ትራምኘ የመጀመሪያውን መሪ በኋይት ሃውስ ዛሬ ተቀበሉ
--------
ትረምፕ በጋዛው የተኩስ አቁም ስምምነት ሂደት ዙሪያ ለመነጋገር ዛሬ ኔታንያሁን በዋይት ሀውስ ተቀብለው ያነጋግራሉ
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁን ዛሬ ማክሰኞ በዋይት ሀውስ ተቀብለው ያነጋግራሉ።
የሁለቱ መሪዎች ንግግር የመጣው ጋዛ ውስጥ የቀሩት ታጋቾች በሙሉ መለቀቅን፣ የውጊያው ሙሉ በሙሉ በቋሚነት መቆምን እና የእስራኤልን ኃይሎች ከጋዛ ተጠቃሎ መውጣት ጨምሮ በእስራኤል እና በሃማስ መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ከወሳኝ ምዕራፍ በደረሰበት ወቅት ነው።
እስራኤል እና ሃማስ በደረሱት ስምምነት መሰረት የውላቸውን ሁለተኛው ዙር አፈጻጸም ተግባራዊ ለማድረግ ከአራት ሳምንታት ያነሰ ጊዜ ነው የቀረው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ “ሰላሙ ስለመያዙ የምሰጠው ዋስትና የለም” ሲሉ ትረምፕ ሰኞ ዕለት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
--------
ትረምፕ በጋዛው የተኩስ አቁም ስምምነት ሂደት ዙሪያ ለመነጋገር ዛሬ ኔታንያሁን በዋይት ሀውስ ተቀብለው ያነጋግራሉ
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁን ዛሬ ማክሰኞ በዋይት ሀውስ ተቀብለው ያነጋግራሉ።
የሁለቱ መሪዎች ንግግር የመጣው ጋዛ ውስጥ የቀሩት ታጋቾች በሙሉ መለቀቅን፣ የውጊያው ሙሉ በሙሉ በቋሚነት መቆምን እና የእስራኤልን ኃይሎች ከጋዛ ተጠቃሎ መውጣት ጨምሮ በእስራኤል እና በሃማስ መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ከወሳኝ ምዕራፍ በደረሰበት ወቅት ነው።
እስራኤል እና ሃማስ በደረሱት ስምምነት መሰረት የውላቸውን ሁለተኛው ዙር አፈጻጸም ተግባራዊ ለማድረግ ከአራት ሳምንታት ያነሰ ጊዜ ነው የቀረው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ “ሰላሙ ስለመያዙ የምሰጠው ዋስትና የለም” ሲሉ ትረምፕ ሰኞ ዕለት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።