ፆታ የቀየሩ ወታደሮችን ከአሜሪካ መከላከያ የሚያግድ ኘሬዝደንታዊ ትዕዛዝ ትራምኘ ዛሬ ይፈርማሉ
-------
ፆታ የለወጡ ወታደሮች ከአሜሪካ ሰራዊት አባልነት እንዲታገዱ ዶናልድ ትራምኘ ኘሬዝደንታዊ ውሳኔ ዛሬ ያሳልፋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።
በአሜሪካ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ብዝሃነትን ማስተናገድ በሚል ማዕቀፍ ፆታ የቀየሩ እና የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን የፈፀሙ ግለሰቦችን በሰራዊት አባልነት እንዲሆኑ ሲደረግ ነበር።
ኘሬዝደንት ትራምኘ በምርጫ ውድድር ወቅት ከፆታ ጋር በተያያዘ ከተፈጥሮአዊ መንገድ ውጭ አካሄዶችን በፅኑ ሲኮንኑ እና ቢመረጡ መንግስታቸው እርምጃዎችን እንደሚወስድ ሲገልፁ እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ ኘሬዝደንቱ ሶስት ኘሬዝደንታዊ ትዕዛዞችን እንደሚፈርሙ የሚጠበቅ ሲሆን ከነዚህ አንዱ ፆታ የቀየሩ በአሜሪካ ሰራዊት ውስጥ እንዳያገለግሉ ክልከላ የሚጥለው ውሳኔ ዋንኛው እንደሆነ ታውቋል።
-------
ፆታ የለወጡ ወታደሮች ከአሜሪካ ሰራዊት አባልነት እንዲታገዱ ዶናልድ ትራምኘ ኘሬዝደንታዊ ውሳኔ ዛሬ ያሳልፋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።
በአሜሪካ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ብዝሃነትን ማስተናገድ በሚል ማዕቀፍ ፆታ የቀየሩ እና የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን የፈፀሙ ግለሰቦችን በሰራዊት አባልነት እንዲሆኑ ሲደረግ ነበር።
ኘሬዝደንት ትራምኘ በምርጫ ውድድር ወቅት ከፆታ ጋር በተያያዘ ከተፈጥሮአዊ መንገድ ውጭ አካሄዶችን በፅኑ ሲኮንኑ እና ቢመረጡ መንግስታቸው እርምጃዎችን እንደሚወስድ ሲገልፁ እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ ኘሬዝደንቱ ሶስት ኘሬዝደንታዊ ትዕዛዞችን እንደሚፈርሙ የሚጠበቅ ሲሆን ከነዚህ አንዱ ፆታ የቀየሩ በአሜሪካ ሰራዊት ውስጥ እንዳያገለግሉ ክልከላ የሚጥለው ውሳኔ ዋንኛው እንደሆነ ታውቋል።