በሚጠቅምህ ነገር ላይ ብቻ መሽሁል ሁን!!إحرص على ما ينفعك


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
👉 ከቁርኣን፣
👉ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
👉 ከታማኝ ዑለማዎችና
👉ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ  @Abu_Sibewe ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ስም ማጥፋት የምቀኞች መዳረሻ
     ትልቅ መንገዳቸው ነው። ."
https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


ለአሏህ መንገር #ትተን ለሰው ነገርንና ...
ገር የነበረው ተመልሶ ጠና!!

https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


Forward from: በሚጠቅምህ ነገር ላይ ብቻ መሽሁል ሁን!!إحرص على ما ينفعك
👉አንዳንድ ገጠመኞች አሉ
ልክ እንደ እርሳስ ቀለም ጠርገን እንዳልነበሩ ምናደርጋቸው።
አንዳንድ ገጠመኞች ደግሞ አሉ

👉ልክ እንደ እርሳስ ቀለም ጠራርገው እንዳልነበርን ሚያደርጉን።

አላህ መልካም ለሆነው ይግጠመን
https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


🥬ምላስን መጠበቅ🥬


ምላስህ ነጃ የመውጫህ ሰበብ ነው ወይም ምላስህ የመክሰሪያህ ሰበብ ነው ይለናል ታላቁ አሊም ሸህ አቢ ሙአዝ ሁሴን አልሓጢቢይ حفظه الله


🥦ምላስን መጠበቅ ያሉት ጥቅሞችና ምላስን አለመጠበቅ ያሉት ጉዳቶች ተዳሰዋል ሰምተን እንጠቀም 🥦

https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


አትደንግጡ❗️ይህ ደም የኢየሱስ ስቅለት የሚያሳየው ፊልም ላይ የተወሰደ ነው።

ይህ የኢየሱስ ሳይሆን የአንድ የፊልም አክተር እግር ነው።

በዚያ ዘመን ዲጂታል ከለርድ ካሜራ በጭራሽ አልነበረም።

ኢየሱስን አንድም ከለርድ ፎቶ ያነሳው ሰው የለም።

ክርስቲያኖች የሚያለቅሱት በሆነ አክተር ፊልም እያዩ እንጂ ኢየሱስን አይደለም።


አስቡት እስቲ አምላክ በዚህ ልክ ተቸንክሮ ደም በደም ሲሆን?


ሀሰኑ አል በስሪይ رحمه الله

ወደ እናት ፊት መመልከት በራሱ ዒባዳ
ነው ታድያ ለእርሷ መልካም መዋሉስ
እንዴት ሊሆን ነው ይላሉ።

مسند ابن المبارك👉ምንጭ


🤝
    ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን በሙሉ
:
:
:
:
:
:
:
:
.
.
.
.
.
.
🤲አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ይምራችሁ🤲




የሰው ልጅ አእምሮ የማይቀበለው አባባል

   “ጌታ ለእኛ ሀጥያት ሲል ተሰቀለ¡”

ጌታ የእኛ ሀጥያት ሊምረን ከፈለገ ይምረናል እንጂ ለምን ይሰቀላል⁉️

             منقول








ሱረቱል ካህፍን  የቻለ ይቅራ📖 ያልቻለ ያዳምጥ

በአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) ላይ ሰለዋት ማውረድ እናብዛ
قَالَ ﷺ: «مَنْ صَلَّ عَلَيَّ صَلاةً صَلَّ اللهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشَراً»

