ትራምኘ ሶማሊያ ውስጥ ይገኛሉ በተባሉ የአይሲስ አመራሮች ላይ የአየር ጥቃት እንዲፈፀም ትዕዛዝ ሰጡ
------
ኘሬዝደንት ዶናልድ ትራምኘ የአሜሪካ አየር ሃይል በሶማሊያ በሚገኙ የአይሲስ ሽብር ቡድን አባላት ላይ የአየር ጥቃት እንዲፈፀም ዛሬ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
ኘሬዝደንቱ በኤክስ ገፃቸው ላይ እንዳስታወቁት በሶማሊያ በመሸጉ የአይሲስ ሽብር ቡድን ከፍተኛ አመራርን ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃት ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ ብለዋል።
ኘሬዝደንት ትራምኘ የጥቃቱ ኢላማ የትኛው አመራር እንደሆነ በስም አልጠቀሱም።
ኘሬዝደንቱ የሽብር ቡድኑ መሪዎች በሶማሊያ ዋሻዎች ውስጥ ተሸሽገው እንደሚገኙ የተጠቀሱ ሲሆን ፥ ከአጋሮቻችን ጋር በመሆን እናጠፋቸዋለን ብለዋል።
------
ኘሬዝደንት ዶናልድ ትራምኘ የአሜሪካ አየር ሃይል በሶማሊያ በሚገኙ የአይሲስ ሽብር ቡድን አባላት ላይ የአየር ጥቃት እንዲፈፀም ዛሬ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
ኘሬዝደንቱ በኤክስ ገፃቸው ላይ እንዳስታወቁት በሶማሊያ በመሸጉ የአይሲስ ሽብር ቡድን ከፍተኛ አመራርን ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃት ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ ብለዋል።
ኘሬዝደንት ትራምኘ የጥቃቱ ኢላማ የትኛው አመራር እንደሆነ በስም አልጠቀሱም።
ኘሬዝደንቱ የሽብር ቡድኑ መሪዎች በሶማሊያ ዋሻዎች ውስጥ ተሸሽገው እንደሚገኙ የተጠቀሱ ሲሆን ፥ ከአጋሮቻችን ጋር በመሆን እናጠፋቸዋለን ብለዋል።