TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

1 Jun, 17:16

Open in Telegram Share Report

እኛን ኢትዮጵያውያንን ጠፍሮ የያዘን ምንድነው?
____
(የባህል አብዮትና መፈንቅለ-አስተሳሰብ እንደ መፍትሄ)

ፀሀፊ -አሰፋ ሀይሉ

ከሃያ ምናምን ዓመታት በፊት ከዩኒቨርሲቲ የመመረቂያ ጥናቴን የሠራሁት በFreedom of Association ላይ ነበረ።

ያ ጥናት በተለይ ሰዎች ፖለቲካዊ ማኅበሮችን የሚፈጥሩበትን ሂደትና በፓርቲ ምሥረታና እንቅስቃሴዎች ላይ ያሏቸውን ነፃነቶችና ገደቦች በዓለም ዙሪያና ባገራችንም across centuries ያሉትን አንኳር እውነቶች ለመዳሰስ የሞከርኩበት ጥናት ነበረ።

የኢትዮጵያችንን በተመለከተ ከእኔ በፊት ጉዳዩን ያጠኑ ጥቂት የውጭና ያገርውስጥ ምሁራን ነበሩ። የሚገርመኝ አንድ ነገር፣ የጥናቶቹ ሁሉ ግኝትና ድምዳሜ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በንጉሡም ዘመን፣ በወታደራዊው ደርግ ዘመንም ሆነ በኢህአዴግ ዘመን፣ (ሌላ ቀርቶ አሁንም ላይ) በአንድ ዓይነት ባህርይ የተቃኘ መሆኑ ነው።

በኢትዮጵያችን ለምን የmultiparty አስተሳሰብ አልዳበረም? ለምን የተቃውሞ ድምፅን ሰብሰብ ብሎ በማኅበር ተደራጅቶ ማሰማት፣ ለጋራ መብት በጋራ መቆም ለምንድነው ኢትዮጵያውያንን የሚያስፈራቸው? ምንድነው የያዘን? የሁሉም፣ የሁላችንም ጥያቄ ነው።

ዋና ታሪካዊ ምንጩ የእኛ የኢትዮጵያውያን አስተሳሰብ ወይም አመለካከት ነው የሚል ነው።

እኛ ኢትዮጵያውያን ሥር-የሰደደ የተገዢነት ስነልቦና ያለን ሕዝቦች ነን! አብረን በጋራ ተደራጅተን መብታችንን ከመጠየቅ የያዘን ነገሬ ጥልቅ የሆነ ሌላን ሰው የሚጠራጠር የወል ሰብዕናችን ነው።

ሥልጣን ካለው ኃይለኛ አካልና ከባለጊዜ ጋር ጫን አድርጎ አፍ መከፋፈት ለቅስፈት ይያርጋል የሚለው ዘመን ያፈጀ የፍርሃት ባህርያችን ነው። እጅግ ጥልቅ መሠረት ያለውና ከዘር ማንዘር የወረደ የአድርባይነት በሽታችን (ባህላችንም) ነው።

የራሳችንን መብት ለመጠየቅ መፍራት ብቻ አይደለም! ሌላውም ከኛ በአቅም ያነሰ ነው የምንለውን ሰውም መብቱን እንዲጠይቀን፣ አሊያም ተቃውሞውን እንዲተነፍስ አንፈቅድለትም።

በድሮ ዘመን ባርያና አሽከር፣ ወይ ጢሰኛ፣ ወይ የቤት ሠራተኛ፣ ወይም የበታች ሠራተኛ መብቴ ነው የሚለውን ወይም ቅር ያለውንና እንዲስተካከልለት የሚሻውን ነገር ከጠየቀን፣ እኛ ኢትዮጵያውያን በመጀመሪያ የሚመጣልን ሃሳብ፣ ጥጋብ ይዞት ነው የሚል ነው።

ተረቶቻችን፣ ምሣሌዎቻችን እና ስነልቦናችን ሁሉ ጥጋበኛን ያወግዛል። የመብት ጥያቄ ሁሉ ከትዕቢት የመነጨ፣ ከመታበይ የመጣ ይመስለናል። ጥጋቡን ሳላስተነፍስለት የቀረሁ እንደሆነ እኔን አያርገኝ እየተባለ ይዛታል! እውር ቢሸፍት እስከ ጓሮ ነው እየተባለ ይዘበታል።