https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


ሰባቱ የ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› መስፈርቶች (ሸርጦች)
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ ናበጣም አዛኝ በኾነዉ፦
1.ዕውቀት፡- ይህም ማለት የዚህ ቃል መልዕክት እና ቃሉ ዉድቅ
የሚያደርጋቸዉንና እና የሚያፀድቃቸውን ነገሮች ጠንቅቆ ማወቅ ማለት ነው፡፡
ለዚህም ማስረጃው ቀጣዩ የአላህ ቃል ነው፡፡
ﻭَﻟَﺎ ﻳَﻤْﻠِﻚُ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻳَﺪْﻋُﻮﻥَ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻧِﻪِ ﺍﻟﺸَّﻔَﺎﻋَﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻣَﻦْ ﺷَﻬِﺪَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ
ﺍﻟﺰﺧﺮﻑ : ٨٦
(እነዚያም ከአላህ ሌላ የሚያመልኳቸዉ እነሱ የሚያውቁ ሆነው በእውነት
ከመሰከሩት በስተቀር ምልጃን አይችሉም) አል-ዙኸሩፍ 86
2.እርግጠኛነት፡- በአላህ ብቸኛ አምላክነት ላይ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ መሆን
ነው፡፡አላህ (ሱ.ወ)እንዲህ ይላል፡-
ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺑِﺎﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻪِ ﺛُﻢَّ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﻭَﺟَﺎﻫَﺪُﻭﺍ ﺑِﺄَﻣْﻮَﺍﻟِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻧْﻔُﺴِﻬِﻢْ
ﻓِﻲ ﺳَﺒِﻴﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃُﻭﻟَﺌِﻚَ ﻫُﻢُ ﺍﻟﺼَّﺎﺩِﻗُﻮﻥَ
ﺍﻟﺤﺠﺮﺍﺕ: ١٥
({እዉነተኞቹ} ምእመናን እነዚያ በአላህና በመልእክተኛዉ ያመኑት ከዚያም
ያልተጠረጠሩት ናቸው) አል-ሑጁራት 15
የአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡ ሑረይራ (ረዲየ አላሁ አንሁ) እንዲህ
ብለውታል፡- ‹‹ ከዚህ አጥር በስተጀርባ የአላህን ብቸኛ አምላክነት ከልቡ
በእርግጠኝነት የሚመሰክር ሰው ብታገኝ በጀነት አበስረው፡፡›› ሙስሊም
ዘግበዉታል
3.መቀበል፡- የላኢላሀ ኢለላህን መልእክት (አላህን በብቸኝነት ማምለክን)
ከልብ መቀበልና ለሌላ አካል የሚከናወኑ አምልኮቶችን መተው ነው፡፡ ይህንን
ያልተቀበለ ግን አላህ ኩራተኛነታቸውን እና አለመቀበላቸው እንዲህ በማለት
ከገለፃቸው ሙሽሪኮች መደዳ ይሰለፋል፡፡
ﺇِﻧَّﻬُﻢْ ﻛَﺎﻧُﻮﺍ ﺇِﺫَﺍ ﻗِﻴﻞَ ﻟَﻬُﻢْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺴْﺘَﻜْﺒِﺮُﻭﻥَ
ﺍﻟﺼﺎﻓﺎﺕ: ٣٥ – ٣٦
(እነርሱ፤ ‹ከአላህ ሌላ አምልኮት የሚገባው ሆኖ የሚመለክ አምላክ የለም›
በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበር፡፡ እኛ ለእብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው
ነን ይሉም ነበር፡፡) አልሷፋት 35-36
4.መታዘዝ፡- ይህ ማለት ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› የሚለው የምስክርነት ቃል
ለሚያመላክታቸው ትዕዛዛትና ክልከላዎች ሙሉ ታዛዥ ተከታይና ተናናሽ መሆን
ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡-
ﻭَﻣَﻦْ ﻳُﺴْﻠِﻢْ ﻭَﺟْﻬَﻪُ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﻫُﻮَ ﻣُﺤْﺴِﻦٌ ﻓَﻘَﺪِ ﺍﺳْﺘَﻤْﺴَﻚَ ﺑِﺎﻟْﻌُﺮْﻭَﺓِ ﺍﻟْﻮُﺛْﻘَﻰ ﻭَﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ
ﻋَﺎﻗِﺒَﺔُ ﺍﻟْﺄُﻣُﻮﺭِ
ﻟﻘﻤﺎﻥ : ٢٢
(እርሱ መልካም ሰሪ ሆኖ ፊቱን (በመታዘዝና በመተናነስ) ወደ አላህ የሚሰጥ
ሰው ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ…)
ሉቅማን 22
5. እውነተኝነት፡- የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል በሚሰጥበት ጊዜ
እውነተኛ መሆን ማለት ነው፡፡ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ
‹‹ማንኛውም ከልቡ በእውነተኛነት በአላህ ብቸኛ አምላክነትና በሙሐመድ
(ሰ.ዐ.ወ) መልዕክተኝነት የሚመሰክር ሰው አላህ ከእሳት እርም ይለዋል ››
ቡኻሪ ዘግበዉታል
6. መውደድ፡- ይህ ማለት ላኢላሀ ኢለላህ የሚለውን የምስክርነት ቃል ፣ አላህን
እንዲሁም አላህን በብቸኝነት የሚያመልኩትን የተውሂድ ሰዎችን መውደድ ነው፡፡
አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል ፡-
( ﻭَﻣِﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﻣَﻦْ ﻳَﺘَّﺨِﺬُ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃَﻧْﺪَﺍﺩًﺍ ﻳُﺤِﺒُّﻮﻧَﻬُﻢْ ﻛَﺤُﺐِّ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺃَﺷَﺪُّ
ﺣُﺒًّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ
ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ: ١٦٥
(ከሰዎችም አላህን እንደሚወዱ የሚወዷቸው ኾነው ከአላህ ሌላ ባለንጣዎችን
(ጣዖታትን) የሚይዙ አሉ፡፡ እነዚያ ያመኑትም አላህን በመውደድ (ከነርሱ)
ይበልጥ የበረቱ ናቸው) አል በቀራህ 165
7. ማጥራት፡- ይህም ማለት የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል የሰጠ ሰው
ስራውን ከሽርክ ማጥራት አለበት፡፡ እንዲሁም በዚህ የምስክርነት ቃል የዱንያ
ጥቅማጥቅሞችን ከመከጀል፣ ከይዩልኝ እና ይስሙልኝ መጥራት አለበት፡፡
የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል ‹‹የቂያማ ዕለት የኔን ምልጃ
በማግኘት ዕድለኛ የሚሆነው ላ ኢላሀ ኢለላህን ከልቡ ያለ ሰው ነው፡፡›› ቡኻሪ
ዘግበዉታል

