ራሳችሁን አትግለፁ!
ብዙዎች ምን ያስባሉ? ራሳቸውን ከልክ በላይ ስለገለፁ ሰዎች የሚረዷቸው ይመስላቸዋል፣ ደጋግመው ስለራሳቸው ስላወሩ ሰው የሚቀበላቸው ይመስላቸዋል፣ የራሳቸውን ችግር ሳይፈቱ የሌሎችን መፍታት እንደሚችሉ ያስባሉ። ነገር ግን ያለው እውነት ከዚህ የተለየ ነው። የሰው ልጅ የሚረዳችሁ ብዙ ስላወራችሁ ወይም ብዙ ስለ ለፋችሁ ሳይሆን ሊረዳችሁ ሲፈልግ ብቻ ነው፤ የሰው ልጅ ከጎናችሁ የሚቆመው ስላሳዘናችሁት ወይም ስር ስሩ ስላላችሁ ሳይሆን በአስፈላጊነቱ ሲያምን ብቻ ነው። ከሰው ጋር ባላችሁ ግልፅ ያልሆነ ግንኙነት ምክንያት ራሳችሁን ስቃይ ውስጥ አትክተቱ፣ ከልክ በላይ ብዙ ነገር ከሰው እየጠበቃችሁ ራሳችሁን አታስጨንቁ። የትኛውም ገደብ የሌለው ግንኙነት መጨረሻው መጎዳዳት እንደሆነ አስተውሉ። ማንንም ለመቆጣጠር አትሞክሩ፣ ማንም እንዲቆጣጠራችሁም አትፍቀዱ። ግንኙነት ሊኖራችሁ የሚችለው ከምታውቁት ሰው ጋር ብቻ እንዳልሆነ እወቁ። በየትኛውም ማህበራዊ ሚድያ የምታውቁትን ሰው ከልክ በላይ እየተከተላችሁና በእርሱ ሃሳብ እየተመራችሁ ከሆነ መጨረሻችሁ እንደማያምር አትጠራጠሩ። መቼም ቢሆን የእኔ የምትሉት አመለካከትና አቋም ሊኖራችሁ አይችልም፣ እንዴትም ቢሆን የምትኮሩበት ደረጃ ላይ ልትገኙ አትችሉም።
አዎ! ራሳችሁን አትግለፁ፤ የምታውቁት ሰው ሁሉ እንዲያውቃችሁ አታድርጉ። ፍላጎታችሁን የሚያውቅ፣ ውስጣችሁን የተረዳ፣ የሚያስደስታችሁን ነገር የሚያውቅ ሰው እናንተን ለመቆጣጠር ትልቅ ነገር ማድረግ አይጠበቅበትም። የምትፈልጉትን ያቀርብላችኋል እናንተም የራሳችሁን ህይወት መኖር ትታችሁ እርሱን መከተል ትጀምራላችሁ፣ ትኩረታችሁን ከራሳችሁ ላይ አንስታችሁ አርሱ ላይ ታደርጋላችሁ፣ ሁን ተብሎ ለሚሰጣችሁ ጊዜያዊ ደስታ ብላችሁ የወደፊት ህይወታችሁን መሱዓት ታደርጋላችሁ። ሳታውቁት ትኩረታችሁን እየሸጣችሁት ነው፣ ሳይገባችሁ የሆነ አካል ባሪያ እየሆናችሁ ነው፣ እንዲሁ በደፈናው ወደማታውቁት የህይወት መስመር እየገባችሁ ነው። ማንነታችሁ በታወቀ ቁጥር ለብዙ ሀሳቦች እየተጋለጣችሁ ትመጣላችሁ፣ ፍላጎታችሁን ባሳያችሁ መጠን ተከታይ ብቻ የመሆን እድላችሁ እየሰፋ ይመጣል። በምንም መንገድ ሊያነቁዋችሁና ለተሻለ ስፍራ ሊያበቋችሁ የማይችሉትን ከዛም በላይ የማይመለከቷችሁን ሰዎች ሌትከቀን ትከታተላላችሁ ቦሃላ ግን ራሳችሁን ትወቅሳላችሁ።
