ብቻውን ለተቃውሞ አደባባይ የወጣው ግለሰብ‼
አዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 16/2018 የጠቅላይ ሚንስትሩን ስም በመጥቀስ መፈክር ይዞ ብቻውን ለተቃውሞ አደባባይ የወጣው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል።
ግለሰቡ ዛሬ ረፋድ 4:00 ላይ ያዘጋጀውን መፈክር ይዞ ከፍተኛ የህዝብ እንቅስቃሴ ባለበት መሀል መገናኛ ብረት ላይ አስደግፎ እሱ ከጎን ቆሞ ተቃውሞውን ሲያንፀባርቅ እንደነበር የገለፁት የአይን እማኞች ወዲያውኑ በአካባቢው በሚገኙ ፖሊሶች መያዙና ወደ ጣቢያ መወሰዱ አስረድተዋል።
በጉዳዩ ላይ እስካሁን ከፖሊስ የተሰጠ ማብራሪያ የለም።ስለሁኔታው ከየካ ሆነ ከቦሌ ክ/ከተሞች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም።
[ @MadoNews ]
አዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 16/2018 የጠቅላይ ሚንስትሩን ስም በመጥቀስ መፈክር ይዞ ብቻውን ለተቃውሞ አደባባይ የወጣው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል።
ግለሰቡ ዛሬ ረፋድ 4:00 ላይ ያዘጋጀውን መፈክር ይዞ ከፍተኛ የህዝብ እንቅስቃሴ ባለበት መሀል መገናኛ ብረት ላይ አስደግፎ እሱ ከጎን ቆሞ ተቃውሞውን ሲያንፀባርቅ እንደነበር የገለፁት የአይን እማኞች ወዲያውኑ በአካባቢው በሚገኙ ፖሊሶች መያዙና ወደ ጣቢያ መወሰዱ አስረድተዋል።
በጉዳዩ ላይ እስካሁን ከፖሊስ የተሰጠ ማብራሪያ የለም።ስለሁኔታው ከየካ ሆነ ከቦሌ ክ/ከተሞች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም።
[ @MadoNews ]