በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር እንዲቀነስ መጠየቁ ተገለጸ
በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድን በደብዳቤ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ገለጹ።የኮንፌደሬሽኑ ፕሬዘዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ለአሜሪካ ድምጽ እንደገለጹት የብር የመግዛት አቅም መዳከም ጋር ተያይዞ ቋሚ ደመወዝ የሚያገኙ ሰራተኞች ለከፍተኛ የኑሮ ፈተና እየተዳረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
"በተለይም ዝቅተኛ ገቢ የሚያገኘው ሰራተኛ ቀን ቀን እየሠራ ማታ ማታ ሆቴሎች ላይ ፍርፋሪ እየለመነ እያደረ ነው።" ያሉት ፕሬዝዳንቱ የኑሮ ጫናው በተለይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ተቀጥረው በሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ያያለ መሆኑን ጠቁመዋል።
አክለውም ከዚህ በፊት በሰራተኞች የኑሮ ሁኔታ ዙርያ ከጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን አስታውሰው ነገር ግን እነዚህ ውይይቶች ይበል የሚያሰኝ ውጤት አለማስገኘታቸውን ተናግረዋል።በመሆኑም የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች የኑሮ ፈተናውን ሊያቀሉ የሚችሉ ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትሩን በድጋሚ በደብዳቤ መጠየቃቸውን አመላክተዋል።
Via Addis Standard
@MeribahTimes
በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድን በደብዳቤ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ገለጹ።የኮንፌደሬሽኑ ፕሬዘዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ለአሜሪካ ድምጽ እንደገለጹት የብር የመግዛት አቅም መዳከም ጋር ተያይዞ ቋሚ ደመወዝ የሚያገኙ ሰራተኞች ለከፍተኛ የኑሮ ፈተና እየተዳረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
"በተለይም ዝቅተኛ ገቢ የሚያገኘው ሰራተኛ ቀን ቀን እየሠራ ማታ ማታ ሆቴሎች ላይ ፍርፋሪ እየለመነ እያደረ ነው።" ያሉት ፕሬዝዳንቱ የኑሮ ጫናው በተለይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ተቀጥረው በሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ያያለ መሆኑን ጠቁመዋል።
አክለውም ከዚህ በፊት በሰራተኞች የኑሮ ሁኔታ ዙርያ ከጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን አስታውሰው ነገር ግን እነዚህ ውይይቶች ይበል የሚያሰኝ ውጤት አለማስገኘታቸውን ተናግረዋል።በመሆኑም የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች የኑሮ ፈተናውን ሊያቀሉ የሚችሉ ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትሩን በድጋሚ በደብዳቤ መጠየቃቸውን አመላክተዋል።
Via Addis Standard
@MeribahTimes