7 ቁጥር


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


፯ ቁጥር ሰው የመሆን ሚስጥር መፍቻ
✔በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ 7 ቁጥር 735 ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን በዚህም ቻናል ጠቅለል ተደርጎ የሚዳሰስ እንዲሁም ኢትዮጵያና ሰባት ቁጥርን ከቀደምት አባቶቻችን እውቀት በመጨለፍ ምን እንደሚያገናኛቸው በስፋት የሚዳሰስበት በተጨማሪም ስለ አውሬው ቁጥር፣ስለ መናፍስቶች ድብቅ ሴራ የሚቀርብበት ቻናል በመሆኑ ይህን ቻናል በመቀላቀል በቂ ግንዛቤን ይያዙ !

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


#የበረከት_ጥሪ

ለገጠር አብያተ ክርስቲያናት ድጋፍ ለማድረግ ከየካቲት 23 ጀምሮ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ የመባዕ ሳምንት መርሐ ግብር የማኅበረ ቅዱሳን የወልድያ ወረዳ ማእከል የሙያ ገዳማትና አብነት ትምህርት ቤት ክፍል በዝግጅት ላይ ነው።

የመብዐ ድጋፍ የሚደረግላቸው በተለይ በጉባላፍቶ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሲሆኑ የማስቀደሻ እጣን፣ ጧፍ እና የካህናት አልባሳት እጥረት ያለባቸው በመሆኑ በዚህ የጾም ወቅት የቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቴሌግራም ቻናል አባላት በዚህ የበረከት ሥራዎችን እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።

ለመሳተፍ ፍላጎቱ ያላችሁ፦
               በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
     ማኅበረ ቅዱሳን ወልድያ ወረዳ ማዕከል
       ሙያና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል
                1000334491602

ለበለጠ መረጃ፦ 0938001464 ይደውሉ


በረከትን እናግኝ🙏🙏🙏😍😍😍😍


Forward from: ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
#ቅድስት
#የዐቢይ_ጾም_ሁለተኛ_ሳምንት

የቅድስና ባለቤት የሆነው እርሱ እግዚአብሔር አምላክ ነው። እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እባረክ አይል ቡሩክ ነው። በእርሱ የባሕርይ ቅድስና እኛን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ቡሩክ ሆኖ ባረከን፣ ቅዱስ ሆኖ ቀደሰን፣ሕያው ሆኖ ሕያዋን አደረገን። የጸጋ ቅድስናንም ከእርሱ አገኘን። ቅድስናው የተለየ፣ የከበረ፣ የሚመሰገን፣ የሚሰጥ/የሚያድል፣ የሚያነጻ፣ የሚባርክ እናም የሚያስተሰርይ ስለሆነ እንከን፣ ጉድለት የሌለበት ምሉዕ ነው። ለባለሟሎቹ ቢሰጠው የማይጎድል፣ ተከፍሎ የሌለበት ቅድስና ሆኖ እኛም የቅድስና በጸጋ ተካፋይ ሆነናል።

የተሰጠንን ቅድስና ገንዘብ እንድናደርግ እና እንድንጠቀምበት ደግሞ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በምጽዋትና በሌሎች በጎ ምግባራት መትጋት ይገባናል። ‹‹እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› እንዲል፡፡ (ዘፍ.፪፥፫፣ ዘሌ.፲፱፥፪) የት መሄድ እንዳለብንም በግልጽ ልበ አምላክ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤ ስለ ትምህርትህና ስለ እውነትህ ስምህን አመሰግናለሁ፤ በሁሉ ላይ ቅዱስ ስምህን ከፍ ከፍ አድርገሃልና›› ይላል። (መዝ.፻፴፯÷፪) የተቀደሰን መሥዋዕት በተቀደሰ ቦታ እንፈጽማለን። መቼ ቢሉ፣ በሰንበት፣ በበዓላት በማኅበረ ዐቢይ/ክርስቲያኖች በሚሰበሰቡበት፣ ስመ እግዚአብሔር በሚጠራበት፣ ታቦት  ባለበት፣ እግረ እግዚአብሔር በቆመበት ቅዱስ ስሙን ከፍ ከፍ በማድረግ ቅድስናን ገንዘብ እናደርጋለን።

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለዐቢይ ጾም ሁለተኛው እሑድ በአዘጋጀው ምስጋና አማካኝነት ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ትርጉሙም ‹‹የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች›› ማለት ነው።  (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፯፻፹፬) ቅድስት የሚለው ቃል ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት እንዲሁም ስለ እግዚአብሔር አምላክ ፍጹም ቅድስና የሚያወሳ በመሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክም ፍጥረታቱ የእርሱን ስም በማመስገን ይኖሩ ዘንድ ለቅድስና ሕይወት ፈጥሯቸዋልና በሰንበት እሑድ ክርስቲያኖች የቅድስና ተግባራትን ከሌላው ቀን አብዝተው ይፈጽማሉ፡፡ ዕለት ከተግባር፣ ስም ከክብር የተባበረባት ክብርት ሰንበት ቅድስት ስለሆነች ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት” ብሎ ጠራት። ይኸውም የምትቀድስ፣ ከብራ የምታከብረን፣ አክብረናት የምንከብርባት በመሆኗ ነው።

