Meribah Times - መሪባ ታይምስ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


በአገራችንና ቀጠናችን ላይ ወቅታዊ መረጃዎችን በዚህ ቴሌግራም ገፅ እንጋራለን !!!
This channel provides political, economical and social information, analysis on Ethiopia and the horn of Africa!!!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ልጆቼ ይቅርታ!

ለልጆቼ የማወርሰው የለኝም፣ የምኖረው በቤት ኪራይ ነው የምሰራው የመንግስት መስሪያ ቤት በሹፌርነት ነው!

ለበርካታ ዓመታት ያጠራቀምኳትን የልጆቼን ውርስ ለመቄዶንያ ለመስጠት ነው የመጣውት!

አካውንቴ ላይ 107ሺህ ብር አለ ያሉት አቶ አብርሃም 100 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጎልናል!

አቶ አብርሃም ልጆቼ ይቅርታ የማወርሳችሁ ገንዘብ አይደለም
ለእናንተ የሚጠቅማችሁ መቄዶንያን ባወርሳችሁ ነው ብለዋል!

አቶ አብርሃም ሌሎች ግለሰቦችም ካላችሁ ላይ ብቻ ሳይሆን ከሌለን ላይም ማካፈል አለብን ሁላችንም ተረባርበን መቄዶንያን ለልጆቻችን እናውርስ ብለዋል!

መርቁልን!

መቄዶንያ-mekedonia


በቀደምት ጀግኖች አያቶቻችን ታላቅ ተጋድሎ እና መስዋዕትነት እንዲሁም በታላቁ ታሪክ የማይረሳው ንጉሳችን ዳግማዊ አጤ ምንሊክ እና በእቴጌ ጣይቱ ብጡል ብልህ አመራር እና አስተባባሪነት ለተቀዳጀነው አንፀባራቂው የ፻፳ ወ፱ኛው የአድዋ ድል በዓል እንኳን አደረሳችሁ የሚል መልዕክቴን ሳስተላልፍ በታላቅ ብሔራዊ ኩራት ነው::  

ይህ በታሪክ ተመዝግቦ በየአመቱ የምንዘክረው አድዋ ላይ የተቀዳጀነው ድል የኢትዮጵያን ነፃነት ያስከበረ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ የቅኝ ግዛት ቀንበር ተጭኗቸው ሲሰቃዩ ለነበሩ አፍሪካዊያን ወንድም እና እህቶቻችን እንዲሁም በመላው አለም በጭቆና ውስጥ የነበሩትን ጥቁር ህዝቦች ቀና ብለው እንዲሄዱ እና ነፃ እንዲወጡ በወቅቱ ታላቅ መነቃቃትን የፈጠረ  ገናና የጥቁር ህዝቦች ድል ነው።

የዘንድሮውን የ፻፳ ወ፱ ኛው የአድዋ ድል በአል ስናከብር ሀገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ቀላል ለማይባሉ አመታት አንድነቷን አስጠብቃ ወደ ፊት እንዳትራመድ ሰቅዞ የያዛትን ተከታታይ የብሔር  ፖለቲካ አዙሪት እንደ ሀገር እና እንደ ህዝብ ያስከፈለንን እና እያስከፈለን ያለውን ዋጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ካለንበት ውስብስብ እና እጅግ ኋላቀር የዘር ፖለቲካ ለመውጣት ከመቼውም ጊዜ በላቀ አንድነታችንን አስተባብረን የህልውናችን መሰረት የሆነችው እናት ሀገራችንን ለማዳን በንቃት መቆም ይጠበቅብናል።



ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)


ፓርቲዎቹ መንግሥታዊ ሽብር እና የጦር ወንጀል የሆነውን የድሮን ጥቃት፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ፣ የፖለቲካ ልኂቃን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሑራን፣ የመገናኛ ብዙኅንና የሰብዓዊ መብት ተማጋቾች እንዲያወግዙት ጥሪ አቀረቡ‼️
==========

እናት ፓርቲ፣ መኢአድ፣ ኢሕአፓ እና አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ በቅርቡ በአማራ ክልል፣ ምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ፣ አነገሽ በተባለ ቀበሌ ልዩ ስሙ ሐሙስ ገበያ በተባለ ሥፍራ የካቲት 13 ቀን የተፈጸመው የድሮን ጥቃት "የመንግሥታዊ ሽብር ማሳያ" ነው በማለት ዛሬ በጋራ ባወጡት መግለጫ አውግዘዋል።