https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


ከተውሂድና ከሱና የራቀ በሙሉ ወደ ሽርክ ፣ ወደ ቢድዐ እንዲሁም ወደ
# ቅጥፈት የቀረበ ነው።
# ሼኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሂመሁላህ

https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


"አስተውሉ! ከመፀፀታችሁ በፊት መልካምን ስራ ፈፅሙ። በዱንያ አትሸወዱ።ምክንያቱም ፦
ጤነኞቿ መታመማቸው ፤ አዲሶቿ ማርጀታቸው፤ ፀጋዎቿ ማለቃቸው ወጣቶቿ ማርጀታቸው አይቀርምና።"
📚【አዙህዱልከቢር ሊልበይሀቂ (1/197)

https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


🔣«የአኼራ መህር ቀላል ነው፤ ኢኽላስ ያለው ልብና አላህን የሚዘክር አደበት።»🔣


قال ابن الجوزي رحمه الله

🛡[بحر الدموع(٨٤)].


Gaza


አላህ ከአርሽ በላይ ስለመሆኑ

የኢማም ማሊክ ድንቅ ምላሽ

ኢስቲዋዕ እንዴት ነው?

ﻗﺎﻝ ﺍﻷﻣﺎﻡ ﻣﺎﻟﻚ ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ -
ﻭ ﻗﺪ ﺳﺌﻞ ﻋﻦ ﻗﻮﻟﻪ ﺗﻌﺎﻟﻰ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﻦُ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟْﻌَﺮْﺵِ ﺍﺳْﺘَﻮَﻯ
ﻛﻴﻒ ﺍﺳﺘﻮﻯ؟
ﻓﻘﺎﻝ ‏« ﺍﻻﺳﺘﻮﺍﺀ ﻏﻴﺮ ﻣﺠﻬﻮﻝ، ﻭﺍﻟﻜﻴﻒ ﻏﻴﺮ ﻣﻌﻘﻮﻝ، ﻭ ﺍﻹﻳﻤﺎﻥ ﺑﻪ ﻭﺍﺟﺐ، ﻭ ﺍﻟﺴﺆﺍﻝ ﻋﻨﻪ ﺑﺪﻋﺔ
ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﻦُ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟْﻌَﺮْﺵِ ﺍﺳْﺘَﻮَﻯ

أثرٌ صحيح : أجرجه اللالكائي في شرح أصول الاعتقاد 2-398

“አላህ ከዓርሽ በላይ ከፍ ያለው እንዴት ነው?” ተባሉ። እርሳቸዉም እንዲህ ብለው መለሱ፦ “የአላህ ከዓርሽ በላይ መሆን “ኢስቲዋዕ” ለማንም ሰው ግልጽ ነው። ‘እንዴት?’ የሚለው ጥያቄ በአዕምሮ ምርምር የሚደረስበት አይደለም፤ ይህንንም ተቀብሎ ማመን ግዴታ ነው፤ ስለዚህ መጠየቅ በዲን ዉስጥ የመጣ ፈጠራ “ቢድዓ” ነው” ።

https://t.me/Abu_babelheyr_bin_Sadik


✍️የሰላተል ጀናዛ አሰጋገድ‼️


ቡዙ ወንድሞች ሰላተል ጀናዛ ለምን አትሰግዱም ስባሉ  ምን ተብሎ እንደምሰገድ አናዉቅም  ይላሉ

እና ሼር እናድርገው  በራከላሁ ፊኩም
     ===============

    🔘ወደ ሰላት ከመገባቱ በፊት

💫እንደ የትኛውም ሰላት ሙሉ የሆነ ውዱእ ይደረጋል።
💫እንደ የትኛውም ሰላት ወደ ቂብላ ይቀጣጫል።
💫እንደ የትኛውም ሰላት ሰፍ ይስተካከላል።
💫እንደ የትኛውም ሰላት ማእሙኖች ኢማሙን ተከትለው ይቆማሉ።

