💢የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት💢
ክፍል ፴፮ [36]
📗የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት
፩.መልእክት ኀበ ሰብአ ሮሜ
ሮም የኢጣልያ ዋና ከተማ ስትሆን በቀድሞ ዘመን ግን በቅኝ ግዛት ለተያዙ አገሮች ሁሉ ርዕሰ ከተማ ነበረች።
የንጉሠ ነገሥት ከተማ ስለሆነች የልዩ ልዩ ሰዎች መናገሻ አድርገው በተለይም አይሁዶች ምኩራብ ሰርተው ሃይማኖታቸውን አጽንተው ብዙ አሕዛብ እየመለሱ ይኖሩ ነበር።
❖ የክርስትና ሃይማኖትም ፈጥኖ ወደ ሮም የገባው ቅዱስ ጳውሎስ ከሮም ጋር ከፍተኛ ግንኙነት ካላቸው ሀገሮች እንደ ኤፌሶን፣ቆሮንቶስ፣ተሰሎንቄ፣አቴና ባሉት ከተማዎች ትምህርቱና ተአምራቱ ተረድቶ ነበር።ከእነዚህ ሀገሮችም ሰዎች ሮም ሲሄዱ ትምህርቱንና ክርስትናውን ለሌላው ያስረዱ ስለነበር ነው።
►በጰንጠቆስጤ (መንፈስ ቅዱስ በወረደበት) ዕለት በግል ፍላጎታቸው በኢየሩሳሌም ተሰብስበው ከነበሩት ሮማውያን አይሁድ ውስጥ የቅዱስ ጴጥሮስን ሰብከት ሰምተው አምነው ተጠምቀው ሄደው ሮም ውስጥ ክርስትናን ያስፋፉ ሰዎች ነበሩ።
►ቅዱስ ጴጥሮስ ሮም ገብቶ ሲሰብክ ስለነበር ቅዱስ ጳውሎስ በ52 ዓ.ም ከአቴና ወጥቶ ወደ ቆሮንቶስ በሄደ ጊዜ በቀላውዴዎስ ቄሣር አዋጅ ከሮም ተሰደው የመጡ አቂላንና ሚስቱን ጵርስቅላን አገኘ።ከእነርሱም ጋር አንድ ዓመት ከስድስት ወር በዚሁ በቆሮንቶስ ቆየ። አቂላና ጵርስቅላ በሮሜ ስለሚገኙ ክርስቲያኖች ለቅዱስ ጳውሎስ ነገሩት። ቅዱስ ጳውሎስ መልእክቷን ሲጽፍ ከሮሜ ክርስቲያኖች መካከል የሚያውቋቸው ስላልነበሩ አቂላንና ጵርስቅላ ከከተማዋ ክርስቲያኖች ታዋቂ የሆኑትን የአንዳንዶቹን ስም ሰጥተውት መልእክቲቱን አዘጋጅቶ የክንክራኦስ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቢት በነበረችው በፌቨን እጅ በ54 ዓ.ም አካባቢ ላከላቸው፡፡(ሮሜ 16፥1) የሮሜ መልእክት 16 ምዕራፎች አሉት።
🍀የሮሜን መልእክት የጻፈበት ምክንያት
፩. ሮም ውስጥ የሚኖሩት ክርስትናን የተቀበሉት ሰዎች ወንጌል የምታስተምረውን ፍቅርና ሰላሞ ትተው በሥርዓትና በባሕል አይሁድና አሕዛብ ባለመስማማት በጭቅጭቅ ይኖሩ ነበር። ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሲሰማ ሁለቱን ወገኖች ለማስታረቅና በክርስትና እምነት ትምህርት እንዲኖሩ ለማድረግ መከፋፈል እንዳይኖር ይህችን መልእክት ጽፎላቸዋል፡፡ሮሜ1፥5-7
፪.አንዳንድ የክርስትና እምነት ጠላቶች የሆኑ ክርስቲያኖች በመንግስት ላይ ያምጻሉ ግብርም አይከፍሉም እያሉ የሀሰት ወሬ እያወሩ ክርስቲያኖችን በሥጋ ለተሾሙ ሁሉ እንዲገዙ (እምነታቸውን እስካልነኩባቸው ድረስ) በነፍስ ግን ለከርስቶስ መገዛት እንደሚገባ ለማስረዳት ጽፎላቸዋል።ሮሜ 13፥5-7
፫.ወደ ሮም እነርሱን ለመጎብኘት ከመሄዱ በፊት እየተማሩ እንዲቆዩና የጉዞውን ሁኔታም ለማመቻቸት ጽፎላቸዋል።