ፓርቲዎቹ፣ በጥቃቱ ታዳጊ ሕጻናትን ጨምሮ 16 ንጹሃን ሰዎች እንደተገደሉና ሌሎች 11 ሰዎች ክፉኛ እንደቆሰሉ ገልጸዋል። ፓርቲዎቹ፣ መንግሥት ፖለቲካዊ ድክመቱን ለመሸፈን የጸጥታ ኃይሉን "ወደ ፖለቲካው በመሳብና እንዲኽ ያሉ በጦር ወንጀል ጭምር የሚያስጠይቁ የንጹኃን ጭፍጨፋ፣ መሰወርና የዘፈቀደ ግድያዎችን እንዲፈጽም የእጅ ጥምዘዛ ያህል እያስገደደውና እያሳሳተው ይገኛል" በማለት ከሰዋል።

ፓርቲዎቹ፣ "መንግሥታዊ ሽብር" እና "የጦር ወንጀል" ሲሉ የጠሩትን የድሮን ጥቃት፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ፣ የፖለቲካ ልኂቃን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሑራን፣ የመገናኛ ብዙኅንና የሰብዓዊ መብት ተማጋቾች እንዲቃወሙት ጠይቀዋል።




Forward from: Asfaw abreha
1.  WTTASA urges GSTS to reevaluate all its politically motivated and biased statements it has issued.
2.  WTTASA demands that GSTS to retract its false claim regarding the indigenous Welqait Tegede and Tellemt Amhara community, as such claim could potentially jeopardize their right to self-determination and freedom of the people.
3.  WTTASA calls on GSTS to refrain from engaging in political agendas and sensationalized narratives. Instead, it should adhere to its stated purpose as non-profit, non- religious and non-political organization in Ethiopia.

Conclusion
The Welqait Tegede Tellemt Amhara Scholars’ Association remains committed to advocating for historical truth, constitutional integrity, and the rights of the indigenous Amhara community. Any attempts to distort historical facts and undermine the people’s right to self-determination will be firmly opposed.

Let’s share the proverb of Albert Einstein, ‘‘Peace cannot be kept by force It can only be achieved by Understanding!’’


Welqait Tegede Tellemt Amhara Scholars Association
(WTTASA)
19th February 2025
Humera, Amhara; Ethiopia.


Forward from: Asfaw abreha
Statement Release
Welqait Tegede Tellemt Amhara Scholars’ Association.
...
Welqait Tegede Tellemt Amhara Scholars’ Association (WTTASA) has carefully reviewed the official statement issued by Global Society of Tigray Scholars and Professionals (GSTS) issued on February 18, 2025 G.C. This statement referenced remarks made by H.E. Chief Olusegun Obasanjo, AU high representative for the horn of Africa, during the recent AU session on the ‘Lessons Learned Report from AU led Peace Process for the Tigray region of Ethiopia’.    
During his session, H.E Olusegun Obasanjo emphasized that Welqait Tegede, Tellemt and Raya ‘‘Contested Areas (indirectly referring to welqait Tegede, Tellemt and Raya) must remain neutral until the issue is solved’’. Despite this, GSTS’s statement attempted to portray these areas as part of Tigray region. A claim that directly contradicts to The Pretoria Agreement for Lasting Peace Through a Permanent Cessation of Hostilities (COHA) between TPLF and FDRE notably, Article 10/4 which explicitly states that ‘‘The Parties commit to resolving issues of Contested Areas in accordance with the constitution of FDRE’’.
Furthermore, any statement that disregards the true nature of Pretoria Agreement and the FDRE constitution jeopardize the ongoing peace process and is unacceptable to WTTASA.