ለዚህም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓ “ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፤ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ፤ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ፤ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ጸልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ” ትርጉም፦ “ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ስሙንም ጥሩ፤ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው፤ ለስሙም ምስጋናን አቅርቡ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፤ ብል የማያበላሸው ሌባም የማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡ፤ ተዘጋጅታችሁም ተቀመጡ፤ ክርስቶስ ወዳለበት ወደ ላይ አስቡ፡፡“  ስለዚህ ሰው ሰንበትን አክብሮ ጾሞ ጸልዮ፣ ቅድስናን ጠብቆ መኖር እንዲችል እግዚአብሔር የፍቅሩ መገለጫ የሆኑ ትእዛዛቱ ይነግሩናል።

#ቅዱስ_ያሬድም_ወቅቱን “#ቅድስት” ብሎ ሲሰይም፦

፩. #የአርባ_ቀን_ጾም_መጀመሪያ_በመሆኑ፦ ዕለቱ ከዐቢይ ጾም ቀናት ውስጥ አርባው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም መጀመሪያ ስለሆነች፣

፪. #ቅድስት_ሰንበት_ላይ_በመዋሉ፣ እንግዲህ “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” ተብሏል፡፡ (ዘፀ.፳፥፰) የሰንበትን ቀን አስቀድሞ የቀደሰ የባረከ ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው፤ ቀደሰውም፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና፡፡” (ዘፍ.፪፥፫)

“ከምእመናን ወገን አንድስ እንኳን በእሑድ ቀን ለገንዘብ መትጋት፣ ገንዘቤን አምጣ ብሎ መጣላት እና ዋስ መያዝ አይገባውም። ሁሉም ምእመናን ወደ ቤተ ክርስቲያን በንጽሕና በትሕትና ሆነው። ዳኛ ግብሬን፣ አበዳሪ ብድሬን፣ ኤጲስ ቆጶስ ዐሥራት በኵራት፣ ነጋ ድራስ ቀረጥ አምጡ ይሉናል ብለው ሳይፈሩ ይምጡ።

፫. #ወቅቱ_ወርኃ_ጾም_በመሆኑ፦ ምእመናን ይህንን ወቅት በጾም፣ በጸሎት፣ በእንባ፣ በስግደት፣ በአርምሞ፣ በመልካም ሥራ ቅድስናን የምናገኝበት፣ ጊዜው ሰው ወደ እግዚአብሔር አብዝቶ የሚተጋበት ወቅት በመሆኑ፣ ለእግዚአብሔር የሚገባ ነገር ለማድረግ የነገር ሁሉ መጀመሪያ፣ ለመልካም ነገር መነሻው በቅድስና በንጹሕ ልቡና መቅረብ ስለሆነ ቅድስት ብሏታል።  “እስመ ጾም እማ ለጸሎት ወእኅታ ለአርምሞ ወነቅዓ ለአንብዕ መቅድመ ኩሉ ግብር ሠናይት፤ ጾም ማለት የጸሎት እናት፣ የትሕትና እኅት፣ የእንባ ምንጭ፣የመልካም ሥራ ሁሉ መጀመሪያ ናት” እንዳለው ቅዱስ ያሬድ። ”ጾምን ቀድሱ፤ ጉባኤውንም ዐውጁ” የተባልን የተሰጠንን የጸጋ ቅድስና በእጃችን ላይ መኖሩን አመላካች ቃል ነው። (ኢዩ.፩፥፲፬)

፬. #የወንጌል_ትእዛዝ_በመሆኑ፡ ዕለቱን ተጠቅሞ ዓለምን አስተምሮበታል። “ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ”  ትርጉም፡- “ይህች ዕለት እግዚአብሔር የሠራት ቀን  ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።” (መዝ.፻፲፯፥፳፬) ቅዱስ ዮሐንስም በራእዩ ሰንበት የጌታ ቀን ስለመሆኗ እንዲህ ይላል፤ “በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ፡፡” (ራእ. ፩፥፲)

ሊቃውንቱ በፍትሐ ነገሥት “ተጋብኡ ኵሎ ዕለት ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወፈድፋደሰ በዕለተ ሰንበት ወበበዓላት ወበዕለተ ትንሣኤ ዘውእቱ ዕለተ እሑድ” ትርጉም፦ “ሁልጊዜ በቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ፤ ይልቁንም በዕለተ እሑድ፣ በዕለተ ቀዳሚት፣ በጌታ በዓላት ወደ ቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ” በማለት አዘውናል፡፡ (ፍትሐ ነገሥት፣ ገጽ ፪፶፬)

