"የመንግስት ተቋማት ፊት ለፊት የሚገኙ የመርካቶ ነጋዴዎች ላይ ብቻ ነው ቁጥጥር ያደረጉት” ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ማክሰኞ ህዳር 10 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) የመንግስት ተቋማት ቁጥጥራቸውን ፊት ለፊት የሚገኙ የመርካቶ ነጋዴዎች ላይ ብቻ ማድረጋቸውን እንደ ትልቅ ክፍተት አግኝተነዋል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
ከንቲባዋ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ አንደኛ መደበኛ ጉባኤ የበጀት ዓመቱን የሶስት ወራት የስራ አፈፃፀም በቀረበበት ወቅት ነው።
በጉባኤው በዋነኝነት ጥያቄ ካስነሱ ጉዳዮች መካከልም፣ በመርካቶ ገበያ ከሰሞኑ በደረሰኝ ከመገበያየት ጋር የተነሱ አለመግባባቶች ነበር።
ከንቲባዋ መርካቶን ዳግም ለማልማት ከመነሳታችን በፊት የተለያዩ ጥናቶች አከናውነናል ያሉ ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ መርካቶ የሀገሪቱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ጀርባ የህገ ወጥ ንግድ መሸሸጊያ ሆኖ በማግኘታችን ነው ብለዋል።
ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት የመንግስት ተቋማት ቁጥጥራቸውን ፊት ለፊት የሚገኙ የመርካቶ ነጋዴዎች ላይ ብቻ ማድረጋቸው እንደሆነ ነው የጠቆሙት።
" ሲነጋ ግብረ ሐይሎች እንዳያገኘን በሚል፣ በሌሊት ትልልቅ ተሸከርካሪዎች ተሰልፈው እቃ ጭነው ለመሄድ ጥረት ይደረጋል። ይህ ሀገርን ይጎዳል። ግብር መክፈል መርህ እስከሆነ፣ ችግሮቻችንን እያሳዩን እና የሚሰርቀውን ለእኛ አሳልፈው እየሰጡ እነርሱም ግድታቸውን መወጣት ነው ያለባቸው።" ሲሉ አስጠንቅቀዋል
@አዲስ ማለዳ
ማክሰኞ ህዳር 10 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) የመንግስት ተቋማት ቁጥጥራቸውን ፊት ለፊት የሚገኙ የመርካቶ ነጋዴዎች ላይ ብቻ ማድረጋቸውን እንደ ትልቅ ክፍተት አግኝተነዋል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
ከንቲባዋ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ አንደኛ መደበኛ ጉባኤ የበጀት ዓመቱን የሶስት ወራት የስራ አፈፃፀም በቀረበበት ወቅት ነው።
በጉባኤው በዋነኝነት ጥያቄ ካስነሱ ጉዳዮች መካከልም፣ በመርካቶ ገበያ ከሰሞኑ በደረሰኝ ከመገበያየት ጋር የተነሱ አለመግባባቶች ነበር።
ከንቲባዋ መርካቶን ዳግም ለማልማት ከመነሳታችን በፊት የተለያዩ ጥናቶች አከናውነናል ያሉ ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ መርካቶ የሀገሪቱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ጀርባ የህገ ወጥ ንግድ መሸሸጊያ ሆኖ በማግኘታችን ነው ብለዋል።
ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት የመንግስት ተቋማት ቁጥጥራቸውን ፊት ለፊት የሚገኙ የመርካቶ ነጋዴዎች ላይ ብቻ ማድረጋቸው እንደሆነ ነው የጠቆሙት።
" ሲነጋ ግብረ ሐይሎች እንዳያገኘን በሚል፣ በሌሊት ትልልቅ ተሸከርካሪዎች ተሰልፈው እቃ ጭነው ለመሄድ ጥረት ይደረጋል። ይህ ሀገርን ይጎዳል። ግብር መክፈል መርህ እስከሆነ፣ ችግሮቻችንን እያሳዩን እና የሚሰርቀውን ለእኛ አሳልፈው እየሰጡ እነርሱም ግድታቸውን መወጣት ነው ያለባቸው።" ሲሉ አስጠንቅቀዋል
@አዲስ ማለዳ