አዎ! ጀግናዬ..! አሰየታደንክ ነው፣ እየተፈለክ ነው። "እንዴት? ለምን?" ካልክ ምክንያቱም ሲበዛ ግልፅ ነህ፣ አዕምሮህን አደባባይ አስጥተሀዋል፣ የውስጥ ገመናህን ለማንም አሳይተሃል። የምትታደነውም ለሚሰጥህ ነገር ምንም የማትከፍል ከሆነ የምትሸጠው አንተ ስለሆንክ ነው። ግልፅ መሆን አለብኝ ካልክ የሚጠቅምህን አቋም ብቻ ግለፅ፣ ማንነቴ ሊታወቅ ይገባል ካልክ የሚጥልህን ማንነት አደባባይ አታውጣ። አደጋ ላይ ነህ ራስህን ጠብቅ፣ ህይወትህ በሰው ቁጥጥር ስር እየገባ ነው ፈጥነህ ራስህን አድን። አሁን የፈለከውን ነገር ሁሉ እያደረክ ያለህ ሊመስልህ ይችላል፣ ምናልባትም ዛሬ በምርጫህ እየኖርክ እንደሆነ ሊሰማህ ይችላል ነገር ግን አሁንም እውነታው ካልገባህ ቀስበቀስ ህይወትህ ካንተ ቁጥጥር ስር እየወጣ እንደሆነ አስተውል። ጊዜ አታጥፋ ከእያንዳንዱ ነገር ተማር። ከሰው ተማር፣ ከተፈጥሮ ተማር፣ ከህይወት ተማር፣ አንተን ማዕከል አድርገው ከሚሰሩ ፕሮግራሞች ተማር፣ ዘመንህን ሙሉ በመዝናናትና በጫወታ ጊዜህን አታባክን። ከመጣብህ አደጋ ራስህን አድን፣ በዙሪያህም ላሉት ከለላ ሁናቸው።
ብዙዎች ምን ያስባሉ? ራሳቸውን ከልክ በላይ ስለገለፁ ሰዎች የሚረዷቸው ይመስላቸዋል፣ ደጋግመው ስለራሳቸው ስላወሩ ሰው የሚቀበላቸው ይመስላቸዋል፣ የራሳቸውን ችግር ሳይፈቱ የሌሎችን መፍታት እንደሚችሉ ያስባሉ። ነገር ግን ያለው እውነት ከዚህ የተለየ ነው። የሰው ልጅ የሚረዳችሁ ብዙ ስላወራችሁ ወይም ብዙ ስለ ለፋችሁ ሳይሆን ሊረዳችሁ ሲፈልግ ብቻ ነው፤ የሰው ልጅ ከጎናችሁ የሚቆመው ስላሳዘናችሁት ወይም ስር ስሩ ስላላችሁ ሳይሆን በአስፈላጊነቱ ሲያምን ብቻ ነው። ከሰው ጋር ባላችሁ ግልፅ ያልሆነ ግንኙነት ምክንያት ራሳችሁን ስቃይ ውስጥ አትክተቱ፣ ከልክ በላይ ብዙ ነገር ከሰው እየጠበቃችሁ ራሳችሁን አታስጨንቁ። የትኛውም ገደብ የሌለው ግንኙነት መጨረሻው መጎዳዳት እንደሆነ አስተውሉ። ማንንም ለመቆጣጠር አትሞክሩ፣ ማንም እንዲቆጣጠራችሁም አትፍቀዱ። ግንኙነት ሊኖራችሁ የሚችለው ከምታውቁት ሰው ጋር ብቻ እንዳልሆነ እወቁ። በየትኛውም ማህበራዊ ሚድያ የምታውቁትን ሰው ከልክ በላይ እየተከተላችሁና በእርሱ ሃሳብ እየተመራችሁ ከሆነ መጨረሻችሁ እንደማያምር አትጠራጠሩ። መቼም ቢሆን የእኔ የምትሉት አመለካከትና አቋም ሊኖራችሁ አይችልም፣ እንዴትም ቢሆን የምትኮሩበት ደረጃ ላይ ልትገኙ አትችሉም።
