🎖🎖 #ለሞት_ምን_ያህል_ተዘጋጅተናል?🎖🎖
✍ አሚር ሰይድ
{ كُلُّ نَفۡسࣲ ذَاۤىِٕقَةُ ٱلۡمَوۡتِۗ وَنَبۡلُوكُم بِٱلشَّرِّ وَٱلۡخَیۡرِ فِتۡنَةࣰۖ وَإِلَیۡنَا
تُرۡجَعُونَ }
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ለመፈተንም በክፉም በበጎም እንሞክራችኋለን፡፡ ወደኛም ትመለሳላችሁ፡፡(አል አንቢያእ 35)
🟢 አሊ (ረ.ዐ) እንዲህ ይሉ ነበር፡-
“ይህች ዓለም ጀርባዋን እየሰጠችንና እያለፈች ነው፡፡ መጪው ዓለም ደግሞ ከፊት ለፊታችን ሆኖ ይጠብቀናል፡፡ ሁለቱም የየራሳቸው ልጆች (ተከታዮች) አሏቸው፡፡ እናንተ የመጪው ዓለም ልጆች (ተከታዮች) እንጂ የዚህች አለም ተከታዮች አትሁኑ፡፡ ዛሬ የስራ ጊዜ ሲሆን ሒሳብ የለም፡፡ ነገ ደግሞ ሂሳብ እንጂ ለስራ የሚሆን ጊዜ የለም፡፡"ብለዋል (ቡኻሪ)
🔴 ሱፍያን አስ-ሰውሪ ገና በወጣትነት ዕድሜው ጀርባው ጐብጧል ፀጉሩም ሸብቷል፡፡ ይህ ለምን ሊሆን እንደቻለ ተጠይቆ ሲመልስ እንዲህ ብሏል፡-
“ብዙ እውቀት ያስገበየኝ አንድ መምህር (ኡስታዝ) ነበረኝ፡፡ ሊሞት በጣእር ላይ እያለ የእምነት ማረጋገጫ የሆነውን ከሊማ እንዲል ደጋግመን ብንወተውተውም ያንን ከሊማ ከአንደበቱ ሊያወጣ ሳይችል ሞተ። ይህ ክስተት ካየሁ በኋላ በሀሳብና በትካዜ ጐበጥኩ ፀጉሬም ሸበተ፡፡”ብሎ መለሰላቸዉ፡፡
🟣 የአላህ ወዳጅ የነበሩት ረቢእ ኢብን ሀይሰም (አላህ ይዘንላቸውና) ንግግርና ተግባር አንድ ሰው ለሞትና ለመጪው ዓለም ሕይወቱ ምን ያክል ማሰብና መጨነቅ እንዳለበት ያስገነዝባል፡-
“ረቢእ ኢብን ሀይሰም አንድ ጊዜ ከቤታቸው ጓሮ የመቃብር ጉድጓድ ቆፈሩ፡፡ ከዚያ በኋላ ቀልባቸው የደረቀና ከአላህ የራቁ በመሰላቸው ጊዜ ሁሉ እዚያ ጉድጓድ ውስጥ እየሄዱ በመጋደም ፍፃሜያቸውን ያስታውሱ ነበር፡፡ ይህን የሚያደርጉት አንድ ወቅት የሚገቡበት ቤታቸው ስለሚሆነዉ ቀብር እያሰቡ ስራቸውን ለማስተንተንና አካሄዳቸውን ለማሳመር ነው፡፡ እዚያ ውስጥ ገብተውም እያለቀሱ አላህን ምሕረት ይጠይቁት ነበር፡፡ የሚከተለውንም የቁርአን አንቀፅ ያነብባሉ፡-
{ حَتَّىٰۤ إِذَا جَاۤءَ أَحَدَهُمُ ٱلۡمَوۡتُ قَالَ رَبِّ ٱرۡجِعُونِ }
