባችሁም ከንስሐ አባታችሁ ጋር ተመካክራችሁ ነገ በጸሎተ ሐሙስ እለት ቅዱስ ቁርባን ተቀበሉ።
ቅዱስ ቁርባን ያልተቀበላችሁ ደግሞ፣ ጌታችን ሥርዓተ ቅዱስ ቁርባንን በመሠረተበት፣ ለቅዱሳን ሐዋርያት ምስጢርን ባካፈለበት በዚህ እለት ተገኝታችሁ አስቀድሳችሁ በቅዳሴው ተቀደሱ።
በጸሎተ ሐሙስ እለት ጌታች "እንኳችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፣ ይህ ደሜ ነው ጠጡ" ብሎ እራሱን ብሉኝ ጠጡኝ ብሎ ሰጠን።
የሚገርመው ጌታችን በማቴ 26፥27 ላይ "ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የሐዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው" በማለት ቅዱስ ሥጋውን እና ክቡር ደሙን ለሁላችን ሰጠን።
እንድ ሰው የሚወደውን ሰው በእንግድነት ቤቱ ቢጠራው የሚወደውን ምግብ እና መጠጥ ሊጋብዘው ይችላል። ጌታችን ግን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንድንመጣ ሲጋብዘን የሚሰጠን እራሱን ነው። የሚጋብዘን ቅዱስ ሥጋውንና ክብር ደሙን ነው።
ሰው ሰውን ቢጋብዝ የራሱን ነገር ነው የሚሰጠው። ጌታችን ግን እራሱን ነው የሰጠን። የሚደንቀው ደግሞ "ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ" አለ። ኃጥአን ፃድቃን ሳይል፣ የበቃ ያልበቃ ሳይል፣ ድንግል ዘማዊ ሳይል፣ ሕፃን ወጣት ጎልማሳ አዛውንት ሳይል፣ ግን ንስሐ የገባውን ሁሉ ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ አለ። አንዴት መታደል ነው!
ቅዱስ ቁርባንን በየትኛውም እለት ልትቀበሉ ትችላላችሁ ግን በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ከጌታ እጅ መቀበል ነው።
በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባንን በማስታወስ መቀበል የቅዱስ ቁርባንን በዓል አስቦ መቀበል ነው። ጸሎተ ሐሙስ ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታችን ቅዱስ ቁርባንን የሰጠን እለት ስለሆነ በዚህ እለት ቅዱስ ቁርባንን መቀበል የቅዱስ ቁርባንን የምሥረታ በዓል አስቦ መቀበል ነው።
በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባን መቀበል እኛ ቆራቢዎች እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ነን፤ ቀድሰው የሚያቆርቡን ክቡራን ካህናት ደግሞ እንደ ጌታችን ናቸው።
በጸሎተ ሐሙስ ቅዱስ ቁርባን መቀበል፣ በምሥጢር እለት ምስጢር መሳተፍ ነው።
እስኪ አስቡት! በጸሎተ ሐሙስ እናንተ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት፣ ክቡራን ካህናት እንደ ጌታችን ሆነን በጸሎተ ሐሙስ በቅዳሴ ስንገኝ! ግሩም ነው!
ስለዚህ በቅዱስ ቁርባን ሕይወት ያላችሁም፣ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል በንስሐ የተዘጋጃችሁም፣ ይህቺ የምስጢር እለት አታምልጣችሁ! ደግሜ እናገራለሁ ለመቁረብ አንዳች ምክንያት እስካልከለከላችሁ ድረስ የቻላችሁ ቅዱስ ቁርባን ተቀበሉ።
እራሱ ጌታችን "ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ" ብሎ አዞናል። በነገራችን ላይ ቅዱስ ቁርባን መቀበል የጌታችን ትዕዛዝ ነው። በቃ አዞናል። በንስሐ ሆኖ ቅዱስ ቁርባን መቀበል ለጌታ መታዘዝ ነው። ቅዱስ ቁርባን አለመቀበል ለጌታ አለመታዘዝ ነው።
በእርግጥ እንደ ኃጢአታችን ላይቻለን ላይሆንልን ይችላል። በንስሐ ሆነን እንደ ቸርነቱ ይቻለናል። ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል እኔ አላዛቹ፣ መምህራን እና ካህናት አያዛቹ። እኛ ማስታወስ ብቻ ነው። ተቀበሉ ያላችሁ የቅዱስ ቁርባኑ ባለቤት ጌታችን ነው። ባለቤቱ ካዘዘ ደግሞ በንስሐ እና በትህትና ሆነን መቀበል ነው።
ቅዱስ ቁርባን የሚቀበል ሰው ዘላለማዊ ሕይወት፣ ጸጋ መለኮት፣ የእግዚአብሔር በረከት፣ የኃጢአት ሥርየት እና መንፈሳዊ ኃይል ወዘተ ይኖረዋል። ስለዚህ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል እነዚህን ጸጋዎች እንቀበል።
እንዲሁም ቅዱስ ቁርባን ያልተቀበላችሁም በምስጢር እለት ተገኝታችሁ ጌታችንን "ከዚህ ምስጢር እንድካፈል አብቃኝ" ብላችሁ በቅዳሴው ተማጸኑ።
በያላንብ የጌታችን ቸርነት የወለላይቱ እመቤት ጸሎት አይለየን!
ሚያዝያ 8-8-17 ዓ.ም
አዲስ አበባ