ትረምፕ የካናዳን እና የሜክሲኮን መሪዎችን ሊነጋገሩ ነው
-----------
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከሁለቱ ጎረቤቶቻቸው ካናዳ እና ሜክሲኮ፣ እንዲሁም ከቻይና በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ ከጣሉ እና በምላሹ ሁለቱ አገሮች በዩናይትድ ስቴትስ ላይ የአጻፋ ቀረጥ መጣላቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ ከመሪዎቹ ጋር ለመነጋገር ማቀዳቸውን አመለከቱ።
ትረምፕ በመጀመሪያው የሥልጣን ዘመናቸው ከካናዳ እና ሜክሲኮ ጋር ተደራድረው ‘ነጻ-የንግግድ ስምምነት’ ተግባራዊ ቢያደርጉም፤ ከነገ ማክሰኞ አንስቶ ተፈጻሚ የሚሆን አዲስ የሃያ አምስት በመቶ ቀረጥ ሲጥሉባቸው፤ በቻይና ላይ ደግሞ ቀደም ሲል ከተደነገገው በተጨማሪ የአሥር በመቶ ቀረጥ ጥለዋል።
ትረምፕ ሕገ-ወጥ ፍልሰትን ለማስቆም እና ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ለብዙዎች ህልፈት ምክኒያት የሆነው ‘ፌንቲኔል’ የተባለ አደገኛ መድሃኒት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ለመከላከል በቂ ጥረት አላደረጉም’ ሲሉ ሦስቱን ሃገራት ከሰዋል።
-----------
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከሁለቱ ጎረቤቶቻቸው ካናዳ እና ሜክሲኮ፣ እንዲሁም ከቻይና በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ ከጣሉ እና በምላሹ ሁለቱ አገሮች በዩናይትድ ስቴትስ ላይ የአጻፋ ቀረጥ መጣላቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ ከመሪዎቹ ጋር ለመነጋገር ማቀዳቸውን አመለከቱ።
ትረምፕ በመጀመሪያው የሥልጣን ዘመናቸው ከካናዳ እና ሜክሲኮ ጋር ተደራድረው ‘ነጻ-የንግግድ ስምምነት’ ተግባራዊ ቢያደርጉም፤ ከነገ ማክሰኞ አንስቶ ተፈጻሚ የሚሆን አዲስ የሃያ አምስት በመቶ ቀረጥ ሲጥሉባቸው፤ በቻይና ላይ ደግሞ ቀደም ሲል ከተደነገገው በተጨማሪ የአሥር በመቶ ቀረጥ ጥለዋል።
ትረምፕ ሕገ-ወጥ ፍልሰትን ለማስቆም እና ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ለብዙዎች ህልፈት ምክኒያት የሆነው ‘ፌንቲኔል’ የተባለ አደገኛ መድሃኒት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ለመከላከል በቂ ጥረት አላደረጉም’ ሲሉ ሦስቱን ሃገራት ከሰዋል።