በትጋት ጾመን፣ ጸልየን ርስቱን እንድንወርስ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃ፤ የቅዱሳን በረከት ይጠብቀን።

የዕለቱ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)፦ ግነዩ ለእግዚአብሔር

#ምንባባት
➛ ፩ኛ ተሰ.፬÷፩-፲፫
➛ ፩ኛ ጴጥ.፩÷፲፫-ፍጻ.
➛ ሐዋ. ፲÷፲፯-፴

#ምስባክ
“እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ::
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ፣
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ፤

(እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፡፡ እምነትና በጎነት በፊቱ፣ ቅድስናና የክብር ገናናነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው፡፡”
(መዝ.፺፭÷፭)

#ወንጌል
(ማቴ.፮÷፲፮-፳፭)

#ቅዳሴ
ዘኤጲፋንዮስ 

(ማኅበረ ቅዱሳን)


ዛሬ በዳዊት ከተማ እርሱ መድሀኒት የሆነ ክርስቶስ ተወልዶላችሁዋል ! ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ...!

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን‎🙏🙏🙏🙏😍😍😍😍😍


#ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል








እግዚአብሔር በቃሉ አንፆ በሞገስ ያሳድግህ
አሜን
@sebat_kutr✝✝✝✝


መዝሙር፡7
 
ስለ፡ብንያማዊ፡ሰው፡ስለኩዝ፡ቃል፡ለእግዚአብሔር፡የዘመረው፡የዳዊት፡መዝሙር።
 
1፤አቤቱ፡አምላኬ፥ባንተ፡ታመንኹ፤ከሚያሳድዱኝ፡ዅሉ፡አድነኝና፡አውጣኝ፥
2፤ነፍሴን፡እንደ፡አንበሳ፡ነጥቀው፡እንዳይሰብሯት፥የሚያድንና፡የሚታደግ፡ሳይኖር።
3፤አቤቱ፡አምላኬ፥እንዲህስ፡ካደረግኹ፥ዐመፃም፡በእጄ፡ቢኖር፥
4፤ክፉ፡ላደረጉብኝም፡ክፉን፡መልሼላቸው፡ብኾን፥ጠላቴንም፡በከንቱ፡ገፍቼው፡ብኾን፥
5፤ጠላት፡ነፍሴን፡ያሳዳ፟ት፡ያግኛትም፥ሕይወቴንም፡በምድር፡ላይ፡ይርገጣት፥ክብሬንም፡በትቢያ፡ላይ፡ያዋርዳት።
6፤አቤቱ፥በመዓትኽ፡ተነሥ፥በጠላቶቼ፡ላይ፡በቍጣ፡ተነሣባቸው፤አቤቱ፡አምላኬ፥ባዘዝኸው፡ትእዛዝ፡ንቃ።
7፤የአሕዛብም፡ጉባኤ፡ይከብ፟ኻል፥በእነርሱም፡ላይ፡ወደ፡ከፍታ፡ተመለስ።
8፤እግዚአብሔር፡በአሕዛብ፡ይፈርዳል፤አቤቱ፥እንደ፡ጽድቄ፡ፍረድልኝ፥እንደ፡የዋህነቴም፡ይኹንልኝ።
9፤የኃጥኣን፡ክፋት፡ይጥፋ፥ጻድቁን፡ግን፡አቅና፤እግዚአብሔር፡ልቡናንና፡ኵላሊትን፡ይመረምራል።
10፤እግዚአብሔር፡የጽድቅ፡ጋሻዬ፡ነው፡ልበ፡ቅኖችን፡የሚያድናቸው።
11፤እግዚአብሔር፡የእውነት፡ዳኛ፡ነው፥ኀይለኛም፡ታጋሽም፡ነው፥ዅልጊዜም፡አይቈጣም።
12፤ባትመለሱ፡ግን፡ሰይፉን፡ይስላል፥ቀስቱን፡ገተረ፡አዘጋጀም፤
13፤የሞት፡መሣሪያንም፡አዘጋጀበት፥ፍላጻዎቹንም፡የሚቃጠሉ፡አደረገ።
14፤እንሆ፥በዐመፃ፡ተጨነቀ፡ጕዳትን፡ፀነሰ፡ኀጢአትንም፡ወለደ።
15፤ጕድጓድን፡ማሰ፡ቈፈረም።ባደረገውም፡ጕድጓድ፡ይወድቃል።
16፤ጕዳቱ፡በራሱ፡ይመለሳል፥ዐመፃውም፡በዐናቱ፡ላይ፡ትወርዳለች።
17፤እግዚአብሔርን፡እንደ፡ጽድቁ፡መጠን፡አመሰግናለኹ፥ለልዑል፡እግዚአብሔርም፡ስም፡እዘምራለኹ።
 