{ لَعَلِّیۤ أَعۡمَلُ صَـٰلِحࣰا فِیمَا تَرَكۡتُۚ كَلَّاۤۚ إِنَّهَا كَلِمَةٌ هُوَ قَاۤىِٕلُهَاۖ وَمِن وَرَاۤىِٕهِم بَرۡزَخٌ إِلَىٰ یَوۡمِ یُبۡعَثُونَ }
አንዳቸውንም ሞት በመጣበት ጊዜ እንዲህ ይላል «ጌታዬ ሆይ! ወደ ምድረ ዓለም መልሰኝ፡፡
በተውኩት ነገር በጎን ሥራ ልሠራ እከጅላለሁና፡፡»
(አል ሙዕሚኑን99-100)
ከዚያ ራላቸው ከማሱት የቀብር ጉድጓዳቸው ሲወጡም እንዲህ ይሉ ነበር-
“ረቢዕ ሆይ! ተመልከት! ዛሬ ወደ ሕይወት የመመለስ እድል አግኝተሀል፡፡ ሆኖም ግን ይህ ምኞትህ ፈፅሞ ተቀባይነት የማያገኝበት የምር ቀን ይመጣል፡፡ ስለዚህ ግሳፄህን ያዝ፡፡ ከዚያም መልካም ስራዎችን ለማብዛት ተጣደፍ፡፡ በአላህYy መንገድ የምታደርገውን ትግልህንና ለሞት የምታደርገውንም ዝግጅት አጧጡፍ፡፡”እያሉ ራሳቸዉን ይመክሩ ነበር፡፡
🟢 አቡ ዘር (ረ.ዐ) ለሞትና ከዚያ በሆላ የሚጠብቀን ፈተናን ሲገልፅ፡-
“በማንኛውም ንብረትህ (ሀብትህ) ይገባኛል ባዮች የሆኑ ሶስት አካላት አሉ፡፡
➊ የመጀመሪያው አንተ ራስህ ነህ፡፡
➋ሁለተኛው እድልህ ወይም እጣህ ነው፡፡ ይህም ጥሩ ይሁን መጥፎ፤ መከራ ወይም ሞት አንተን ሳያማክር ከች የሚል ነው፡፡
➌ ሶስተኛው ደግሞ ወራሽህ ሲሆን ባፍጢምህ እስክትደፋና ውርስ እስኪያገኝ ድረስ ትእግስት በማጣት የሚጠባበቅ ነው፡፡ ከሞትክለት ወዲያውኑ አንተ አላህ ፊት የምትጠየቅበትን ሀብትህን መንትፎ ዘወር ይላል፡፡ ስለሆነም አቅምህ ከቻለ በእነዚህ ሶስት ባለጋራዎችህ ላይ ክንድህ እንዳይዝል ቶሎ ቶሎ ብለህ ገንዘብህን ለመጪው ዓለም ሕይወትህ አሻግር፡፡ ብሏል
🔵 ኡመር (ረ.ዐ) በአንድ ወቅት አንዱን አገልጋያቸውን በየዕለቱ የሚከተለውን አረፍተ ነገር እንዲደግምላቸው አዘውት ነበር-
“ኡመር ሆይ! ሞትን አትርሳ!" አገልጋዩም ቀን በቀን ኡመር ሆይ ሞትን አትርሳ ይላቸዉ ነበር....ይሁን እንጂ በፂማቸው ላይ የተወሰኑ ነጫጭ ፀጉሮች መታየት ከጀመሩ በኋላ አገልጋያቸውን እንዲህ አሉት፡-
"ከእንግዲህ ማስታወሱ ይበቃሀል፡፡ እነዚህ በፂሜ ላይ የበቀሉት ነጫጭ ፀጉሮች በያንዳንዱ ቅፅበት ሞትን ያስታውሱኛልና፡፡''አሉት፡፡
እኛስ ሞትን እናስታዉሳለን ወይ??ዛሬ ላይ ወጣቱ የሚሰራዉ በስሜት ነዉ ነገ መሞትን እና አላህ ፊት መቅረብን ዘንግተናል ወገን!!!
ነገ ሞት ሳይቀድመን ዛሬ ለአላህ ቤታችን ሀብት ንብረት እናሻግር....