በቅሎ ገመዷን በጠሰች በራሷ አሳጠረች እየተባለ ይሰለቃል። ይቺ ባቄላ ያደረች እንደሆን አትቆረጠምም ይባላል። ለአኩራፊ ቁርሱ ራቱ ይሆናል ይባልለታል።

አጓጉል የረዘመች የማሽላ ዛፍ፣ አንድም ለወፍ አሊያም ለወንጭፍ - እየተባለ ከሰው ተነጥሎ አጉል መንጠራራት ለመቀሰፍ እንደሚዳርግ ይሰበካል። አጉል መንፈራገጥ ለመላላጥ ይባላል፣ ቆማ* ሲጠግብ በትሩን ይወረውራል እየተባለ "ጥጋቡ" መሣለቂያ ይደረጋል።

ንጉሥ አይከሰስ፣ ሠማይ አይታረስ እንላለን። ወንዝ ቁልቁል እንጂ ሽቅብ አይፈስም እንላለን። ወደላይ አንጋጠህ ለበላዮችህ ምን ማድረግ እንዳለባቸው መንገር ድፍረት ነው። ብልግና ነው። ጥጋብ ነው።

እና ዝምታ ወርቅ መሆኑን እንሰበካለን። ዝም ባለ አፍ ዝንብ የማይገባ መሆኑን እንማራለን። በአፍ ይጠፉ በለፈለፉ እየተባለ ይተረታል። ሰው ያመነበትን አውጥቶ እንዳይናገር የሚያሠለጥን የዝጎች ባህል ነው ያለን። መከበር በከንፈር መሆኑን እናምናለን። ኢፍትሃዊነትን ከመጋፈጥ ይልቅ በአድርባይነት የምናገኛት ሽልማት ትናፍቀናለች!

በእነዚህ ከዘር ማንዘር ከወረስናቸው የፖለቲካ ውርዴዎች ይባብሎ ደግሞ፣ በኢትዮጵያችን የመንግሥትነት ሥልጣንን የያዙ ገዢዎች ሁሉ ደግሞ - እስካሁንም ድረስ -  በሥልጣናቸው ላይ ጥያቄ ያነሳባቸውን ማናቸውንም አካል የሚያስተናግዱት - እጅግ አስከፊውን ቅጣት በማከናነብ ነው!

ደፍሮ ሥልጣንን የተቃወመን ሰው ወይም የሰዎች ስብስብ፣ አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ ሌሎች እንዳይነሱ መቀጣጫ ማድረግ ነው ለዘመናት የኖረና ያልለቀቀን ባህላችን። የተቃወመ ሰው የሚቀጣው የራሱን ፋንታ ብቻ አይደለም፣ የሌሎችንም ድርሻ ነው! ሌሎች እሱን አይተው አደብ ገዝተው መቀመጥ አለባቸው።

አፄ ዮሐንስ ያመፁባቸውን ወሎዬዎችና ጎጃሜዎች ወርረው፣ ጨፍጭፈው፣ ዘርፈው፣ አልበቃ ብሏቸው የየሰዉን እጅ ቆራርጠው ይመለሱ ነበር።

አፀ ቴዎድሮስ ሸዋ፣ ጎጃም፣ ወሎ፣ ራሱ ጎንደር ላይ ዘምተው ዘርፈው፣ አቃጥለው፣ ገድለው አላረካ ሲላቸው የሰውን እጅ ሁሉ ቆርጠው ጥለው ይመለሱ ነበረ።

ጎንደር ከተማዋ ሙሉዋን በታሪኳ ሶስት አራት ጊዜ ስትቃጠል፣ አንዴ ዮዲት ጉዲት፣ ግራኝ አህመድ፣ ደርቡሽ፣ እያለ በመጨረሻ ራሳቸው አፄ ቴዎድሮስ ናቸው ሌላ ቦታ ዘምቼ ስመለስ ከድታችሁ ጠበቃችሁኝ ብለው ከተማዋን ያቃጠሏት። ሌላ ቀርቶ እሳቸውን ለመቀበል አበባ ይዘው የወጡ ሴቶች አልቀሯቸውም!

