ዛሬ ላይ ዐበይት ክርስትና በሚባሉት በካቶሊክ፣ በምሥራቅ ኦርቶዶክስ"Eastern Orthodox" እና በጽባሕ ኦርቶዶክስ"Oriental Orthodox" ለመላእክት፣ ለነቢያት፣ ለጻድቃን እና ለሰማዕታት "የአክሮት ስግደት" እየተባለ የሚሰገደው ስግደት ጸሎት፣ ልመና፣ ተማጽኖ ስላለበት የአምልኮ ስግደት ነው፥ ምክንያቱም ዱዓእ እራሱ ዒባዳህ ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 2
አን-ኑዕማን ኢብኑ በሺር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ "ዱዓእ ዒባዳህ ነው"። عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ” إِنَّ الدُّعَاءَ هُوَ الْعِبَادَةُ ” .
"ዱዓእ" دُعَآء የሚለው ቃል “ደዓ” دَعَا ማለትም “ለመነ” “ጠራ” “ጸለየ” “ተማጸነ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ልመና” “ጥሪ” “ጸሎት” “ተማጽንዖ” ማለት ነው፥ ከፈጠረን አምላክ ከአሏህ ውጪ "ድረሱልን እርዱን" የሚባሉት ፍጡራን ሁሉን ቻይ፣ ሁሉን ዐዋቂ፣ ሁሉን ሰሚ እና ሁሉን ተመልካች መለኮት ስላልሆኑ አያውቁም፣ አይሰሙም፣ አያዩም፦
7፥194 እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትጠሯቸው እንደ እናንተ አምላኪዎች ናቸው፥ እውነተኞችም እንደሆናችሁ ጥሩዋቸው ለእናንተ ይመልሱላችሁ። إِنَّ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ عِبَادٌ أَمْثَالُكُمْ ۖ فَادْعُوهُمْ فَلْيَسْتَجِيبُوا لَكُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ
46፥5 እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስም ለእርሱ የማይመልስለትን ከአሏህ ሌላ ከሚጠራ ሰው ይበልጥ የተሳሳተ ማነው? እነርሱም ከጥሪያቸው ዘንጊዎች ናቸው፡፡ وَمَنْ أَضَلُّ مِمَّن يَدْعُو مِن دُونِ اللَّهِ مَن لَّا يَسْتَجِيبُ لَهُ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ وَهُمْ عَن دُعَائِهِمْ غَافِلُونَ
በትንሣኤ ቀን አሏህ ከእርሱ ሌላ በዱዓእ የሚያመልኳቸውንም ይሰበስብና እያወቁ «እናንተ እነዚህን ባሮቼን አሳሳታችሁን ወይስ እነርሱው መንገድን ሳቱ?» ብሎ ይጠይቃቸዋል፦
25፥17 እነርሱን እና ከአሏህ ሌላ የሚያመልኳቸውንም የሚሰበስብባቸውንና «እናንተ እነዚህን ባሮቼን አሳሳታችሁን ወይስ እነርሱው መንገድን ሳቱ?» የሚልበትን ቀን አስታውስ፡፡ وَيَوْمَ يَحْشُرُهُمْ وَمَا يَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ فَيَقُولُ أَأَنتُمْ أَضْلَلْتُمْ عِبَادِي هَـٰؤُلَاءِ أَمْ هُمْ ضَلُّوا السَّبِيلَ
25፥18 «ጥራት ይገባህ፤ ከአንተ ሌላ ረዳቶችን ልንይዝ ለእኛ ተገቢያችን አልነበረም፥ ግን እነርሱን እና አባቶቻቸውን መገንዘብን እስከተዉ ድረስ አጣቀምካቸው፡፡ ጠፊ ሕዝቦችም ኾኑ» ይላሉ፡፡ قَالُوا سُبْحَانَكَ مَا كَانَ يَنبَغِي لَنَا أَن نَّتَّخِذَ مِن دُونِكَ مِنْ أَوْلِيَاءَ وَلَـٰكِن مَّتَّعْتَهُمْ وَآبَاءَهُمْ حَتَّىٰ نَسُوا الذِّكْرَ وَكَانُوا قَوْمًا بُورًا
35፥14 ብትጠሩዋቸው ጥሪያችሁን አይሰሙም፡፡ ቢሰሙም ኖሮ ለእናንተ አይመልሱላችሁም? በትንሣኤም ቀን ማጋራታችሁን ይክዳሉ፡፡ እንደ ውስጠ ዐዋቂው ማንም አይነግርህም፡፡ إِن تَدْعُوهُمْ لَا يَسْمَعُوا دُعَاءَكُمْ وَلَوْ سَمِعُوا مَا اسْتَجَابُوا لَكُمْ ۖ وَيَوْمَ الْقِيَامَةِ يَكْفُرُونَ بِشِرْكِكُمْ ۚ وَلَا يُنَبِّئُكَ مِثْلُ خَبِيرٍ
መላእክት፣ ነቢያት፣ ጻድቃን እና ሰማዕታት በትንሣኤም ቀን ማጋራታቸውን ይክዳሉ፥ ከእነርሱ ስም በስተኃላ አምልኮውን የሚጋሩት ሸያጢን ናቸው።
ክርስቲያኖች ሆይ! "የአክሮት ስግደት" እያላችሁ የምሰግዱት ስግደት ጸሎት፣ ልመና፣ ተማጽኖ ስላለበት የአምልኮ ስግደት ነውና የአምልኮ ሐቅ ገንዘቡ የሆነውን አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 2
አን-ኑዕማን ኢብኑ በሺር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ "ዱዓእ ዒባዳህ ነው"። عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ” إِنَّ الدُّعَاءَ هُوَ الْعِبَادَةُ ” .
