በልብ ግዘፉ!
ሳታስቡት ቀን ይጥላችኋል፣ እንዲሁ ከመቅፅበት ነገሮች ይበላሹባችኋል፣ በአጋጣሚ በሰውም ሆነ በሁኔታዎች ተጎጂ ትሆናላችሁ፣ ብቻችሁን ፊትለፊት መጋፈጥ ላለባችሁ ችግር ትጋለጣላችሁ። አውቃችሁ አልገባችሁበትም ነገር ግን ከዚህ አጣብቂኝ የመውጣት ግዴታ ይኖርባችኋል፣ ፈልጋችሁ አልተፈተናችሁም ነገር ግን ፈተናውን የማለፍ ግዴታ አለባችሁ። ሁሉን ነገር እንደ አመጣጡ የሚመልስ ማንነት በአንዴ አይገነባም፣ ከሁኔታዎች በላይ የሆነ ስብዕና በትንሽ ጊዜ አይመጣም። ልባችሁ ትንሽ ሲሆን በትንሹም በትልቁም ነገር ላይ ለመፍረድ ትቸኩላላችሁ፣ የማስተዋል አቅማችሁ አናሳ ሲሆን ከራሳችሁ በላይ የሰውን ጉድፍና ድክመት መመልከት ትጀምራላችሁ፣ ያልተሰራ ማንነት ሲኖራችሁ ዝቅ ማለትን ትጠየፋላችሁ፣ ንቀትና እብሪት ይነግስባችኋል፣ በሰው ላይ የበላይነታችሁን ለማሳየት ትደክማላችሁ፣ ሁሉም ሰው እንዲወዳችሁና እንዲቀበላችሁ ትጠብቃላችሁ፣ ክፋትን በላቀ ክፋት፣ መጎዳትንም በሌላ ጉዳት ለመመለስና ለመሻር ትሞክራላችሁ። ስታድጉ ሁሉም ነገር ድካም እንደሆነ ይገባችኋል፣ ትንሽ መብሰል ስትጀምሩ ጥሩ ስለሆናችሁ ብቻ የሚወሰድባችሁ ነገር እንደሌለ ትረዳላችሁ።
አዎ! በልብ ግዘፉ፣ በሃሳብ እደጉ፣ ራሳችሁን በማስተዋል አንፁ፣ በትምህርት ከፍ በሉ፣ ለጥበብ ልቦናችሁን ክፈቱ፣ ብስለትን በጊዜ ተለማመዱ። እውቀት ስም ያስጠራል፣ ተፈላጊና ተወዳጅ ያደርጋል፣ ጥበብ ግን ያነግሳል፣ ጥበብ ችግር ፈቺና እንቁ ሰው ያደርጋል። ልባችሁን ለጥበብ ክፈቱ፣ ውስጣችሁን ተነግሮ በማያልቅ መንፈሳዊ እውቀት ሙሉት፣ ሁሉም ሰው የሚመኘውን ፅኑ ማንነት ገንቡ። ማድረግ እየቻላችሁ እናንተን የሚጠቅም ቢሆን አንኳን ሰውን የሚጎዳ ስለሆነ ብቻ የማታደርጉት ነገር ይኑር። ከማንኛውም ሰው ጋር የምትወዳደሩት በሚታየው ስኬት፣ ንብረት ወይም ገንዘብ ሳይሆን፣ በማይታየውና በመልካም ምግባሮች በሚገለጠው ትልቁ ልባችሁ ይሁን። ልባቸው ትልቅ የሆኑ ሰዎች ቅንኖች ናቸው፣ ራሳቸውን የሚያውቁ፣ የሚፈልጉትን የሚያውቁ፣ ህይወትን በተለየ መንገድ የተረዱና እንዴት ክብራቸውን ሳያጡ ከሰው ጋር መኖር እንደሚችሁ የተረዱ ሰዎች ናቸው። ልባችሁን ዘግታችሁ ራሳችሁን አታስጨንቁ፣ ቀለል ብላችሁ ቀላል ህይወት ኑሩ።