አዎ! ራሳችሁን አትግለፁ፤ የምታውቁት ሰው ሁሉ እንዲያውቃችሁ አታድርጉ። ፍላጎታችሁን የሚያውቅ፣ ውስጣችሁን የተረዳ፣ የሚያስደስታችሁን ነገር የሚያውቅ ሰው እናንተን ለመቆጣጠር ትልቅ ነገር ማድረግ አይጠበቅበትም። የምትፈልጉትን ያቀርብላችኋል እናንተም የራሳችሁን ህይወት መኖር ትታችሁ እርሱን መከተል ትጀምራላችሁ፣ ትኩረታችሁን ከራሳችሁ ላይ አንስታችሁ አርሱ ላይ ታደርጋላችሁ፣ ሁን ተብሎ ለሚሰጣችሁ ጊዜያዊ ደስታ ብላችሁ የወደፊት ህይወታችሁን መሱዓት ታደርጋላችሁ። ሳታውቁት ትኩረታችሁን እየሸጣችሁት ነው፣ ሳይገባችሁ የሆነ አካል ባሪያ እየሆናችሁ ነው፣ እንዲሁ በደፈናው ወደማታውቁት የህይወት መስመር እየገባችሁ ነው። ማንነታችሁ በታወቀ ቁጥር ለብዙ ሀሳቦች እየተጋለጣችሁ ትመጣላችሁ፣ ፍላጎታችሁን ባሳያችሁ መጠን ተከታይ ብቻ የመሆን እድላችሁ እየሰፋ ይመጣል። በምንም መንገድ ሊያነቁዋችሁና ለተሻለ ስፍራ ሊያበቋችሁ የማይችሉትን ከዛም በላይ የማይመለከቷችሁን ሰዎች ሌትከቀን ትከታተላላችሁ ቦሃላ ግን ራሳችሁን ትወቅሳላችሁ።
አዎ! ጀግናዬ..! አሰየታደንክ ነው፣ እየተፈለክ ነው። "እንዴት? ለምን?" ካልክ ምክንያቱም ሲበዛ ግልፅ ነህ፣ አዕምሮህን አደባባይ አስጥተሀዋል፣ የውስጥ ገመናህን ለማንም አሳይተሃል። የምትታደነውም ለሚሰጥህ ነገር ምንም የማትከፍል ከሆነ የምትሸጠው አንተ ስለሆንክ ነው። ግልፅ መሆን አለብኝ ካልክ የሚጠቅምህን አቋም ብቻ ግለፅ፣ ማንነቴ ሊታወቅ ይገባል ካልክ የሚጥልህን ማንነት አደባባይ አታውጣ። አደጋ ላይ ነህ ራስህን ጠብቅ፣ ህይወትህ በሰው ቁጥጥር ስር እየገባ ነው ፈጥነህ ራስህን አድን። አሁን የፈለከውን ነገር ሁሉ እያደረክ ያለህ ሊመስልህ ይችላል፣ ምናልባትም ዛሬ በምርጫህ እየኖርክ እንደሆነ ሊሰማህ ይችላል ነገር ግን አሁንም እውነታው ካልገባህ ቀስበቀስ ህይወትህ ካንተ ቁጥጥር ስር እየወጣ እንደሆነ አስተውል። ጊዜ አታጥፋ ከእያንዳንዱ ነገር ተማር። ከሰው ተማር፣ ከተፈጥሮ ተማር፣ ከህይወት ተማር፣ አንተን ማዕከል አድርገው ከሚሰሩ ፕሮግራሞች ተማር፣ ዘመንህን ሙሉ በመዝናናትና በጫወታ ጊዜህን አታባክን። ከመጣብህ አደጋ ራስህን አድን፣ በዙሪያህም ላሉት ከለላ ሁናቸው።