ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሀገር ዉስጥ ገንዘብ ለመገበያየት መስማማታቸው ተሰማ
----
ሩሲያ ኢትዮጵያን ጨምሮ ናይጄሪያን እና ቱኒዚያን በሰሜን እስያዊቷ ሀገር ውስጥ በገንዘብ ለመገበያየት ከተፈቀደላቸው አገሮች ዝርዝር ውስጥ አካታለች።
ሀገራቱ ከሩሲያ ጋር በሚፈጽሙት ግብይት የሚያጋጥማቸውን የውጭ ምንዛሪ እጥረት ለመቅረፍ እና የተሻለ የንግድ ግንኙነት ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተገልጿል ።
የዩክሬኑን ጦርነት ተከትሎ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ከዶላር ውጭ የሆነ ግብይት ለመፈጸም ስምምነቶችን እያደረገች የምትገኝው ሞስኮ ተጨማሪ ሶስት የአፍሪካ ሀገራትን የተቀበለችው ከሰሞኑ ነዉ።
ስፑትኒክ እንደዘገበዉ የሩሲያ መንግስት እንደገለጸው ይህ መመሪያ የሩሲያ ኢኮኖሚ በመገበያያ ገንዘብ የሚከፈለዉን ፍላጎት ለማሟላት እንዲረዳ እንዲሁም የወዳጅ እና ገለልተኛ መንግስታትን የብሔራዊ ገንዘቦችን በቀጥታ ለመለዋወጥ የሚያስችለውን ስርዓት ውጤታማነት እንደሚያረጋግጥ አስረድተዋል ።
ከሁለት አመት በፊት በዚህ ዝርዝር ውስጥ የነበሩ አገሮች ቁጥር 30 የነበረ ሲሆን አሁን ግን ከሩሲያ ጋር በሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመገበያየት ስምምነት ላይ የደረሱ ሀገራት ቁጥር 40 ደርሷል ይላል ካፒታል ጋዜጣ ያዘጣው መረጃ ፡፡
----
ሩሲያ ኢትዮጵያን ጨምሮ ናይጄሪያን እና ቱኒዚያን በሰሜን እስያዊቷ ሀገር ውስጥ በገንዘብ ለመገበያየት ከተፈቀደላቸው አገሮች ዝርዝር ውስጥ አካታለች።
ሀገራቱ ከሩሲያ ጋር በሚፈጽሙት ግብይት የሚያጋጥማቸውን የውጭ ምንዛሪ እጥረት ለመቅረፍ እና የተሻለ የንግድ ግንኙነት ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተገልጿል ።
የዩክሬኑን ጦርነት ተከትሎ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ከዶላር ውጭ የሆነ ግብይት ለመፈጸም ስምምነቶችን እያደረገች የምትገኝው ሞስኮ ተጨማሪ ሶስት የአፍሪካ ሀገራትን የተቀበለችው ከሰሞኑ ነዉ።
ስፑትኒክ እንደዘገበዉ የሩሲያ መንግስት እንደገለጸው ይህ መመሪያ የሩሲያ ኢኮኖሚ በመገበያያ ገንዘብ የሚከፈለዉን ፍላጎት ለማሟላት እንዲረዳ እንዲሁም የወዳጅ እና ገለልተኛ መንግስታትን የብሔራዊ ገንዘቦችን በቀጥታ ለመለዋወጥ የሚያስችለውን ስርዓት ውጤታማነት እንደሚያረጋግጥ አስረድተዋል ።
ከሁለት አመት በፊት በዚህ ዝርዝር ውስጥ የነበሩ አገሮች ቁጥር 30 የነበረ ሲሆን አሁን ግን ከሩሲያ ጋር በሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመገበያየት ስምምነት ላይ የደረሱ ሀገራት ቁጥር 40 ደርሷል ይላል ካፒታል ጋዜጣ ያዘጣው መረጃ ፡፡