Condemnation of GSTS’s Statement 
Welqait Tegede Tellemt Amhara Scholars Association strongly condemns the GSTS’s characterization of these areas as ‘‘occupied Tigray Territories’’ as such cliam are misleading and inconsistent with the Pretoria Permeant Peace Agreement and FDRE constitution. Historical records clearly shows that Welqait Tegede Tellemt and Raya were unlawfully and forcefully annexed to Tigray region in 1991 before the adoption and enforcement of FDRE constitution in 1995.
As it is well documented and known by both TPLF and FDRE the People of Welqait Tegede Tellemt has submitted Amhara Identity Quest Petition signed by greater than 25,000 individuals to Tigray regional administration and Federal government in December 2015 G.C. However, rather than addressing these demands through legal and constitutional means, TPLF response was Kidnappings, Mass detentions and the killing of representatives advocating for their People’s identity rights.  (Refer to the United States House of Representatives Committee on Foreign Affairs: (https://docs.house.gov/meetings/FA/FA16/20170309/105673/HHRG-115-FA16-Wstate-TirfeT-20170309.pdf).

Additionally, the Tigray regional council deliberately obstructed the effort of the Federal government by totally rejecting the work of the Commission for Identity and Administrative boundaries of Ethiopia to resolve the issues of Welqait Tegede Tellemt and Raya. The TPLF also hampered legal procedures and the due process of law by appointing its Executive committee member as a speaker for the House of Federation.      
November 4, 2020 TPLF launched a military attack on the Northern Division of Ethiopian National Defense Force, triggering in to a full-scale war aimed at regaining power in Ethiopia.  Following the law enforcement action by FDRE against TPLF’s aggression, The People of Welqait Tegede, Tellemt and Raya declared its freedom from TPLF’s Apartheid like regime. By now the people continue to exercise self-administration and freedom, in spite of numerous challenges; like the threat of reinvasion by TPLF and war mongering by TPLF combatants. This self-administration of the people by the people is not only constitutional but also helpful for maintaining regional stability and sustainable peace in the Horn of Africa.

Call to Action
All in all, Weqlait Tegede Tellemt Amhara Scholars Association strongly condemns the statement issued by GSTS regarding welqait Tegede Telllemt and Raya and calls for the following actions;


የኦሮሚያው ባለስልጣን ተገደሉ ‼️

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሱሉልታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አበበ ወርቁ እና የወረዳው የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ ነጋሽ ድሪባ፣ አማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ዛሬ ከቀትር በኋላ በፈጸመባቸው ድንገተኛ ጥቃት መገደላቸውን ተሰማ።

። የቡድኑ ታጣቂዎች ድንገተኛ ተኩስ የከፈቱት፣ ዋና አስተዳዳሪው፣ የወረዳው የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊና በርካታ የጸጥታ ኃይል አባላት ቡድኑ በስፋት ይንቀሳቀስበታል ወደሚባለው 'ሞዬ ጋጆ' በተባለ ሥፍራ ላይ ሲደርሱ እንደነበር ምንጮች ተናግረዋል።

ታጣቂዎቹን በርካታ የጸጥታ ኃይል አባላትን አፍነው እንደወሰዱም ምንጮች ጠቁመዋል።

ቁጥራቸው ያልታወቀ የጸጥታ ኃይል አባላት በጥቃቱ ሲገደሉ፣ በርካቶች ደሞ ቆስለው ጫንጮ ሆስፒታል ገብተዋል ተብሏል። አበበ ከኹለት ዓመት በፊት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ኾነው ከመሾማቸው በፊት፣ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ነበሩ።

ዋዜማ




«በአሸባሪነት የሚፈልገኝ የኢትዮጵያ መንግስት ወደ ሀገር ቤት እንዳልገባ ከለከለኝ!» ልደቱ አያሌው

አቶ ልደቱ አያሌው ዛሬ ለመላ ኢትዮጵያውያን የሚከተለውን ደብዳቤ ተበትነዋል👇

ጉዳዩ፦ ወደ አገሬ እንዳልጓዝ መከልከልን ይመለከታል

ወደ ኢትዮዽያ ለመሄድ በኢትዮዽያ አየር መንገድ ትኬት የቆረጥኩት ለዛሬ ስለሆነ ከጧቱ 12 ሰዓት በአትላንታ ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝቸ ነበር። የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈ የኢትዮዽያ ፓስፖርትና የተረጋገጠ የጉዞ ትኬት ይዥ የተገኘሁ ቢሆንም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ግን በአሜሪካ የኢትዮዽያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮዽያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።