መ/ር ኢሳይያስ ሀብቴ
@mekra_abaw
ክፍል ፴፮ [36]
📗የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት
፩.መልእክት ኀበ ሰብአ ሮሜ
ሮም የኢጣልያ ዋና ከተማ ስትሆን በቀድሞ ዘመን ግን በቅኝ ግዛት ለተያዙ አገሮች ሁሉ ርዕሰ ከተማ ነበረች።
የንጉሠ ነገሥት ከተማ ስለሆነች የልዩ ልዩ ሰዎች መናገሻ አድርገው በተለይም አይሁዶች ምኩራብ ሰርተው ሃይማኖታቸውን አጽንተው ብዙ አሕዛብ እየመለሱ ይኖሩ ነበር።
❖ የክርስትና ሃይማኖትም ፈጥኖ ወደ ሮም የገባው ቅዱስ ጳውሎስ ከሮም ጋር ከፍተኛ ግንኙነት ካላቸው ሀገሮች እንደ ኤፌሶን፣ቆሮንቶስ፣ተሰሎንቄ፣አቴና ባሉት ከተማዎች ትምህርቱና ተአምራቱ ተረድቶ ነበር።ከእነዚህ ሀገሮችም ሰዎች ሮም ሲሄዱ ትምህርቱንና ክርስትናውን ለሌላው ያስረዱ ስለነበር ነው።
►በጰንጠቆስጤ (መንፈስ ቅዱስ በወረደበት) ዕለት በግል ፍላጎታቸው በኢየሩሳሌም ተሰብስበው ከነበሩት ሮማውያን አይሁድ ውስጥ የቅዱስ ጴጥሮስን ሰብከት ሰምተው አምነው ተጠምቀው ሄደው ሮም ውስጥ ክርስትናን ያስፋፉ ሰዎች ነበሩ።
►ቅዱስ ጴጥሮስ ሮም ገብቶ ሲሰብክ ስለነበር ቅዱስ ጳውሎስ በ52 ዓ.ም ከአቴና ወጥቶ ወደ ቆሮንቶስ በሄደ ጊዜ በቀላውዴዎስ ቄሣር አዋጅ ከሮም ተሰደው የመጡ አቂላንና ሚስቱን ጵርስቅላን አገኘ።ከእነርሱም ጋር አንድ ዓመት ከስድስት ወር በዚሁ በቆሮንቶስ ቆየ። አቂላና ጵርስቅላ በሮሜ ስለሚገኙ ክርስቲያኖች ለቅዱስ ጳውሎስ ነገሩት። ቅዱስ ጳውሎስ መልእክቷን ሲጽፍ ከሮሜ ክርስቲያኖች መካከል የሚያውቋቸው ስላልነበሩ አቂላንና ጵርስቅላ ከከተማዋ ክርስቲያኖች ታዋቂ የሆኑትን የአንዳንዶቹን ስም ሰጥተውት መልእክቲቱን አዘጋጅቶ የክንክራኦስ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቢት በነበረችው በፌቨን እጅ በ54 ዓ.ም አካባቢ ላከላቸው፡፡(ሮሜ 16፥1) የሮሜ መልእክት 16 ምዕራፎች አሉት።
🍀የሮሜን መልእክት የጻፈበት ምክንያት
፩. ሮም ውስጥ የሚኖሩት ክርስትናን የተቀበሉት ሰዎች ወንጌል የምታስተምረውን ፍቅርና ሰላሞ ትተው በሥርዓትና በባሕል አይሁድና አሕዛብ ባለመስማማት በጭቅጭቅ ይኖሩ ነበር። ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሲሰማ ሁለቱን ወገኖች ለማስታረቅና በክርስትና እምነት ትምህርት እንዲኖሩ ለማድረግ መከፋፈል እንዳይኖር ይህችን መልእክት ጽፎላቸዋል፡፡ሮሜ1፥5-7
፪.አንዳንድ የክርስትና እምነት ጠላቶች የሆኑ ክርስቲያኖች በመንግስት ላይ ያምጻሉ ግብርም አይከፍሉም እያሉ የሀሰት ወሬ እያወሩ ክርስቲያኖችን በሥጋ ለተሾሙ ሁሉ እንዲገዙ (እምነታቸውን እስካልነኩባቸው ድረስ) በነፍስ ግን ለከርስቶስ መገዛት እንደሚገባ ለማስረዳት ጽፎላቸዋል።ሮሜ 13፥5-7
፫.ወደ ሮም እነርሱን ለመጎብኘት ከመሄዱ በፊት እየተማሩ እንዲቆዩና የጉዞውን ሁኔታም ለማመቻቸት ጽፎላቸዋል።
መ/ር ኢሳይያስ ሀብቴ
@mekra_abaw