ኤርትራውያን ከኢትዮጵያ ለመውጣት እስከ 4ሺህ ዶላር የሚደርስ የተጋነነ ክፍያ እንደሚጠየቁ ገለጹ!
በኢትዮጵያ የሚኖሩ ኤርትራውያን ወደ ሌሎች ሀገራት ለመሄድ ሲፈልጉ የመውጫ ቪዛ ለማስመታት እስከ 4ሺህ ዶላር የሚደርስ የተጋነነ ክፍያ እየተጠየቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።የክፍያው ምክንያት ግልፅ እንዳልኾነና ወጥነትም እንደሌለው የተናገሩት ኤርትራውያኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የክፍያውን መጠን ዳግም እንዲመለከተው መጠየቃቸውን የአሜሪካ ድምጽ ዘግቧል።
የኢሚግሬሽና ዜግነት አገልግሎት በበኩሉ፣ እየተጠየቀ ያለው ክፍያ፣ ለመውጫ ቪዛ ሳይሆን፣ በሕገወጥ መንገድ ለቆዩበት ጊዜ የሚወሰን ቅጣት ነው ማለቱን ዘገባው አመላክቷል፡፡ክፍያው በኤርትራውያን ስደተኞች ላይ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ሃገራት ዜጎች ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆን የተቋሙ የውጭ ዜጎች ምዝገባና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ አዳነ ደበበ ገልጸዋል።
አክለውም ክፍያው የውጭ አገር ዜጎቹ በኢትዮጵያ የሚቆዩበት ጊዜ በጨመረ ቁጥር ክፍያውም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በህገወጥ መንገድ፣ በሀገሪቱ ውስጥ እየኖሩ ያሉ የውጭ ሀገራት ዜጎች፣ በተቋሙ ተመዝግበው ህጋዊ የመኖሪያ ሰነድ እንዲይዙም አሳስበዋል።
Via_VoA
@Addis_News
@Addis_News
በኢትዮጵያ የሚኖሩ ኤርትራውያን ወደ ሌሎች ሀገራት ለመሄድ ሲፈልጉ የመውጫ ቪዛ ለማስመታት እስከ 4ሺህ ዶላር የሚደርስ የተጋነነ ክፍያ እየተጠየቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።የክፍያው ምክንያት ግልፅ እንዳልኾነና ወጥነትም እንደሌለው የተናገሩት ኤርትራውያኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የክፍያውን መጠን ዳግም እንዲመለከተው መጠየቃቸውን የአሜሪካ ድምጽ ዘግቧል።
የኢሚግሬሽና ዜግነት አገልግሎት በበኩሉ፣ እየተጠየቀ ያለው ክፍያ፣ ለመውጫ ቪዛ ሳይሆን፣ በሕገወጥ መንገድ ለቆዩበት ጊዜ የሚወሰን ቅጣት ነው ማለቱን ዘገባው አመላክቷል፡፡ክፍያው በኤርትራውያን ስደተኞች ላይ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ሃገራት ዜጎች ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆን የተቋሙ የውጭ ዜጎች ምዝገባና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ አዳነ ደበበ ገልጸዋል።
አክለውም ክፍያው የውጭ አገር ዜጎቹ በኢትዮጵያ የሚቆዩበት ጊዜ በጨመረ ቁጥር ክፍያውም እንደሚጨምር ጠቅሰው፤ በህገወጥ መንገድ፣ በሀገሪቱ ውስጥ እየኖሩ ያሉ የውጭ ሀገራት ዜጎች፣ በተቋሙ ተመዝግበው ህጋዊ የመኖሪያ ሰነድ እንዲይዙም አሳስበዋል።
Via_VoA
@Addis_News
@Addis_News