መዝሙር፡7
ስለ፡ብንያማዊ፡ሰው፡ስለኩዝ፡ቃል፡ለእግዚአብሔር፡የዘመረው፡የዳዊት፡መዝሙር።
1፤አቤቱ፡አምላኬ፥ባንተ፡ታመንኹ፤ከሚያሳድዱኝ፡ዅሉ፡አድነኝና፡አውጣኝ፥
2፤ነፍሴን፡እንደ፡አንበሳ፡ነጥቀው፡እንዳይሰብሯት፥የሚያድንና፡የሚታደግ፡ሳይኖር።
3፤አቤቱ፡አምላኬ፥እንዲህስ፡ካደረግኹ፥ዐመፃም፡በእጄ፡ቢኖር፥
4፤ክፉ፡ላደረጉብኝም፡ክፉን፡መልሼላቸው፡ብኾን፥ጠላቴንም፡በከንቱ፡ገፍቼው፡ብኾን፥
5፤ጠላት፡ነፍሴን፡ያሳዳ፟ት፡ያግኛትም፥ሕይወቴንም፡በምድር፡ላይ፡ይርገጣት፥ክብሬንም፡በትቢያ፡ላይ፡ያዋርዳት።
6፤አቤቱ፥በመዓትኽ፡ተነሥ፥በጠላቶቼ፡ላይ፡በቍጣ፡ተነሣባቸው፤አቤቱ፡አምላኬ፥ባዘዝኸው፡ትእዛዝ፡ንቃ።
7፤የአሕዛብም፡ጉባኤ፡ይከብ፟ኻል፥በእነርሱም፡ላይ፡ወደ፡ከፍታ፡ተመለስ።
8፤እግዚአብሔር፡በአሕዛብ፡ይፈርዳል፤አቤቱ፥እንደ፡ጽድቄ፡ፍረድልኝ፥እንደ፡የዋህነቴም፡ይኹንልኝ።
9፤የኃጥኣን፡ክፋት፡ይጥፋ፥ጻድቁን፡ግን፡አቅና፤እግዚአብሔር፡ልቡናንና፡ኵላሊትን፡ይመረምራል።
10፤እግዚአብሔር፡የጽድቅ፡ጋሻዬ፡ነው፡ልበ፡ቅኖችን፡የሚያድናቸው።
11፤እግዚአብሔር፡የእውነት፡ዳኛ፡ነው፥ኀይለኛም፡ታጋሽም፡ነው፥ዅልጊዜም፡አይቈጣም።
12፤ባትመለሱ፡ግን፡ሰይፉን፡ይስላል፥ቀስቱን፡ገተረ፡አዘጋጀም፤
13፤የሞት፡መሣሪያንም፡አዘጋጀበት፥ፍላጻዎቹንም፡የሚቃጠሉ፡አደረገ።
14፤እንሆ፥በዐመፃ፡ተጨነቀ፡ጕዳትን፡ፀነሰ፡ኀጢአትንም፡ወለደ።
15፤ጕድጓድን፡ማሰ፡ቈፈረም።ባደረገውም፡ጕድጓድ፡ይወድቃል።
16፤ጕዳቱ፡በራሱ፡ይመለሳል፥ዐመፃውም፡በዐናቱ፡ላይ፡ትወርዳለች።
17፤እግዚአብሔርን፡እንደ፡ጽድቁ፡መጠን፡አመሰግናለኹ፥ለልዑል፡እግዚአብሔርም፡ስም፡እዘምራለኹ።
ስለ፡ብንያማዊ፡ሰው፡ስለኩዝ፡ቃል፡ለእግዚአብሔር፡የዘመረው፡የዳዊት፡መዝሙር።
1፤አቤቱ፡አምላኬ፥ባንተ፡ታመንኹ፤ከሚያሳድዱኝ፡ዅሉ፡አድነኝና፡አውጣኝ፥
2፤ነፍሴን፡እንደ፡አንበሳ፡ነጥቀው፡እንዳይሰብሯት፥የሚያድንና፡የሚታደግ፡ሳይኖር።
3፤አቤቱ፡አምላኬ፥እንዲህስ፡ካደረግኹ፥ዐመፃም፡በእጄ፡ቢኖር፥
4፤ክፉ፡ላደረጉብኝም፡ክፉን፡መልሼላቸው፡ብኾን፥ጠላቴንም፡በከንቱ፡ገፍቼው፡ብኾን፥
5፤ጠላት፡ነፍሴን፡ያሳዳ፟ት፡ያግኛትም፥ሕይወቴንም፡በምድር፡ላይ፡ይርገጣት፥ክብሬንም፡በትቢያ፡ላይ፡ያዋርዳት።
6፤አቤቱ፥በመዓትኽ፡ተነሥ፥በጠላቶቼ፡ላይ፡በቍጣ፡ተነሣባቸው፤አቤቱ፡አምላኬ፥ባዘዝኸው፡ትእዛዝ፡ንቃ።
7፤የአሕዛብም፡ጉባኤ፡ይከብ፟ኻል፥በእነርሱም፡ላይ፡ወደ፡ከፍታ፡ተመለስ።
8፤እግዚአብሔር፡በአሕዛብ፡ይፈርዳል፤አቤቱ፥እንደ፡ጽድቄ፡ፍረድልኝ፥እንደ፡የዋህነቴም፡ይኹንልኝ።
9፤የኃጥኣን፡ክፋት፡ይጥፋ፥ጻድቁን፡ግን፡አቅና፤እግዚአብሔር፡ልቡናንና፡ኵላሊትን፡ይመረምራል።
10፤እግዚአብሔር፡የጽድቅ፡ጋሻዬ፡ነው፡ልበ፡ቅኖችን፡የሚያድናቸው።
11፤እግዚአብሔር፡የእውነት፡ዳኛ፡ነው፥ኀይለኛም፡ታጋሽም፡ነው፥ዅልጊዜም፡አይቈጣም።
12፤ባትመለሱ፡ግን፡ሰይፉን፡ይስላል፥ቀስቱን፡ገተረ፡አዘጋጀም፤
13፤የሞት፡መሣሪያንም፡አዘጋጀበት፥ፍላጻዎቹንም፡የሚቃጠሉ፡አደረገ።
14፤እንሆ፥በዐመፃ፡ተጨነቀ፡ጕዳትን፡ፀነሰ፡ኀጢአትንም፡ወለደ።
15፤ጕድጓድን፡ማሰ፡ቈፈረም።ባደረገውም፡ጕድጓድ፡ይወድቃል።
16፤ጕዳቱ፡በራሱ፡ይመለሳል፥ዐመፃውም፡በዐናቱ፡ላይ፡ትወርዳለች።
17፤እግዚአብሔርን፡እንደ፡ጽድቁ፡መጠን፡አመሰግናለኹ፥ለልዑል፡እግዚአብሔርም፡ስም፡እዘምራለኹ።