በአሸባሪነት ወንጀል ሊከሰኝ እንደሚፈልግና በቁጥጥር ስር እንድውል ከኢንተር-ፖል ጋር ጭምር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲገልፅ የነበረው የኢትዮዽያ መንግስት ዛሬ በራሴ ፈቃድ ወደ አገሬ ለመመለስ ስሞክር በእኔ ላይ ህገ-ወጥ ክልከላ ማድረጉ አስገርሞኛል። ምን አልባት እንዲህ አይነቱ ድርጊት በአለም ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈፀመ ሊሆን ይችላል። መንግስት እኔን በወንጀለኛነት ከጠረጠረኝ ሊከሰኝና ሊያስረኝ ይችላል እንጅ ወደ አገሬ እንዳልገባ ሊከለክለኝ አይችልም።

አንድን ኢትዮዽያዊ የሆነና የኢትዮዽያ ፓስፖርት የያዘን ዜጋ ወደ አገሩ እንዳይገባ ለመከልከል የሚያስችል ምንም ዓይነት የህግ ማዕቀፍ የለም። ስለሆነም በሌላ አገር አየር መንገድ ትኬት ቆርጨ ሰሞኑን ወደ አገሬ ተመልሸ እንደምሄድ በዚህ አጋጣሚ አሳውቃለሁ።

ከአክብሮት ጋር

ልደቱ  አያሌው




መልካም ዜና

#ቲክቶክ ከቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳነት ትራምፕ በተሰጠው ዋስትና ወደ አገልግሎት ለጊዜው መመለሱን አስታወቀ።

#UnitedStates #SocialMedia #TiktokBan #China #DonaldTrump


#ታላቅ_የምሥራች_ከወደ_ፌዴራል_ከፍተኛ_ፍርድ_ቤት

እናት ፓርቲ የመሠረተውን ክስ በተመለከተ!
***
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር ብሎ ከከተማዋ ነዋሪ እየሰበበሰበ ያለው ግብር "ሕገ ወጥ መኾኑን" በመግለጽ እናት ፓርቲ ክስ መመሥረቱ ይታወሳል። ክሱን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አስተዳደር ችሎት ዛሬ ጥር ፱ ቀን  ፳፻፲፯ ባስቻለው ችሎት የንብረት ግብር ማሻሻያ ጥናት ተብሎ ሚያዝያ ፫ ቀን ፳፻፲፭ የወጣውና "ለግብሩ መሰብሰብ መሠረት የሆነው መመሪያ ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም" ተብሎ መመሪያው እንዲሻር በሙሉ ድምጽ መወሰኑን እናት ፓርቲ ለመላው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችና የፍርድ ሂደቱን ሲከታተሉ ለነበሩ ፍትሕ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በደስታ ይገልጻል።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

እናት ፓርቲ
ጥር ፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ


ልባቸውን ጨምሮ ከወገባቸው በታች ተጣብቀው የተወለዱት አሜሪካዊ ጥንዶች ማርገዛቸው  እየተነገረ ነው።

እነዚሁ አንድ ማህፀን ያላቸው አቢ እና ብሪቲና ሂንሲል ከአንድ ወር በኋላ 35ኛ እድሜያቸውን የሚያከብሩት ተጣብቀው የተወለዱ መንትዮች "ልጅ ለማግኘት መንገድ ላይ ነን" ሲሉ በቲክቶክ ላይ ያጋሩ ሲሆን 'ሳያረግዙ አልቀረም' የሚል ግምት በስፋት እየተናፈሰ ይገኛል።

** የሚወልዱት ልጅ እናቱ ማን ልትሆን ነው? የሚል ድንገትም አዲስ ህግ የሚያስፈልገው ጥያቄም አስነስቷል።
ምንጩ ፊደል ነው።


Erasmus Mundus GOALS Scholarship 2025/27 in Europe 🇪🇺 (Fully Funded)

2 Year Master Degree Program Prepared by Five Universities in France, Portugal, Lithuania, Luxembourg, and Poland.

The Scholarship Covers Airfare, Meals, Accommodation, Visa, Tuition, Insurance, Allowance.

Visit: https://opportunitiescorners.com/erasmus-mundus-goals-scholarship/

Deadline: 16th February 2025

@MeribahTimes


"የመንግስት አካላት ለሰብዓዊ መብት መጠበቅ ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው ጥሰቶቹ  እንደቀጠሉ ይገኛሉ"- ኢሰመጉ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ በሚገኙ ቀበሌዎች በተደረገ ምርመራ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህጻናት፣አረጋውያን እና ሴቶች በታጠቁ መገደላቸውን አስታውቋል፡፡

ምርመራው የተደረገው ከታህሳስ 7ቀን2016 እስከ ህዳር 23/ 2017 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ በሚገኙ 20 ቀበሌዎች በተፈጸሙ ኢሰብዓዊ ድርጊቶች የንጹሀን ህይወት ማለፉን ለማወቅ መቻሉን ኢሰመጉ ገልጿል።

ይህን ተከትሎም የፌደራል እና የኦሮምያ ክልል መንግስታት በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሱ የመጡትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በቂ ትኩረት በመስጠት የህዝቡ ሰላም ተጠብቆለት የመኖር መብቱን እንዲያስከብሩ አሳስቧል፡፡

በተጨማሪም በኦሮምያ ክልል በተደጋጋሚ ጊዜ ለሚፈጸሙ ጥቃቶች የፌደራልና የኦሮምያ ክልል መንግስታት የጸጥታ አካላት ጥቃቶች ሳይደርሱ ቅድመ የመከላከል ስራን መስራት፣ ተፈጽመው ሲገኙም አፋጣኝ ምላሽ የመስጠት ስራን በትኩረት በመስራት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል፡፡

@MeribahTimes


የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ከ #አየር መንገድ
-------
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ሙያ መስክ የስራ ቅጥር አውጥቷል።


መወዳደር የምትፈልጉ ዝርሩን በተከታዩ የአየር መንገዱ ሊንክ ታገኛላችሁ 👇

https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies

#ኢትዮጵያ
#ET
@MeribahTimes


የስራ ማስታወቂያ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ
------

በበረራ አስተናጋጅነት ጀማሪ ሰራተኞችን ለመቅጠር አየር መንገድ ማስታወቂያ አውጥቷል።


ዝርዝሩ በፎቶ ላይ የሚገኝ ሲሆን ለተጨማሪ ግን ይህን ሊንክ ይጠቀሙ 👇👇

https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies#collapsetwo_6

@MeribahTimes


የስራ ማስታወቂያ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ
------

በበረራ አስተናጋጅነት ጀማሪ ሰራተኞችን ለመቅጠር አየር መንገድ ማስታወቂያ አውጥቷል።


ዝርዝሩ በፎቶ ላይ የሚገኝ ሲሆን ለተጨማሪ ግን ይህን ሊንክ ይጠቀሙ 👇👇

https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies#collapsetwo_6

@MeribahTimes


በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር እንዲቀነስ መጠየቁ ተገለጸ

በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድን በደብዳቤ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ገለጹ።የኮንፌደሬሽኑ ፕሬዘዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ለአሜሪካ ድምጽ እንደገለጹት የብር የመግዛት አቅም መዳከም ጋር ተያይዞ ቋሚ ደመወዝ የሚያገኙ ሰራተኞች ለከፍተኛ የኑሮ ፈተና እየተዳረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

"በተለይም ዝቅተኛ ገቢ የሚያገኘው ሰራተኛ ቀን ቀን እየሠራ ማታ ማታ ሆቴሎች ላይ ፍርፋሪ እየለመነ እያደረ ነው።" ያሉት ፕሬዝዳንቱ የኑሮ ጫናው በተለይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ተቀጥረው በሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ያያለ መሆኑን ጠቁመዋል።

አክለውም ከዚህ በፊት በሰራተኞች የኑሮ ሁኔታ ዙርያ ከጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ ጋር ተደጋጋሚ  ውይይቶች መደረጋቸውን አስታውሰው ነገር ግን እነዚህ ውይይቶች ይበል የሚያሰኝ ውጤት አለማስገኘታቸውን ተናግረዋል።በመሆኑም የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች የኑሮ ፈተናውን ሊያቀሉ የሚችሉ ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትሩን በድጋሚ በደብዳቤ መጠየቃቸውን አመላክተዋል።

Via Addis Standard

@MeribahTimes


የስራ ቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ሰራተኞች ሸማቾች ማህበር በሶስት መደብ የሰራተኛ ቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል ።

ገንዘብ ያዥ ፣ አካውንታት እና ሽያጭ

ዝርዝሩን ፎቶው ላይ ይመልከቱ ☝️☝️

20 last posts shown.