"ዱዓእ" دُعَآء የሚለው ቃል “ደዓ” دَعَا ማለትም “ለመነ” “ጠራ” “ጸለየ” “ተማጸነ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ልመና” “ጥሪ” “ጸሎት” “ተማጽንዖ” ማለት ነው፥ ከፈጠረን አምላክ ከአሏህ ውጪ "ድረሱልን እርዱን" የሚባሉት ፍጡራን ሁሉን ቻይ፣ ሁሉን ዐዋቂ፣ ሁሉን ሰሚ እና ሁሉን ተመልካች መለኮት ስላልሆኑ አያውቁም፣ አይሰሙም፣ አያዩም፦
7፥194 እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትጠሯቸው እንደ እናንተ አምላኪዎች ናቸው፥ እውነተኞችም እንደሆናችሁ ጥሩዋቸው ለእናንተ ይመልሱላችሁ። إِنَّ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ عِبَادٌ أَمْثَالُكُمْ ۖ فَادْعُوهُمْ فَلْيَسْتَجِيبُوا لَكُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ
46፥5 እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስም ለእርሱ የማይመልስለትን ከአሏህ ሌላ ከሚጠራ ሰው ይበልጥ የተሳሳተ ማነው? እነርሱም ከጥሪያቸው ዘንጊዎች ናቸው፡፡ وَمَنْ أَضَلُّ مِمَّن يَدْعُو مِن دُونِ اللَّهِ مَن لَّا يَسْتَجِيبُ لَهُ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ وَهُمْ عَن دُعَائِهِمْ غَافِلُونَ
በትንሣኤ ቀን አሏህ ከእርሱ ሌላ በዱዓእ የሚያመልኳቸውንም ይሰበስብና እያወቁ «እናንተ እነዚህን ባሮቼን አሳሳታችሁን ወይስ እነርሱው መንገድን ሳቱ?» ብሎ ይጠይቃቸዋል፦
25፥17 እነርሱን እና ከአሏህ ሌላ የሚያመልኳቸውንም የሚሰበስብባቸውንና «እናንተ እነዚህን ባሮቼን አሳሳታችሁን ወይስ እነርሱው መንገድን ሳቱ?» የሚልበትን ቀን አስታውስ፡፡ وَيَوْمَ يَحْشُرُهُمْ وَمَا يَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ فَيَقُولُ أَأَنتُمْ أَضْلَلْتُمْ عِبَادِي هَـٰؤُلَاءِ أَمْ هُمْ ضَلُّوا السَّبِيلَ
25፥18 «ጥራት ይገባህ፤ ከአንተ ሌላ ረዳቶችን ልንይዝ ለእኛ ተገቢያችን አልነበረም፥ ግን እነርሱን እና አባቶቻቸውን መገንዘብን እስከተዉ ድረስ አጣቀምካቸው፡፡ ጠፊ ሕዝቦችም ኾኑ» ይላሉ፡፡ قَالُوا سُبْحَانَكَ مَا كَانَ يَنبَغِي لَنَا أَن نَّتَّخِذَ مِن دُونِكَ مِنْ أَوْلِيَاءَ وَلَـٰكِن مَّتَّعْتَهُمْ وَآبَاءَهُمْ حَتَّىٰ نَسُوا الذِّكْرَ وَكَانُوا قَوْمًا بُورًا
35፥14 ብትጠሩዋቸው ጥሪያችሁን አይሰሙም፡፡ ቢሰሙም ኖሮ ለእናንተ አይመልሱላችሁም? በትንሣኤም ቀን ማጋራታችሁን ይክዳሉ፡፡ እንደ ውስጠ ዐዋቂው ማንም አይነግርህም፡፡ إِن تَدْعُوهُمْ لَا يَسْمَعُوا دُعَاءَكُمْ وَلَوْ سَمِعُوا مَا اسْتَجَابُوا لَكُمْ ۖ وَيَوْمَ الْقِيَامَةِ يَكْفُرُونَ بِشِرْكِكُمْ ۚ وَلَا يُنَبِّئُكَ مِثْلُ خَبِيرٍ
መላእክት፣ ነቢያት፣ ጻድቃን እና ሰማዕታት በትንሣኤም ቀን ማጋራታቸውን ይክዳሉ፥ ከእነርሱ ስም በስተኃላ አምልኮውን የሚጋሩት ሸያጢን ናቸው።
ክርስቲያኖች ሆይ! "የአክሮት ስግደት" እያላችሁ የምሰግዱት ስግደት ጸሎት፣ ልመና፣ ተማጽኖ ስላለበት የአምልኮ ስግደት ነውና የአምልኮ ሐቅ ገንዘቡ የሆነውን አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም