የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽ በግማሽ ዓመቱ ከእቅድ በላይ 2.6 ቢሊየን ብር ገቢ ማገኘቱን አስታወቀ
----------------
ኮርፖሬሽኑ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የተቋሙን ስኬት ቀጣይነት ያረጋገጡ ስኬታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ባካሄደው የአፈጻጸም ግምገማ አረጋግጧል፡፡
በግማሽ ዓመቱ 2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት የታቀደ ቢሆንም ከ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡
ገቢውም ከኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ ኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ ገቢ የሚያገኝባቸው ቤቶች በመልሶ ማልማት አካል በመሆናቸው የተቋሙ ገቢ ያሽቆለቁላል የሚለውን ስጋት የቀረፈ የገቢ እድገት ነው፡፡
ኮርፖሬሽኑ በመልሶ ማልማት ያጣውን ገቢ ለማካካስ በፍጥነት ተጨማሪ ሱቆችን በመስራት እና ሌሎች የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በማከናወን በግማሽ ዓመቱ ከፍተኛ የገቢ እድገትና ተጨማሪ ከ 1 በሊየን ብር በላይ አሴት እንዲፈጠር ያስቻለ ውጤታማ ሥራ መሰራቱም ተጠቁሟል፡፡
በገቢ እድገትና ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት ከመፍጠር አኳያ የተሰራው ሥራ የኮርፖሬሽኑን የለውጥ ጉዞ አስተማማኝ እንዲሆን እያደረገ መሆኑን ነው የተገመገመው፡፡
ኮርፖሬሽኑ በራሱ አቅም ግዙፍ የቤት ግንባታ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት የሚያስችል አቅም መፍጠር መቻሉም በጥንካሬ ተግምግሟል፡፡
ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ንጹህ የኦዲት አስተያያት ማግኘት መቻሉም በግምገማው ተነሰቷል፡፡ ይህም ዘመናዊ የፋይናንስ ሥርዓት ዝርጋታው የደረሰበትን ደረጃ የሚያሳይ ነው፡፡
ወጪ ቆጣቢ አካሄድን ተግባራዊ በማደረግ ረገድና የገቢ አማራጮችን ከማስፋት አንጻርም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸው ነው በግምገማው የተመለካተው፡፡
በግማሽ ዓመቱ የምስራቅ አጠቃላይ፣ ኮከበ ጽብሃና ግዙፍ የግብዓት ማምረቻ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት መብቃት መቻሉ የኮርፖሬሽኑ በላቀ አፈጻጸም ላይ እንዳለ የሚያሳይ መሆኑን ተገምግሟል።
በዚህ ስኬትን ለማጽትና ለማስቀጠል በተሰሩ አንኳር ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገውን ግምገማ የመሩት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር ረሻድ ከማል ተጨማሪ የአፈጻጸም አቅጣጫም ሰጥተዋል፡፡
አገራዊ ፋይዳው የላቀ ትእምርት ባለው የኮሪደር ልማት፣ ኮርፖሬሽኑ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ በተጠናከረ ሁኔታ ለማስቀጠል የሚያስችል አቅጣጫም ተቀምጧል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ይዞት የመጣውን እድል በአግባቡ በመጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ውይይትና የአፈጻጸም አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ገንብቶ ለማስረከብ ውል የገባበቸውን ግዙፍ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ግንባታቸውን በጊዜ ገንብቶ ለማጠናቀቅ በልዩ ሁኔታ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡
የበርካታ ተቋማትን የአብረን እንስራ ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል ያልተቋረጠ የአቅም ግንባታ ሥራ መሰራት እንደለበት በግምገማው አጽንኦት ተሰጥቶበታል፡፡
----------------
ኮርፖሬሽኑ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የተቋሙን ስኬት ቀጣይነት ያረጋገጡ ስኬታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ባካሄደው የአፈጻጸም ግምገማ አረጋግጧል፡፡
በግማሽ ዓመቱ 2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት የታቀደ ቢሆንም ከ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡
ገቢውም ከኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ ኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ ገቢ የሚያገኝባቸው ቤቶች በመልሶ ማልማት አካል በመሆናቸው የተቋሙ ገቢ ያሽቆለቁላል የሚለውን ስጋት የቀረፈ የገቢ እድገት ነው፡፡
ኮርፖሬሽኑ በመልሶ ማልማት ያጣውን ገቢ ለማካካስ በፍጥነት ተጨማሪ ሱቆችን በመስራት እና ሌሎች የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በማከናወን በግማሽ ዓመቱ ከፍተኛ የገቢ እድገትና ተጨማሪ ከ 1 በሊየን ብር በላይ አሴት እንዲፈጠር ያስቻለ ውጤታማ ሥራ መሰራቱም ተጠቁሟል፡፡
በገቢ እድገትና ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት ከመፍጠር አኳያ የተሰራው ሥራ የኮርፖሬሽኑን የለውጥ ጉዞ አስተማማኝ እንዲሆን እያደረገ መሆኑን ነው የተገመገመው፡፡
ኮርፖሬሽኑ በራሱ አቅም ግዙፍ የቤት ግንባታ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት የሚያስችል አቅም መፍጠር መቻሉም በጥንካሬ ተግምግሟል፡፡
ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ንጹህ የኦዲት አስተያያት ማግኘት መቻሉም በግምገማው ተነሰቷል፡፡ ይህም ዘመናዊ የፋይናንስ ሥርዓት ዝርጋታው የደረሰበትን ደረጃ የሚያሳይ ነው፡፡
ወጪ ቆጣቢ አካሄድን ተግባራዊ በማደረግ ረገድና የገቢ አማራጮችን ከማስፋት አንጻርም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸው ነው በግምገማው የተመለካተው፡፡
በግማሽ ዓመቱ የምስራቅ አጠቃላይ፣ ኮከበ ጽብሃና ግዙፍ የግብዓት ማምረቻ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት መብቃት መቻሉ የኮርፖሬሽኑ በላቀ አፈጻጸም ላይ እንዳለ የሚያሳይ መሆኑን ተገምግሟል።
በዚህ ስኬትን ለማጽትና ለማስቀጠል በተሰሩ አንኳር ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገውን ግምገማ የመሩት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር ረሻድ ከማል ተጨማሪ የአፈጻጸም አቅጣጫም ሰጥተዋል፡፡
አገራዊ ፋይዳው የላቀ ትእምርት ባለው የኮሪደር ልማት፣ ኮርፖሬሽኑ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ በተጠናከረ ሁኔታ ለማስቀጠል የሚያስችል አቅጣጫም ተቀምጧል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ይዞት የመጣውን እድል በአግባቡ በመጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ውይይትና የአፈጻጸም አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ገንብቶ ለማስረከብ ውል የገባበቸውን ግዙፍ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ግንባታቸውን በጊዜ ገንብቶ ለማጠናቀቅ በልዩ ሁኔታ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡
የበርካታ ተቋማትን የአብረን እንስራ ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል ያልተቋረጠ የአቅም ግንባታ ሥራ መሰራት እንደለበት በግምገማው አጽንኦት ተሰጥቶበታል፡፡