መዝሙር፡6



ለመዘምራን፡አለቃ፡በበገናዎች፡ስለ፡ስምንተኛ፤የዳዊት፡መዝሙር።



1፤አቤቱ፥በቍጣኽ፡አትቅሠፈኝ፥በመዓትኽም፡አትገሥጸኝ።

2፤ድውይ፡ነኝና፡አቤቱ፥ማረኝ፤ዐጥንቶቼ፡ታውከዋልና፥ፈውሰኝ።

3፤ነፍሴም፡እጅግ፡ታወከች፤አንተም፡አቤቱ፥እስከ፡መቼ፡ድረስ፡ነው፧

4፤አቤቱ፥ተመለስ፡ነፍሴንም፡አድናት፥ስለ፡ቸርነትኽም፡አድነኝ።

5፤በሞት፡የሚያስብኽ፡የለምና፥በሲኦልም፡የሚያመሰግንኽ፡ማን፡ነው፧

6፤በጭንቀቴ፡ደክሜያለኹ፤ሌሊቱን፡ዅሉ፡ዐልጋዬን፡ዐጥባለኹ፥በዕንባዬም፡መኝታዬን፡አርሳለኹ።

7፤ዐይኔ፡ከቍጡ፡ዕንባ፡የተነሣ፡ታወከች፤ከጠላቶቼ፡ዅሉ፡የተነሣ፡አረጀኹ።

8፤ዐመፃን፡የምታደርጉ፡ዅሉ፥ከእኔ፡ራቁ፥እግዚአብሔር፡የልቅሶዬን፡ቃል፡ሰምቷልና።

9፤እግዚአብሔር፡ልመናዬን፡ሰማኝ፤እግዚአብሔር፡ጸሎቴን፡ተቀበለ።

10፤ጠላቶቼ፡ዅሉ፡ይፈሩ፡እጅግም፡ይጐስቍሉ፤ወደ፡ዃላቸው፡ይመለሱ፥በፍጥነትም፡ይፈሩ።

@delikamedia
@sebat_kutr


መዝሙር፡4
 
ለመዘምራን፡አለቃ፡በበገናዎች፤የዳዊት፡መዝሙር።
 
1፤የጽድቄ፡አምላክ፡በጠራኹት፡ጊዜ፡መለሰልኝ፥በጭንቀቴም፡አሰፋኽልኝ፤ማረኝ፥ጸሎቴንም፡ስማ።
2፤እናንት፡የሰው፡ልጆች፥እስከ፡መቼ፡ድረስ፡ልባችኹን፡ታከብዳላችኹ፧
3፤እግዚአብሔር፡በጻድቁ፡እንደ፡ተገለጠ፡ዕወቁ፤እግዚአብሔር፡ወደ፡ርሱ፡በተጣራኹ፡ጊዜ፡ይሰማኛል።
4፤ተቈጡ፥ነገር፡ግን፥ኀጢአትን፡አታድርጉ፤በመኝታችኹ፡ሳላችኹ፡በልባችኹ፡ዐስቡ፤ዝም፡በሉ።
5፤የጽድቅን፡መሥዋዕት፡ሠዉ፥በእግዚአብሔርም፡ታመኑ።
6፤በጎውን፡ማን፡ያሳየናል፧የሚሉ፡ብዙ፡ናቸው።አቤቱ፥የፊትኽ፡ብርሃን፡በላያችን፡ታወቀ።
7፤በልቤ፡ደስታን፡ጨመርኽ፤ከስንዴ፡ፍሬና፡ከወይን፡ከዘይትም፡ይልቅ፡በዛ።
8፤በሰላም፡እተኛለኹ፡አንቀላፋለኹም፤አቤቱ፥አንተ፡ብቻኽን፡በእምነት፡አሳድረኸኛልና።

@delilamedia
@sebat_kutr


“ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም ለዘይጼውዖ
ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብስተ ሕይወት ለዘይበልዖ፤
ኢየሱስ ክርስቶስ ጽዋዐ መድኀኒት ለዘይሰትዮ፤
ኢየሱስ ክርስቶስ በግዐ መድኀኒት ለዘይሠውዖ ከመ ይባርኩነ ይፈኑ አርዳኦ ለጸባኢነ ይጽብኦ ወልታሁ ነሢኦ”
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠራው ስሙ ጣፋጭ ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚበላው የሕይወት እንጀራ ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠጣው የመድኃኒት ጽዋ ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚሠዋው የድኅነት በግ ነው፤ ይባርኩን ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን ይላክ፤ ጋሻውን አንሥቶ የሚጣላንን ይጣላው
ተአምረ ኢየሱስ





15 last posts shown.