ቀሲስ በላይ መኮንን በአምስት ዓመት ጽኑ እስራት እና በ10 ሺህ ብር ተቀጡ
በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ገንዘብ ለማውጣት በመሞከር የሙስና ወንጀል ክስ የተመሠረተባቸው ቀሲስ በላይ መኮንን በአምስት ዓመት እስራት እና በ10 ሺህ ብር ተቀጡ።
ከቀሲስ በላይ ጋር አንድ ላይ ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ሌሎች ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው የአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት እንደተፈረደባቸው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
የቅጣት ውሳኔውን ያስተላለፈው ሐሙስ ጥር 22/2017 ዓ.ም. የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ መድብ ሦስተኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ጥፋተኛ የተባሉት ግለሰቦች ዐቃቤ ሕግ ክስ የቀረበባቸው የወንጀል ሕጉን እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ተላልፈዋል በሚል ነበር።
ግለሰቦቹ ላይ የተመሠረተው ክስ በአፍሪካ ኅብረት ስም የተዘጋጀ ሐሰተኛ ሰነድ በመጠቀም በኅብረቱ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ስድስት ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማውጣት ሞክረዋል በሚል ነው።
ተከሳሾቹ በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸው ክስ እንዲሻሻል መቃወሚያ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፤ ፍርድ ቤቱ ግን ሳይቀበለው መቅረቱ ይታወሳል። ይህን ተከትሎ ግለሰቦቹ የእምነት ክህደት ቃላቸውን የሰጡ ሲሆን ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ ሦስት ምስክሮችን በችሎት አሰምቷል።
የዐቃቤ ሕግን ማስረጃ የመረመረው ፍርድ ቤቱ የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን ዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ ብይን መስጠቱ ይታወሳል።
ተከሳሾቹ በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸውን ክስ በሚገባ መከላከል ባለማቻላቸው ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ናቸው ሲል ከሁለት ሳምንት በፊት ወስኗል።
ይህን ውሳኔ ተከትሎ በተላለፈው የቅጣት ውሳኔ መሠረት 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በአምስት ዓመት ጽኑ እስራት እና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ቀሪዎቹ ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው በአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት ተወስኖባቸዋል።
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የኦሮሚያ ቤተ ክህነትን ለመመሥረት በነበራቸው እንቅስቃሴ የሚታወቁት ቀሲስ በላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ነበሩ።
በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ገንዘብ ለማውጣት በመሞከር የሙስና ወንጀል ክስ የተመሠረተባቸው ቀሲስ በላይ መኮንን በአምስት ዓመት እስራት እና በ10 ሺህ ብር ተቀጡ።
ከቀሲስ በላይ ጋር አንድ ላይ ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ሌሎች ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው የአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት እንደተፈረደባቸው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
የቅጣት ውሳኔውን ያስተላለፈው ሐሙስ ጥር 22/2017 ዓ.ም. የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ መድብ ሦስተኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ጥፋተኛ የተባሉት ግለሰቦች ዐቃቤ ሕግ ክስ የቀረበባቸው የወንጀል ሕጉን እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ተላልፈዋል በሚል ነበር።
ግለሰቦቹ ላይ የተመሠረተው ክስ በአፍሪካ ኅብረት ስም የተዘጋጀ ሐሰተኛ ሰነድ በመጠቀም በኅብረቱ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ስድስት ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማውጣት ሞክረዋል በሚል ነው።
ተከሳሾቹ በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸው ክስ እንዲሻሻል መቃወሚያ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፤ ፍርድ ቤቱ ግን ሳይቀበለው መቅረቱ ይታወሳል። ይህን ተከትሎ ግለሰቦቹ የእምነት ክህደት ቃላቸውን የሰጡ ሲሆን ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ ሦስት ምስክሮችን በችሎት አሰምቷል።
የዐቃቤ ሕግን ማስረጃ የመረመረው ፍርድ ቤቱ የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን ዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ ብይን መስጠቱ ይታወሳል።
ተከሳሾቹ በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸውን ክስ በሚገባ መከላከል ባለማቻላቸው ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ናቸው ሲል ከሁለት ሳምንት በፊት ወስኗል።
ይህን ውሳኔ ተከትሎ በተላለፈው የቅጣት ውሳኔ መሠረት 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በአምስት ዓመት ጽኑ እስራት እና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ቀሪዎቹ ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው በአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት ተወስኖባቸዋል።
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የኦሮሚያ ቤተ ክህነትን ለመመሥረት በነበራቸው እንቅስቃሴ የሚታወቁት ቀሲስ በላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ነበሩ።