█
┻┻
╚▩PubLished by ▩╗
ISLAMIC UNIVERSITY
◈━━━━━━━━◈━━━━━━━━
4 another channal👇
t.me/Islam_and_Science
💐_⭐️💐⭐️___💐
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
✍ አሚር ሰይድ
{ كُلُّ نَفۡسࣲ ذَاۤىِٕقَةُ ٱلۡمَوۡتِۗ وَنَبۡلُوكُم بِٱلشَّرِّ وَٱلۡخَیۡرِ فِتۡنَةࣰۖ وَإِلَیۡنَا
تُرۡجَعُونَ }
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ለመፈተንም በክፉም በበጎም እንሞክራችኋለን፡፡ ወደኛም ትመለሳላችሁ፡፡(አል አንቢያእ 35)
🟢 አሊ (ረ.ዐ) እንዲህ ይሉ ነበር፡-
“ይህች ዓለም ጀርባዋን እየሰጠችንና እያለፈች ነው፡፡ መጪው ዓለም ደግሞ ከፊት ለፊታችን ሆኖ ይጠብቀናል፡፡ ሁለቱም የየራሳቸው ልጆች (ተከታዮች) አሏቸው፡፡ እናንተ የመጪው ዓለም ልጆች (ተከታዮች) እንጂ የዚህች አለም ተከታዮች አትሁኑ፡፡ ዛሬ የስራ ጊዜ ሲሆን ሒሳብ የለም፡፡ ነገ ደግሞ ሂሳብ እንጂ ለስራ የሚሆን ጊዜ የለም፡፡"ብለዋል (ቡኻሪ)
🔴 ሱፍያን አስ-ሰውሪ ገና በወጣትነት ዕድሜው ጀርባው ጐብጧል ፀጉሩም ሸብቷል፡፡ ይህ ለምን ሊሆን እንደቻለ ተጠይቆ ሲመልስ እንዲህ ብሏል፡-
“ብዙ እውቀት ያስገበየኝ አንድ መምህር (ኡስታዝ) ነበረኝ፡፡ ሊሞት በጣእር ላይ እያለ የእምነት ማረጋገጫ የሆነውን ከሊማ እንዲል ደጋግመን ብንወተውተውም ያንን ከሊማ ከአንደበቱ ሊያወጣ ሳይችል ሞተ። ይህ ክስተት ካየሁ በኋላ በሀሳብና በትካዜ ጐበጥኩ ፀጉሬም ሸበተ፡፡”ብሎ መለሰላቸዉ፡፡
🟣 የአላህ ወዳጅ የነበሩት ረቢእ ኢብን ሀይሰም (አላህ ይዘንላቸውና) ንግግርና ተግባር አንድ ሰው ለሞትና ለመጪው ዓለም ሕይወቱ ምን ያክል ማሰብና መጨነቅ እንዳለበት ያስገነዝባል፡-
“ረቢእ ኢብን ሀይሰም አንድ ጊዜ ከቤታቸው ጓሮ የመቃብር ጉድጓድ ቆፈሩ፡፡ ከዚያ በኋላ ቀልባቸው የደረቀና ከአላህ የራቁ በመሰላቸው ጊዜ ሁሉ እዚያ ጉድጓድ ውስጥ እየሄዱ በመጋደም ፍፃሜያቸውን ያስታውሱ ነበር፡፡ ይህን የሚያደርጉት አንድ ወቅት የሚገቡበት ቤታቸው ስለሚሆነዉ ቀብር እያሰቡ ስራቸውን ለማስተንተንና አካሄዳቸውን ለማሳመር ነው፡፡ እዚያ ውስጥ ገብተውም እያለቀሱ አላህን ምሕረት ይጠይቁት ነበር፡፡ የሚከተለውንም የቁርአን አንቀፅ ያነብባሉ፡-
{ حَتَّىٰۤ إِذَا جَاۤءَ أَحَدَهُمُ ٱلۡمَوۡتُ قَالَ رَبِّ ٱرۡجِعُونِ }
{ لَعَلِّیۤ أَعۡمَلُ صَـٰلِحࣰا فِیمَا تَرَكۡتُۚ كَلَّاۤۚ إِنَّهَا كَلِمَةٌ هُوَ قَاۤىِٕلُهَاۖ وَمِن وَرَاۤىِٕهِم بَرۡزَخٌ إِلَىٰ یَوۡمِ یُبۡعَثُونَ }
አንዳቸውንም ሞት በመጣበት ጊዜ እንዲህ ይላል «ጌታዬ ሆይ! ወደ ምድረ ዓለም መልሰኝ፡፡
በተውኩት ነገር በጎን ሥራ ልሠራ እከጅላለሁና፡፡»
(አል ሙዕሚኑን99-100)
ከዚያ ራላቸው ከማሱት የቀብር ጉድጓዳቸው ሲወጡም እንዲህ ይሉ ነበር-
“ረቢዕ ሆይ! ተመልከት! ዛሬ ወደ ሕይወት የመመለስ እድል አግኝተሀል፡፡ ሆኖም ግን ይህ ምኞትህ ፈፅሞ ተቀባይነት የማያገኝበት የምር ቀን ይመጣል፡፡ ስለዚህ ግሳፄህን ያዝ፡፡ ከዚያም መልካም ስራዎችን ለማብዛት ተጣደፍ፡፡ በአላህYy መንገድ የምታደርገውን ትግልህንና ለሞት የምታደርገውንም ዝግጅት አጧጡፍ፡፡”እያሉ ራሳቸዉን ይመክሩ ነበር፡፡
🟢 አቡ ዘር (ረ.ዐ) ለሞትና ከዚያ በሆላ የሚጠብቀን ፈተናን ሲገልፅ፡-
“በማንኛውም ንብረትህ (ሀብትህ) ይገባኛል ባዮች የሆኑ ሶስት አካላት አሉ፡፡
➊ የመጀመሪያው አንተ ራስህ ነህ፡፡
➋ሁለተኛው እድልህ ወይም እጣህ ነው፡፡ ይህም ጥሩ ይሁን መጥፎ፤ መከራ ወይም ሞት አንተን ሳያማክር ከች የሚል ነው፡፡
➌ ሶስተኛው ደግሞ ወራሽህ ሲሆን ባፍጢምህ እስክትደፋና ውርስ እስኪያገኝ ድረስ ትእግስት በማጣት የሚጠባበቅ ነው፡፡ ከሞትክለት ወዲያውኑ አንተ አላህ ፊት የምትጠየቅበትን ሀብትህን መንትፎ ዘወር ይላል፡፡ ስለሆነም አቅምህ ከቻለ በእነዚህ ሶስት ባለጋራዎችህ ላይ ክንድህ እንዳይዝል ቶሎ ቶሎ ብለህ ገንዘብህን ለመጪው ዓለም ሕይወትህ አሻግር፡፡ ብሏል
🔵 ኡመር (ረ.ዐ) በአንድ ወቅት አንዱን አገልጋያቸውን በየዕለቱ የሚከተለውን አረፍተ ነገር እንዲደግምላቸው አዘውት ነበር-
“ኡመር ሆይ! ሞትን አትርሳ!" አገልጋዩም ቀን በቀን ኡመር ሆይ ሞትን አትርሳ ይላቸዉ ነበር....ይሁን እንጂ በፂማቸው ላይ የተወሰኑ ነጫጭ ፀጉሮች መታየት ከጀመሩ በኋላ አገልጋያቸውን እንዲህ አሉት፡-
"ከእንግዲህ ማስታወሱ ይበቃሀል፡፡ እነዚህ በፂሜ ላይ የበቀሉት ነጫጭ ፀጉሮች በያንዳንዱ ቅፅበት ሞትን ያስታውሱኛልና፡፡''አሉት፡፡
እኛስ ሞትን እናስታዉሳለን ወይ??ዛሬ ላይ ወጣቱ የሚሰራዉ በስሜት ነዉ ነገ መሞትን እና አላህ ፊት መቅረብን ዘንግተናል ወገን!!!
ነገ ሞት ሳይቀድመን ዛሬ ለአላህ ቤታችን ሀብት ንብረት እናሻግር....
█
┻┻
╚▩PubLished by ▩╗
ISLAMIC UNIVERSITY
◈━━━━━━━━◈━━━━━━━━
4 another channal👇
t.me/Islam_and_Science
💐_⭐️💐⭐️___💐
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group