       🔘የሰላቱ አሰጋገድ

✍️የመጀመሪያው ተክቢራ ይባልና…
ሱረቱል ፋቲሃ ይቀራል።
          {بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ}
     {الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
                 الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
                   مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ
           إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ
               اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ
              صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ
         غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا الضَّالِّينَ}
ይህንን ሲጨርስ ሁለተኛው ተክቢራ ይላል።

✍️ከሁለተኛው ተክቢራ በኋላ……
በነብዩﷺ ላይ ሰለዋት ያወርዳል።
«اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد، اللهم بارك على محمد وعلى آل محمد كما باركت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد»
ይልና ሶስተኛው ተክቢራ ይላል

✍️ከሶስተኛው ተክቢራ በኋላ……
ለሟቹ ዱዓ ያደርግለታል። ለምሳሌ ከመጡ ዱዓዎች መሃል……
«اللهم اغفر له وارحمه، وعافه واعف عنه،
   وأكرم نزله، ووسع مدخله، واغسله بالماء والثلج والبرد، ونقه من الخطايا كما ينقى الثوب الأبيض من الدنس،
  اللهم أبدله دارًا خيرًا من داره، وأهلًا خيرًا من أهله،
  اللهم أدخله الجنة، وأعذه من عذاب القبر، ومن عذاب النار، ووسع له في قبره، ونور له فيه»
ከዚህም ውጪ ያሉ ዱዓዎች የቻለውን ያደርግለታል። ይህንን ሲጨርስ አራተኛው ተክቢራ ይላል።

✍️ከአራተኛው ተክቢራ በኋላ…
ቲንሽ ዝም ይልና እዛው በቆመበት ወደ ቀኝና ወደ ግራው ያሰላምታል።
«السلام عليكم ورحمة الله,
       السلام عليكم ورحمة الله»
ይላል።

  
        🔘አንዳንድ ነጥቦች

💫ጀናዛው ከኢማሙ ፊት ይቀመጣል።
ጀናዛው የወንድ ከሆነ;
   ኢማሙ ጭንቅላቱጋ ይቆማል።
ጀናዛው የሴት ከሆነ;
   ኢማሙ ወገቧ አካባቢ ይቆማል።

💫ባለው የሰጋጆች ብዛት ረዥም ሰፍ ከመስራት ይልቅ ሰፎቹ መብዛታቸው ይመረጣል።

💫አራቱንም ተክቢራዎች ሲባሉ እጅ ማንሳቱ የተሻለ የተወደደ ነው።

💫አንድ ሰው ኢማሙ የተወሰነ ከሰገደ በኋላ ደርሶ ወደ ሰላቱ ቢገባ የሚጀምረው ኢማሙ ከደረሰበት ቦታ ሳይሆን ከመጀመሪያው ቦታ ነው።
ለምሳሌ፦
ኢማሙ የሁለተኛው ተክቢራ ሲያደርግ ቢደርስ እሱ የሚያደርገው ሰለዋት ማውረድ ሳይሆን ፋቲሃን መቅራት ነው; በመጨረሻ ኢማሙ ሲያሰላምት ቶሎ ቶሎ ብሎ ይጨርስና ያሰላምታል።

💫ጀናዛው የሆነ ቦታ ተሰግዶበት የተቀበረ ከሆነ ሌላ ቦታ "ሰላተል غይብ" ተብሎ አይሰገድበትም።

💫አንድ ሰው ሰላተል ጀናዛ ቢያመልጠውና መስገድ ቢፈልግ ጀናዛው ቢቀበር እንኳ ቀብሩ አጠገብ ሄዶ ይሰግድበታል።

        🔘ማሳሰቢያ

✏️ቀላል ከመሆኑም ጋ ብዙሃኖች የሚከብድ መስሏቸው ብዙ ጊዜ ከመስገድ ሲቆጠቡ ይታያሉና ሼር አድርጉላቸው።

20 last posts shown.