አዎ! ጀግናዬ..! በማይሆን መንገድ አዕምሮህን አትወጥረው፣ በአጉል ልክ አልባ የክፋት ሃሳብ ልህን አታስጨንቃት። ትልቅ ሆነህ ትንሽ ስራ አትስራ፣ እያወቅክ በሚያጠፋህ መጥፎ ምግባር አትወጠር። አንተ አሳልፈህ ካልሰጠሀው ያንተን ሰላም የሚቀማህ ሰው የለም፣ አንተ ካልፈቀድክ ማንም ከታላቅነት ማማህ ላይ ሊያወርድህ አይችልም። ለሰው ብዙ አድርገህ ምላሽ የጠበቅበትን ጊዜ አስታውስ፣ አንተ መልካም ሆነ በክፉ ሰዎች የተጎዳህበትን ወቅት አስታውስ፣ ብዙ ሰጥተህ ባዶ እጅህን የቀረበትን ሰዓት አስታውስ። ትልቅ ሰው የሚሰጠው ተቀባዩን ለመጥቀም ሳይሆን ራሱን ለመጥቀም ነው። ካንተ የሆነው ነገር በቅንነት ከሆነ ትልቁ ስጦታህና ሽልማት ውስጣዊ ሃሴት ነው። ልብህ ብሩህ ሆኖ ሳለ የጨለማን ሃሳብ አታስብ፣ ተስፋ እያለህ የተስፋ ቢስ ሰው ተግባርን አትፈፅም። ለሰው ለመድረስ ከመድከምህ በፊት አስቀድመህ ራስህን ከመጥፎ ትርክቶችና ኩናኔዎች አድን። ለራስህ መሆን ሰትችል ለሁሉ መድረስ ትችላለህ፣ ራስህን ሰትጠቅም የምትፈልገውን ሰው መጥቀም ትችላለህ። ያንተ እያረረ የሰው በማማሰል አትጠመድ። ምንምያህል ደግና መልካም ሰው ብትሆን ራስን ከማዳን የሚቀድም ሌላ በጎ ስራ እንደሌለህ አስታውስ።
ሳታስቡት ቀን ይጥላችኋል፣ እንዲሁ ከመቅፅበት ነገሮች ይበላሹባችኋል፣ በአጋጣሚ በሰውም ሆነ በሁኔታዎች ተጎጂ ትሆናላችሁ፣ ብቻችሁን ፊትለፊት መጋፈጥ ላለባችሁ ችግር ትጋለጣላችሁ። አውቃችሁ አልገባችሁበትም ነገር ግን ከዚህ አጣብቂኝ የመውጣት ግዴታ ይኖርባችኋል፣ ፈልጋችሁ አልተፈተናችሁም ነገር ግን ፈተናውን የማለፍ ግዴታ አለባችሁ። ሁሉን ነገር እንደ አመጣጡ የሚመልስ ማንነት በአንዴ አይገነባም፣ ከሁኔታዎች በላይ የሆነ ስብዕና በትንሽ ጊዜ አይመጣም። ልባችሁ ትንሽ ሲሆን በትንሹም በትልቁም ነገር ላይ ለመፍረድ ትቸኩላላችሁ፣ የማስተዋል አቅማችሁ አናሳ ሲሆን ከራሳችሁ በላይ የሰውን ጉድፍና ድክመት መመልከት ትጀምራላችሁ፣ ያልተሰራ ማንነት ሲኖራችሁ ዝቅ ማለትን ትጠየፋላችሁ፣ ንቀትና እብሪት ይነግስባችኋል፣ በሰው ላይ የበላይነታችሁን ለማሳየት ትደክማላችሁ፣ ሁሉም ሰው እንዲወዳችሁና እንዲቀበላችሁ ትጠብቃላችሁ፣ ክፋትን በላቀ ክፋት፣ መጎዳትንም በሌላ ጉዳት ለመመለስና ለመሻር ትሞክራላችሁ። ስታድጉ ሁሉም ነገር ድካም እንደሆነ ይገባችኋል፣ ትንሽ መብሰል ስትጀምሩ ጥሩ ስለሆናችሁ ብቻ የሚወሰድባችሁ ነገር እንደሌለ ትረዳላችሁ።