በሃገራችን ሥልጣንን በተቃወሙ ላይ ከሠማይ የአውሮፕላን ጥቃት ማዝነብ የጀመሩት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ናቸው! ደርግ ቀጠለበት! ኢህአዴግ በሄሊኮፕተሮች ያጭድ ነበር ሶማሌ ድረስ ሄዶ።

ይሄኛው የብልፅግናው መንግሥትም በሥልጣኑ ላይ የተነሱበትን የገዛ ወገኖቹን በድሮንና ሔሊኮፕተር ያጭዳል! የዘር ውርስ ነው። የማይለቅ ውርዴያችን ነው የተቃወሙንን ያለምህረት መቅጣት!

ይህ ነገር የሚጀምረው በቤት ውስጥ ከህፃናት አስተዳደግ ጀምሮ ነው! በእኛ ሀገር እስከቅርብ ጊዜ ህፃን ልጅ ከነስሙ አሽከር ነው። ጩሎ ነው። ከቁምነገር የማይጣፍ ነው። እንዲከበር የሆነ ነገር ይዞ ወይ ሠርቶ ማሳየት አለበት። ...

አለበለዚያ በሌላ ሰው ቁጥጥር ስር ነው። የሚቸረው እንጂ የሚጠይቀው መብት የለውም። አለዚያ አይቀጡ ቅጣት ይጠብቀዋል። ሰጥ ለጥ ብሎ ለauthority መገዛትን የምንለማመደው በህፃንነታችን ነው። የታዛዥነት ዓመል የሚያሸልምበት፣ ማጉረምረም የሚያስኮረኩምበት አስተዳደግ ነው ያለን!

ልጅ ፊቱን አይበርደውም፣ ደሃ ሕዝብም አይርበውም! አሽከር መረገጥ አይቆረቁረውም! የምንኖረው በአገዛዞች መልካም ፈቃድ ነው እንጂ፣ እኛ የተገባን ባለመብቶች ሆነን አይደለም!...

እነዚህንና እነዚህን የመሠሉ ሥር የሰደዱ አስተሳሰቦቻችን ናቸው፣ ቢያንስ ያለፈውን በዓለም ሁሉ ንቃት ያላቸው ሕዝቦች በምድራቸው ማንበር የቻሉትን የመናገር፣ የመቃወም፣ የመፃፍ፣ የመሰብሰብ፣ ሠላማዊ ተቃውሞ የማድረግና ለፖለቲካ ወይም ለሥልጣን መያዝ ዓላማ ተሰባስቦ የመደራጀት መብታችንን ማስከበር እንዳንችል ቀፍድደው የያዙን።

በእነዚህ ሁሉ ላይ ደግሞ፣ ህዝቡ ራሱን censor እንዲያደርግ፣ ጥላውን እንኳ እንዳያምን፣ እርስበርሱ እንዳይተማመን የሚያደርጉ የመንግሥት የምሥጢር ወሬ አቀባዮችና ሠላዮች ደግሞ ተመድበውበታል።

ዛሬ አፍህን ከፍተህ በማግሥቱ የለህም! ሃሳቡን ሊያወያይህ የቀረበህ፣ ተናግሮ አናጋሪ ነው። ማንንም አታምንም። ስለሆነም ግፋ ቢል በዘመድ አዝማድና በቅርብ ቤተሰብ ትደራጃለህ።

ለዚህም ነው ባገራችን በ1900ዎቹ የታዩ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በአብዛኛው በአንድ ቤተሰብ አባላት፣ በአንድ ወገን፣ በአንድ ብሔር፣ በአንድ ካዴት ሁሉ ሊሆኑ የበቁት። ማንም ስለማይታመንም፣ ባልንጀራ በየወንዙ ይማማላል። ሲጀመር እንጂ ሲጨረስ የሚታይ ህብረት የለም!

6.7k 0 33 3 39
Catalog
Channels and groups catalog Channels compilations Search for channels Add a channel/group
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
API
API statistics Search API of posts API Callback
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
Read
Академия TGStat Telegram Research 2019 Telegram Research 2021 Telegram Research 2023
Contacts
Справочный центр Support Email Jobs
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot