........ የቀጠለ.......
ኤኤፍፒ ያነጋገረው አንድ የአካባቢው ነዋሪ ሁለት የሞርታር ጥይቶች ቡሎሁቤይ ከተባለ ሰፈር ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት አቅራቢያ ላይ ወድቀው አንዲት በዕድሜ የገፉ ሴትን መቁሰላቸውን ተናግሯል።
በሞቃዲሾ አየር ማረፊያ የነበሩ የደኅንነት ባለሥልጣናትም የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸው ከአየር ማረፊያው በመውጣት ወደ ፕሬዝዳንቱ ቤተመንግሥት እስከሄዱበት ጊዜ ድረስ ምንም ዓይነት ነገር አለመከሰቱን ለዜና ወኪሉ አረጋግጠዋል።
አንድ ወደ ሞቃዲሾ ካመራው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ልዑክ ውስጥ አባል የሆኑ ግለሰብ ለዜና ምንጩ እንደተናገሩት ቡድኑ የሞርታር ጥቃት ስለመፈጸሙ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።
ይህ የኢትዮጵያው መሪ በሶማሊያ ጉብኝት በሚያደርጉበት ጊዜ የተፈጸመው የሞርታር ጥቃት ከጉብኝቱ ጋር ስለመያያዙ የታወቀ ነገር የለም። ለጥቃቱም በይፋ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን እስካሁን የለም።
ሐሙስ ረፋድ ሞቃዲሾ የገቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካን ቡድናቸው ከሶማሊያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ከተወያዩ በኋላ ከሰዓት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸው ተዘግቧል።
BBC
[ @MadoNews ]
ኤኤፍፒ ያነጋገረው አንድ የአካባቢው ነዋሪ ሁለት የሞርታር ጥይቶች ቡሎሁቤይ ከተባለ ሰፈር ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት አቅራቢያ ላይ ወድቀው አንዲት በዕድሜ የገፉ ሴትን መቁሰላቸውን ተናግሯል።
በሞቃዲሾ አየር ማረፊያ የነበሩ የደኅንነት ባለሥልጣናትም የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸው ከአየር ማረፊያው በመውጣት ወደ ፕሬዝዳንቱ ቤተመንግሥት እስከሄዱበት ጊዜ ድረስ ምንም ዓይነት ነገር አለመከሰቱን ለዜና ወኪሉ አረጋግጠዋል።
አንድ ወደ ሞቃዲሾ ካመራው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ልዑክ ውስጥ አባል የሆኑ ግለሰብ ለዜና ምንጩ እንደተናገሩት ቡድኑ የሞርታር ጥቃት ስለመፈጸሙ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።
ይህ የኢትዮጵያው መሪ በሶማሊያ ጉብኝት በሚያደርጉበት ጊዜ የተፈጸመው የሞርታር ጥቃት ከጉብኝቱ ጋር ስለመያያዙ የታወቀ ነገር የለም። ለጥቃቱም በይፋ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን እስካሁን የለም።
ሐሙስ ረፋድ ሞቃዲሾ የገቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካን ቡድናቸው ከሶማሊያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ከተወያዩ በኋላ ከሰዓት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸው ተዘግቧል።
BBC
[ @MadoNews ]