አዎ! በልብ ግዘፉ፣ በሃሳብ እደጉ፣ ራሳችሁን በማስተዋል አንፁ፣ በትምህርት ከፍ በሉ፣ ለጥበብ ልቦናችሁን ክፈቱ፣ ብስለትን በጊዜ ተለማመዱ። እውቀት ስም ያስጠራል፣ ተፈላጊና ተወዳጅ ያደርጋል፣ ጥበብ ግን ያነግሳል፣ ጥበብ ችግር ፈቺና እንቁ ሰው ያደርጋል። ልባችሁን ለጥበብ ክፈቱ፣ ውስጣችሁን ተነግሮ በማያልቅ መንፈሳዊ እውቀት ሙሉት፣ ሁሉም ሰው የሚመኘውን ፅኑ ማንነት ገንቡ። ማድረግ እየቻላችሁ እናንተን የሚጠቅም ቢሆን አንኳን ሰውን የሚጎዳ ስለሆነ ብቻ የማታደርጉት ነገር ይኑር። ከማንኛውም ሰው ጋር የምትወዳደሩት በሚታየው ስኬት፣ ንብረት ወይም ገንዘብ ሳይሆን፣ በማይታየውና በመልካም ምግባሮች በሚገለጠው ትልቁ ልባችሁ ይሁን። ልባቸው ትልቅ የሆኑ ሰዎች ቅንኖች ናቸው፣ ራሳቸውን የሚያውቁ፣ የሚፈልጉትን የሚያውቁ፣ ህይወትን በተለየ መንገድ የተረዱና እንዴት ክብራቸውን ሳያጡ ከሰው ጋር መኖር እንደሚችሁ የተረዱ ሰዎች ናቸው። ልባችሁን ዘግታችሁ ራሳችሁን አታስጨንቁ፣ ቀለል ብላችሁ ቀላል ህይወት ኑሩ።
አዎ! ጀግናዬ..! በማይሆን መንገድ አዕምሮህን አትወጥረው፣ በአጉል ልክ አልባ የክፋት ሃሳብ ልህን አታስጨንቃት። ትልቅ ሆነህ ትንሽ ስራ አትስራ፣ እያወቅክ በሚያጠፋህ መጥፎ ምግባር አትወጠር። አንተ አሳልፈህ ካልሰጠሀው ያንተን ሰላም የሚቀማህ ሰው የለም፣ አንተ ካልፈቀድክ ማንም ከታላቅነት ማማህ ላይ ሊያወርድህ አይችልም። ለሰው ብዙ አድርገህ ምላሽ የጠበቅበትን ጊዜ አስታውስ፣ አንተ መልካም ሆነ በክፉ ሰዎች የተጎዳህበትን ወቅት አስታውስ፣ ብዙ ሰጥተህ ባዶ እጅህን የቀረበትን ሰዓት አስታውስ። ትልቅ ሰው የሚሰጠው ተቀባዩን ለመጥቀም ሳይሆን ራሱን ለመጥቀም ነው። ካንተ የሆነው ነገር በቅንነት ከሆነ ትልቁ ስጦታህና ሽልማት ውስጣዊ ሃሴት ነው። ልብህ ብሩህ ሆኖ ሳለ የጨለማን ሃሳብ አታስብ፣ ተስፋ እያለህ የተስፋ ቢስ ሰው ተግባርን አትፈፅም። ለሰው ለመድረስ ከመድከምህ በፊት አስቀድመህ ራስህን ከመጥፎ ትርክቶችና ኩናኔዎች አድን። ለራስህ መሆን ሰትችል ለሁሉ መድረስ ትችላለህ፣ ራስህን ሰትጠቅም የምትፈልገውን ሰው መጥቀም ትችላለህ። ያንተ እያረረ የሰው በማማሰል አትጠመድ። ምንምያህል ደግና መልካም ሰው ብትሆን ራስን ከማዳን የሚቀድም ሌላ በጎ ስራ እንደሌለህ አስታውስ።